2022-08-03 22:43:30
“የበጎ ፍቃድ ተግባሮቻችን በአጋሮቻችን ትብብር ውጤታማ ይሆናሉ”
****
የቦሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከግሬስ ላይፍ ኮሚዩኒቲ ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር በወረዳ 4 የአቅመ ደካማ ነዋሪ መኖሪያ ቤት እድሳት አስጀመረ።
በተያዘው የክረምት ወራት በክፍለ ከተማው በመካሄድ ላይ ባለው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በርካታ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች በአዲስ መልክ እየተገነቡ እንደሚገኙና ከመካከላቸውም የተጠናቀቁ ቤቶች እንዳሉ የተናገሩት የቦሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረሰ ፈይሳ፣ ቤተ እምነቶች “የሕዝቡ ችግር የእኛ ችግር ነው” በማለትና ከመንግሥት ጎን በመቆም እያደረጉ ያለው የማኅበረሰብ ችግሮችን የማቃለል ጥረት የሚመሰገን መሆኑን አክለው ተናግረዋል። “በክፍለ ከተማችን ከሃይማኖት ተቋማት ጋር በሰላም ዙሪያ ሰፊ ሥራዎችን ስንሠራ ቆይተናል” ያሉት ኃላፊው፣ በበጎ ተግባር ዙሪያ የተጀመረው የጋራ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አክለው ገልጸዋል።
የግሬስ ላይፍ ኮሚዩኒቲ ቤተክርስቲያን መጋቢ አማረ ሐጎስ በበኩላቸው በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ያሉ ባለሙያዎችና ባለሀብቶች ከእምነት ተልዕኮ ባለፈ የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት በበጎ ፍቃድ ተግባራት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ገልጸው፣ “ከቦሌ ክፍለ ከተማ ጋር ላለፉት አምስት ዓመታት በተማሪዎች ምገባና ሌሎች ዘርፎች ላይ ስንሳተፍ ቆይተናል፣ አሁንም በአቅመ ደካማ ወገኖች የቤት እድሳት ላይ ያለንን ተሳትፎ በማሳደግ በቀጣይ ሁለትና ከዚያ በላይ ቤቶችን በአዲስ መልክ እንገነባለን” ብለዋል። የክፍለ ከተማው አስተዳደር የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ዕቅድ አዘጋጅቶ ቤተክርስቲያኗ ተሳታፊ እንድትሆን ሁኔታዎችን በማመቻቸቱ መጋቢ አማረ ምስጋና አቅርበዋል።
በዛሬው ዕለት የተጀመረው የቤት ግንባታ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ለማወቅ ተችሏል።
ሐምሌ 27/2014
መረጃዎቻችንን በአማራጭ ለማግኘት: -
በትዊተር: twitter.com/bole_comm
በዩቲዩብ: https://www.youtube.com/channel/UCTc1t2_k9iNhr80vlG5zMJg
በቴሌግራም: https://t.me/bolecommunication
ኢንስታግራም: instagram.com/bole_communication
883 viewsME, 19:43