2022-09-01 08:32:12
"#ሌላኛዋ_ማርያም " (ማቴ.27:61፤ ማቴ.28:1)
በሐዲስ ኪዳን "ማርያም" በሚል ስም ከሰባት ያላነሱ ሴቶች ተጠርተውበታል ፣ መ"ና"ፍ"ቃ"ን ከድንግል ማርያም በቀር ስለሌሎቹ "ማርያሞች" ይዘምራሉ ፣ ይሰብኳቸዋልም ፣ በላያቸው የሰፈረው አስለፍልፍ ግን ስለ ድንግል ማርያም ክብር እንዲናገሩ አያደርጋቸውም ።
#ከድንግል ማርያም በቀር በሐዲስ ኪዳን የተጠቀሱት "ሁሉም ማርያሞች" ባለትዳር የነበሩና ወንድ የሚያውቁ ናቸው ፣ ድንግል ማርያም ግን ዘላለማዊት ድንግል ስትሆን መቼም ቢሆን ወንድ የማታውቅ ንጽሕት ናት ። (ሉቃ.1:26) ፣ የሁሉም "ማርያሞች" ታሪካቸው በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጻፈልን አንዳቸው ከሌላቸው የሚለዩበት መለያ ቅጽል አላቸው ።
#በዚህ የመለያ ቅጽልነት መሠረት ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ድንግል ማርያምን በተለይ ከታዋቂዋ "ባለትዳሯ ማርያም" የተለየች መሆኗን ሲያሳይ፤ ሌላኛዋ ስመ ሞክሼ "ሁለተኛዋ ማርያም" የምትባል ሌላ ማርያም እንዳለች ይነግረናል ። እርሷም ከድንግል ማርያም የምትለይ ሌላ ማርያም መሆኗን ለማሳወቅ መጽሐፍ ቅዱስ "ሁለተኛዋ ማርያም" ሲል መለያ ቅጽል ይሰጣታል ።(ማቴ.27:61፤ ማቴ.28:1) "ሁለተኛዋ ማርያም" ተብሎ መጠራትም አንደኛ ማርያምነትን ለድንግል ማርያም ሰጥቶ በመናገር የመጣ አገላለጽ ነው ።
#ጎበዝ !!!
#አንደኛዋ ማርያም ፣ ድንግል ማርያምና የሁለተኛዋ ማርያም ባለትዳሯ ማርያም ፍጹም የተለያዩ መሆናቸውን መጽሐፍ ቅዱስ በማያሻማ መልኩ ይገልጻል ። በርግጥ "ማርያም" የሚለው ስመ ሞክሼ ሁለቱም ማርያሞች ስለሚጠሩበት መለያ ቅጽሉን እስካላወቁ ድረስ ብዙዎች አሁንም ሊደናገሩ ይችላሉ ። መጽሐፍ ቅዱስ ግን ድንግል ማርያምን አንደኛዋ ማርያም በማለቱ ሌላኛዋን "ባለትዳሯ" ማርያምን "ሁለተኛዋ ማርያም" ከሚለው መለያ ቅጽል ጋር ሁለቱ "ማርያሞች" የሚለዩበት ዝርዝር ማንነት ስላስቀመጠልን መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነብ ሰው መደናገር የለበትም ።
#ድንግል ማርያም በመልአክ ብሥራት ያለወንድ ዘር ኢየሱስን ወልዳልናለች ፣ ከኢየሱስም በቀር ልጅ የላትም ፤ እስከ መጨረሻው ወንድ የማታውቅ ዘላለማዊ ድንግል ናት ፣፤ "ሁለተኛዋ ማርያም" ግን ትዳር መስርታ ልጆች ያሏት ናት ። ልጆቿም ያዕቆብ ፣ ዮሳ፣ ስምዖን ፣ ይሁዳ ይባላሉ ። (ማቴዎስ.13:53፣ ማር.3:31)
ድንግል ማርያም የኢየሱስ እናት ተብላ ስትጠቀስ ፣ "ሁለተኛዋ ማርያም" የእነ ዮሳ እናት ማርያም ተብላ ትታወቃለች ።
#በመጽሐፍ ቅዱስ ድንግል ማርያም ፣ የኢየሱስ እናት ተብላ ተጠራች እንጅ የያዕቆብ ፣ የዮሳ፣ የስምዖን ፣ የይሁዳ እናት ተብላ አልተጠራችም ። ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ የተነሱ ሐሰተኛ ሃይማኖተኞች የእነ ዮሳን ( ያዕቆብ ፣ ዮሳ፣ ስምዖን ፣ ይሁዳ ) እናት "የሁለተኛዋን ማርያም" ማንነት ከድንግል ማርያም ጋር እያቆራኙ ከእውነተኛይቱ ሃይማኖት ሕዝቡን አስወጥተውታል ። (ማቴዎስ.13:53፣ ማር.3:31፤ማር.6:3) በዛሬ ዘመንም "ሐሳውያን መሲሖች"" በኦርቶዶክስ ላይ በሚያደርጉት የቅሰጣ ዘመቻ ድንግል ማርያም ያይደለች ሌላኛዋን ማለትም "የሁለተኛዋን ማርያም" ስም እየጠሩ ከድንግል ማርያም ጋር ማንነቷን እያቀላቀሉ መንጋቸውን ያደናግሩበታል ። የኢየሱስን እናት፣ የድንግል ማርያምን ንጽሕና ፣ቅድስናና ድንግልና ላለመቀበል በላያቸው የሰፈረው ክፉ መንፈስ ያስለፈልፋቸዋል ።
#ጎበዝ !!!
#በ"ድንግል ማርያም"ና በ"ሁለተኛዋ ማርያም" መካከል ሰፊ ልዩነት አለ ። #ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ስለ እኛ ሲሞት፣ ወዲያው ከመቀበሩ በፊት የኢየሱስ እናት ድንግል ማርያምን ዮሐንስ ወደ ቤቱ ወስዷታል ፣(ዮሐንስ.19:27) የእነዮሳ እናት ባለትዳሯ "ሁለተኛዋ ማርያም" ግን ኢየሱስን ከመስቀል አውርደው ወደ መቃብር ሲያወርዱት ሁሉ ትመለከት ነበር ፤ (ማርቆስ.15:47፤ ማርቆስ 16:1) ፣ የኢየሱስ እናት ድንግል ማርያም አማኝ ናት ፤ ልጇ አምላክ እንደሆነና ሞትን ድል አድርጎ በሦስተኛው ቀን እንደሚነሳ ታውቃለች ። የእነዮሳ እናት "ሁለተኛዋ ማርያም" ግን ተጠራጣሪ ናት ። ኢየሱስ ክርስቶስ በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣም አታውቅም ነበር ። ሰውነቱን ሽቱ ለመቀባት በሦስተኛው ቀን ወደ መቃብሩ ተጉዛለች (ማር. .16:1፤ማቴ.28:1) ፣
#የእግዚአንሔር ቃል የሚነግረን እውነታ ይህ ሆኖ ሳለ ጸረ ኦርቶዶክሶችና ሐሰተኞቹ በሚያደርጉት ቅሰጣ የኢየሱስ እናት ድንግል ማርያምን ሊያስጥሉን ስለፈለጉ የኢየሱስን አምላክነት ያልተገነዘበችውን የእነ ዮሳን እናት "ሁለተኛዋ ማርያምን" ስም እየጠሩ ኦርቶዶክሳውያንን ሊያሳስቱ ዘመቻ ከፍተውብናል ። (ማርቆስ .6:3)
#ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ ኃጢአት ሀሞት ሲያጠጡት መራራውን ታግሶና በመስቀል ላይም ችንካሩን ታግሶ ባለበት ሁኔታ "እነሆ እናትህ !!" ብሎ የሰጠንን እናቱን ድንግል ማርያምን ፤ ማንም አይነጥቀንም ።እርሷ የሥርዐተ አምልኮአችን ምልክት ናት ፤
#ስለእኛ በመስቀል የተሰቀለውን ኢየሱስ ክርስቶስን ልናመልክ ስለተፈጠርን ፣ በመስቀሉ ስር የተሰጠችንን ድንግል ማርያምን ልናመሰግን ስለተወለድን፣ መስቀሉን ደግሞ ልናከብር ስለተመረጥን እጅግ ደስ ሊለን ይገባል ።
#መቼም ቢሆን ከታች ቮድካ ሰውሮ ከላይ ኮካ የሚጠጣ ሰካራም "ሐሳዊ መሲሕ" ኦርቶዶክሳውያንን ሊያስት አይችልም ። ይኸው ነው።
https://t.me/abagiyorgismnale
ሊቀ ጠበብት ዶ/ር ዘሪሁን ሙላቱ
55 viewsMichael Eshetu, edited 05:32