Get Mystery Box with random crypto!

መገለጥ - Revelation

የቴሌግራም ቻናል አርማ gracewins — መገለጥ - Revelation
የቴሌግራም ቻናል አርማ gracewins — መገለጥ - Revelation
የሰርጥ አድራሻ: @gracewins
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.31K
የሰርጥ መግለጫ

ክርስቶስን ያወቀና በክርስቶስ ያገኘውን በሙሉነት የሚጠቀም ትውልድ ማየት
#የተለያዩ ትምህርቶች እናቀርባለን
#እህቶች ይበረታታሉ
#የሌሎች ወንድሞች እና እህቶች ትምህርት የባለቤትነት መብት ጠብቀን ወይም ምንጭ ጠቅሰን እናቀርባለን
Inbox 😍 @Lovewithhopee

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-15 16:02:13
ዘሪቱ

እጅግ የበሰለ ስብዕና በይቅርታ የተሞላ ልብ እጅግ በጣም ጥበበኛ እና ማስተዋል የበዛላት ሴት ከመንጋው ጉዞ ተነጥላ በቃሉ መንገድ የተጓዘች በትህትና የተሞላች ሴት ሀይማኖተኛ ሳይሆን አዲስ ፍጥረት ስንሆን የምንገልጠው ስብዕና ውድ ሰዎች ሊያወርዷቸው ለመጡት ሁሉ አይወርዱም የሚያደርጉት ነገር ቢኖር የልጁን መልክ መግለጥ እንጂ። እግዚአብሔር ያክብርልኝ በክርስቶስ ደም የተዛመድን እህቴ ዘሪቱ ፀጋ እና ህይወት ይብዛልሽ
አዲሱን ቪድዮ ተመልከቱት




አገልጋይ Dave khc

https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
195 viewsedited  13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 18:46:28 #መንፈሳዊ_ባለጠግነት_8 (የኤፌሶን 1፡9-10 ጥናት )
#ስጋዬን_ተጋርቶ_ሚስጥሩን_አጋርቶኛል
.
#እግዚአብሔር በክርስቶስ ሊያደርገው የወደደውን ሚስጥሩን አጋርቶናል። በእኛ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ሚስጥር በክርስቶስ ኢየሱስ የተደረገው እና ሊደረገው ያለው ሀሳቡ ነው። ይህ ምሥጢር ከሁለም ሰዎች ተሰውሮ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ለሚያምኑት ሁሉ የተገለጠ ነው። እግዚአብሔር የሰውን ማንነት ተጋርቶ በክርስቶስ ሊያደርግ ያለውን ሚስጥሩን አጋርቶናል። ሚስጥሩን የአባቶች ተስፋ የነቢያት ትንቢት የፍጥረታት ናፍቆት የሆነው ክርስቶስ በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በእርሱ ለመጠቅለል ነው። የእግዚአብሔር የመጨረሻው ሀሳቡ በአንድ ልጁ ለመጨረሻ ጊዜ አለምን የመጠቅለል ለራሱ የማስገዛት ሀሳብ ነው ያለው።
.
https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
#በእርግጥ በክርስቶስ የምትገኘው ቤተክርስቲያን ከብሉይ ኪዳን አገልጋዮች የተሰወረ ሚስጥር ነው። የኢየሱስ መወለድ መከራን መቀበል እና ዳግም መምጣት አሻግረው ተመለከቱ እንጂ በመካከል ያለውን የቤተክርስቲያን ዘመን ማየት አልቻሉም። የቤተክርስቲያን ዘመን ከብሉይ ኪዳን ሰዎች ተሰውሮ የቆየ ህይወት ነው። እግዚአብሔር በክርስቶስ ያዘጋጀው የደህንነት ስራ በክርስቶስ የተደረገልን በክርስቶስ ያገኘነው የአዲስ ኪዳን ህይወት የከበረ የእግዚአብሔር ህይወት ነው። ከብሉይ ኪደን ቅዱሳን ከሰማይ መላዕክት በዚህ ዘመን በጨለማው ውስጥ ካለው የተሰወረ ህይወት ተሰጥቶናል።
https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
ለማለት ያልተባለ በመሆን የሆነው ከዘላለም ውስጥ የወጣ ብረሃን ዝም ብሎ ይበራል ማንነቱ ብርሃን ነው ብርሃኑን ወይም ሚስጥሩን አካፍሎልናል። ጨለማ በነገሰው ልባችን ውስ ክብሩን እና እውቀቱ ይገለጥ ዘንድ በጨለማው ላይ ብርሃን ይብራ ያለው እግዚአብሔር ብርሃን አድርጓል። እግዚአብሔር አለምን ያዳነበት ፈቃዱ ሚስጥር ነው። የተገለጠ ቢመስልም የተሰወረ ነው።
.
https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
#መጠቅለል የሚለው በክርስቶስ ውስጥ መሰወርን ወይም በክርስቶስ ስልጣንን ስር መሆንን ያለመክታል፡፡ እውነት ነው ይህ ክፍል በመጨረሻው ግዜ እግዚአብሔር በሰማይም በምድርም ያለውን ሁሉ በኢየሱስ ስር እንዲውል ማድረጉን ያመለክታል፡፡ ሀጢያት ወደ አለም ከገባበት ግዜ ጀምሮ ነገር አለሙ ሁሉ ተበላሽቷል፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር ተለየ፡፡ ሰው ከሰውም ተለየ፡፡ ከሰው የሀጢያት ብዛት የተነሳ አይሁድን በራሱ በእግዚአብሔር ምርጫ ሊመጣ ላለው መንገድ ይሆን ዘንድ መረጠ፡፡ሀጢያት ሁሉንም ነገር ኢያፈራረሰ ቢሆንም አምላክ ግን በዘመነ ፍፃሜ ሁሉንም በክርስቶስ ይጠቀልል ዘንድ ተገለጠ፡፡ እናም በዚህ ዘላለማዊ እቅድ ውስጥ ገብቼ በክርስቶስ ተጠቅልያለሁ፡፡
https://telegram.me/gracewins
አገልጋይ Dave khc
623 views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 13:09:31 #መንፈሳዊ_ባለጠግነት_7 (የኤፌ 1፡8 ጥናት ) “ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን።” ኤፌ 1:8
ምንም ያልተነካ ያልተነካካ የጥበብና የእውቀት መዝገብ በክርስቶስ ዘንድ አለ።
.
#ዞዊ የሆነው የእግዚአብሔር ስጦታ የአቅርቦታችን ስፍራ ነው፡፡ ህይወት እንዲበዛላቹ እንዲትረፈረፍላቹ መጥቻለሁ ያለ ጌታ ስጦታው እልፍ ነው። በእግዚአብሔር ህይወት ውስጥ ካገኘናቸው እልፍ ስጦታዎች ውስጥ ጥበብና እውቀት (ማስተዋል) ነው። ከጠቢብ ሰለምን በሚበልጠው በኢየሱስ የእግዚአብሔር ጥበብ ሞልቶብናል። በክርስቶስ ያለ ሰው ከሰለሞን በተሻለ በእግዚአብሔር ዘንድ ጠቢብ ተደርጓል።ምክንያቱም ሰለሞን በእግዚአብሔር ፊት የሚያስቆመው የእግዚአብሔር ጥበብ ስላነበረው። “በክርስቶስ ኢየሱስ ለመሆን የበቃችሁት ከእርሱ የተነሣ ነው፤ እርሱ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበባችን፣ ጽድቃችንና ቅድስናችን፣ ቤዛችንም ሆኖአል።”1ቆ 1፥30
.
#ጥበብ በዚህ አለም 'ጥበበኞች' ነን ከሚሉት እጅግ የራቀች በክርስቶስ ውስጥ የምተገኝ ነች። በዓለም ላይ ትልቁ ድንቁርና አዋቂ ነኝ ብሎ ማሰብ ነው። “ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ፥” ሮሜ 1፥22።ደግሞ ምንም ያልተነካ ያልተነካካ የጥበብና የእውቀት መዝገብ በክርስቶስ ዘንድ አለ።“የተሰወረ የጥበብና የእውቀት መዝገብ ሁሉ በእርሱ ነውና።” ቆላ 2፥3።ማንም ጥበብ ቢጎድለው ተዝቆ ከማያልቀው ሳይሰስት በልግስና ከሚሰጠው ከእግዚአብሔር ዘንድ መጠየቅ ይችላል።በእግዚአብሔር ጥበብ (በላይኛይቱ ጥበብ)የተሞላ አማኝ ሕይወትን የሚገዛ እግዚአብሔር የሚወደውን የሚከተል ሰው ነው።
. https://telegram.me/gracewins
#ሰማያዊ ጠቢብ ጊዜን ይገዛል በይቅርታ ይሞላል የፅድቅ ኑሮን ይፈልጋል ከዚች አለም ጥበብ ጋር በማይመች መንገድ አይጠመድም እምነት እንጂ ፌዘኝነት ትጋት እንጂ ስንፍናን አይሞላም። በአኗኗር ጥበብ እንጂ በንግግር የምንበልጠው አለም የለም ምክንያቱም ጥበብ ከእግዚአብሔር ዘንድ የምትቀበለው በዚህ አለም የምትገልጠው ኑሮ ነው። አኗኗሯችን እንደ ሰማይ ጥበብ ይሆን? አይመስለኝም ምክንያቱም በዚች አለም ወይም ምድራዊ ጥበብ ተሸንፍ የወደቀ እልፍት ትውልድ እያየን ነው። ምስጋና ያጠረው ለእርቅ ለገርነት ለእሺታ የተሸነፍ አማኞች እያየን ነው። በምስጋና የማይሞሉ ሁሉን ማጣጣል ሁሉን መናቅ የሚወዱ በጥላቻና በትዕቢት የሚወጠሩ ሞልተዋል።
. https://telegram.me/gracewins
#አብዛኞቻችን እንደ እግዚአብሔር ልጆች በባለጠግት መኖር ሲገባን በመረዳት (በእውቀት) ባለጠጋ ስላልሆንን በክርስቶስ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ፊት ያለንን ማንነት ባለማወቃችን በመንፈሳዊ ህይወታችን ጎስቋሎች ነን። እግዚአብሔር በክርስቶስ በኩል የተገለጠው ሰዎች እንዲያውቁት ነው። ቅድም እንዳልን ምንም ያልተነካካ የእውቀት እና የጥበብ ሀብት ያለው በክርስቶስ ውስጥ ነው። ኢየሱስ በማወቅ ባለጠጋ ስንሆን በኢየሱስ ውስጥ ያለውን የተሰወረውን ሀብት እየመነዘርን በሚገባን ልክ እንጠቀማለን።
. https://telegram.me/gracewins
#በዚህ ምድር ላይ ተምረህ አንተን የበቃህ ዶክተር አስደማሚ ኢንጂነር አፅም መርማሪ አርኪዮጂስት አይምሮ መርማሪ ሳይኮሎጂስት ሊያደርግህ የሚችሉ በርካታ እውቀቶች አሉ ትክክለኛ የእግዚአብሔር ህይወት ለመካፈል እና የእግዚአብሔር ሰው ለመሆን ብቸኛው ትምህርት ኢየሱስ ነው። ልብ በሚሰጠው ነገር ያድጋል አይምሮ በሚያስገባው ነገር ያድጋል። በማወቅ ወይም በማስተዋል ውስጥ ለእግዚአብሔር ምስጋና እናበዛለን። ጥበብን የምትገለጠው በማትሞላ እውቀት ነው። እግዚአብሔር እውቀት እና ጠበብ በእኛ ውስጥ በሙላት ይግለጠው።
.
https://telegram.me/gracewins
አገልጋይ Dave khc
373 views10:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 00:51:00 #በሀጢያት_ላይ_መራራ_ትውልድ
.https://telegram.me/gracewins
#እግዚአብሔር ልጁን የገደለበት የመስቀሉ ስራ ምን ያህል እንደሚወደን የሚያሳይ የመጨረሻ የፍቅር ጥግ ሲሆን በተዘዋዋሪ እግዚአብሔር ለሀጢያት ያለውን ጥላቻ ያሳያል። ያህዌ በሀጢያት ላይ እንደማያመቻምች ማሳያው ብቸኛ እና ምትክ የሌለው ልጁን ሳይራራ መስጠቱ ነው። እግዚአብሔር በሀጢያት ላይ መራር በሆነበት በዚያን ልክ በሀጢያት ላይ የመረረ ትውልድ ያስፈልገናል። ሀጢያት እሰከሞት የሚጋፈጥ አማኝ ያሻናል።
.
#እግዚአብሔር በጨከነበት ጉዳይ የምንራራበት ምክንያት የለንም። እግዚአብሔር በተቆጣው ጉዳይ ፈገግ የምንልበት ምክንያት የለንም። ልጁ በሞተበት ሀጢያት ላይ ህያው የምሆንበት ምክንያት የለኝም። አብ በመስቀል ላይ ሀጢያት ማየት እንዳልቻለ ጀርባውን ለሀጢያት እንደሰጠ ሀጢያት የሚጠላ ሀጢያት ማየት የማይወድ ለሀጢያት ጀርባውን የሰጠ የፅድቅ መንገድ የሚከተል ትውልድ ልንሆን ይገባል።
https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
አገልጋይ Dave khc
594 views21:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 23:49:56 #በክፋ_እንጂ_በቤተክርስቲያን_እጅ_አልተያዘም
በእኛ መቀደስ የምትቀደስ ከእርኩሰት የምታመልጥ ገነት የምትሆን አለም የለችም።
.
#ሰሞኑን ለኢትዮጲያ የውድቀት ምክንያት ቤተክርስቲያን ነች ቤተ ክርስቲያን ጤነኛ ብትሆን ሀገር ጤነኛ ትሆናለች የሚሉ ንግግሮች በተደጋጋሚ እየሰማሁ ስለሆነ ይህንን ሀሳብ ላነሳ ወደድኩ። ቤተክርስቲያን የዚህ አለም ውድቀት ( የኢትዮጵያ ውድቀት ) ምክንያት አይደለችም። ቤተክርስቲያን ስለወደቀች ነው ሀገር የወደቀችው? ቤተክርስቲያን ስለወደቀች ነው በዘረኝነት ኢትዮጵያ የምትታመሰው? አይመስለኝም ቤተክርስቲያን ለሰው መዳን ምክንያት እንጂ ለአለም ወይም ለሀገር መበላሸት ምክንያት ፈፅሞ አትሆንም። የቤተክርስቲያን ፍፁም ንፅህና የአለምን ውድቀት የትውልድ መበላሸት አይገታውም። ቤተክርስቲያን የመጨረሻውን ዘመን መምጣት አትገታም አስጨናቂውን ህይወት መለወጥ አትችልም። ይልቁንም እውነተኛ ልጆቿን በፅድቅ እንዲኖሩ ከማድረግ እና ነፍሳት ከአለም ከመናጠቅ ውጪ ኃላፊነት የለባትም።
.
#ከተንኮተኮተውና ከወደቀው አለም በደሙ ተዋጅተው የመጡ አማኞች ለአለም ክፋት እና ውደቀት ምክንያት የሚሆኑበት ምክንያት አይታየኝም። በቃ አለም ወደ መጥፋቷ ክርስቶስም ወደ መምጣቱ እየተቃረበች ነው። መላው አለም በክፋ እጅ እንጂ በቤተክርስቲያን እጅ አልተያዘም። ስለዚህ የወደቀው አለም በወደቀው እጅ ውስጥ ነው ቤተክርስቲያን ከዚያ የመናጠቅ ስራ ነው ያላት። ጨርሶ በወደቀ አለም ውርጥ የቤተክርስቲያን ድክመት የሚጨምረው ውድቀት የለም።ከድካም ብንወጣ እግዚአብሔር ብንመስል ብንቆም ለራሳችን ለምንናጠቀው ትውልድ እንጂ እየከፋ የሚሄደውን ዘመን የምንገታው አይደለም። በእኛ መቀደስ የምትቀደስ ከእርኩሰት የምታመልጥ ገነት የምትሆን አለም የለችም። በእኛ ውበት ከጥፋት ከውድመት የምታመልጥ አለም የለችም።

በውስጣችን ያለውን የክርስቶስ መዓዛ እየገለጥን ለሚጠፋው የሞት ሽታ ለሚድኑት የህይወት ሽታ እየሆንን በድል መኖር የእግዚአብሔር መልክ እየገለጡ ነፍሳትን መማረክ አማኞችን ለዳግም ምፅአት ማዘጋጀት የተሰጠን ሀላፊነት ነው። የአለም ውድቀት አስጨናቂው ዘመን እየመጣ ትውልድ በከፋ ማዕበል በሚናጥበት ዘመን ቤተክርስቲያን ግን “አንተ ግን ትምህርቴንና አካሄዴን አሳቤንም እምነቴንም ትዕግሥቴንም ፍቅሬንም መጽናቴንም ስደቴንም መከራዬንም ተከተልህ፤” 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥10

አገልጋይ Dave khc ( የግል እሳብዬ ነው)

https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
405 views20:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 00:44:50 #አታገልግሉት
.
#እግዚአብሔር በክርስቶስ የጠራችሁ በመጀመሪያ ማይክ እንድትይዙለት አይደለም ወይም መፅሐፍ ቅዱስ ይዛችሁ እንድትሰብኩለት ወይም እንድታገለግሉት አይደለም። እግዚአብሔር በልጁ በመጀመሪያ የጠራችሁ በደሙ ፀድቀህ የእግዚአብሔር ልጅ እንድትሆንለት ነው። ልጅነት ደግሞ በህይወት የሚገለጥ እንጂ መድረክ እና አደባባይ የሚሻ አይደለም። ልጅነት በምንም ምክንያት አትለውጥም። ልጅነት በምንም ምክንያት ለድርድር አይቀርብም።
.https://telegram.me/gracewins
#ቸርች አገልግሎት አልሰጠችኝም መድረክ አልሰጠችኝም ብለው ወደ አለም የሚሄዱ ሰዎች አገልግሎትን የስኬት መንገድ አገልግሎትን የገንዘብ ማግኛና የብልጥግና መንገድ አድርገው ስላሰቡት እንጂ ኢየሱሴን ባለማገልገላቸው ለትውልድ ባለ መግለጣቸው ተበሳጭተው አይደለም። የአግልግሎት ቅናት ወይም ፍቅር ወደ አለም የሚመራበት መንገድ ለእኔ አይታየኝም። ኢየሱሴን የማገልገል ፍቅር አናትህ ላይ ሲወጣ ኢየሱስ ለማገልገል ወደ አለማዊነት ትሄዳለህ? በምንም ምክንያት ልጅነትን የሚተካ አገልግሎት ፈፅሞ የለም።
. https://telegram.me/gracewins
#በክርስቶስ የተሰጠን ሳታውቅ የተደረገልህን ሳታውቅ እግዚአብሔር ለማገልገል አትድከም የሚያስፈልገው ጥቂት ነገር እርሱ ከእግሩ ስር ቁጭ ብሎ ልጅነት ማጣጣም። የተሰጠህን ሳታውቅ አታገልግል የተጠራኸው ለምን እንደሆነ ሳታውቅ አታገልግል። ስሜትህ ሲቀጣጠል አለምን መያዝ ይናፍቅሀል እምነት ሲቀጣጠል ግን መንፈሳዊነት እና እግዚአብሔር መያዝ ይናፍቃል። ልጅነት ስሜት አይደለም አገልግሎት ቢሆን ስሜት አይደለም። የአማኝ ትልቁ ውድቀት ዓለምን የግልህ ለማድረግ ያሰብህ ቀን ነው ። ትልቁ መሳሳት እግዚአብሔር በአለም በለወጥክበት ቀን ነው። ትልቅ ድፍረት ወደ ትፋትህ መሄድ ነው።
.https://telegram.me/gracewins
#አብርሃም የሚበልጠው እግዚአብሔር ስላየ ነው ልጁን ለመስዋዕትነት የሰጠው። ራስህን እና የአንተ የሆነው ነገር ለእግዚአብሔር ብቻ የምትሰዋው ከአንተ እና ከአንተ ነገር በላይ የሆነው እግዚአብሔር ማየት ስትችል ነው። አለማዊ ከመሆናችሁ በላይ ከእግዚአብሔር ጋር የነበራችሁ ጊዜ ለመበቀል ይመስል በአደባባይ የሰይጣን አገልጋይ ሆኖ መገለጥ የመስቀሉ ፍቅር እንዳልገባችሁ ማሳያ ነው። የኤሊ ልጆችን ካህን የመሆን ስልጣን ወይም እግዚአብሔር የማገልገል መብት ተሰጧቸው ነበር። “የዔሊም ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አያውቁም ነበር። 1ኛ ሳሙ 2፥12
በቤቱ እያገለገሉ እግዚአብሔር ካለማወቅ ምናምንቴ ከመሆን እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ።
.
በDave khc ተፃፈ
856 viewsedited  21:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 18:12:53 Live stream finished (9 minutes)
15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 18:03:53 Live stream started
15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 10:40:38 #መንፈሳዊ_ባለጠግነት_6 (የኤፌ 1፡7 )
#በህይወት_መኖር_መብቴ_ነው
“በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።” ኤፌ 1፥7
#የእግዚአብሔር_የፀጋውን_ባለጠግነት_በአማኝ_ውስጥ_ገልጧል።
.
#ከውዶች ሁሉ በተወደደ ከምርጦች ሁሉ በተመረጠ በክርስቶስ ኢየሱስ ነው እግዚአብሔር ያደረገልንን ሁሉ ያደረገልን። ለእኛ ሁለት ያለው አንድ ይስጥ ብሎ ሲመክረን እርሱ ግን ያለውን አንድ ልጁን ሰጠን።እግዚአብሔር የሚወደውን አንድያ ልጁን ምትክ የሌለውን ሰጠን። እግዚአብሔር ባለጠጋ ነው። ባለጠጋ ነው ማለት ሰጥቶ ሰጥቶ ምንም የማይጎድልበት ማለት ነው።
. https://telegram.me/gracewins
#የእግዚአብሔር ባለጠግነት እንደ ሰው አይደለም። የዚህ አለም ባለጠጎች የተሰጣቸው ናቸው ወይም በድካም በጥረት ያገኙት ነው። የትናንት ባለጠጋዎች ነገ ድሆች ይሆናሉ ምን ይዘው አልመጡምና ምንም ይዘው አይሄዱም። የእግዚአብሔር ባለጠግነት ባህሪው ነው። የዚህ አለም ባለጠግነት እርግጠኝነት የለውም። እግዚአብሔር የፀጋውን ባለጠግነት በአማኝ ውስጥ ገልጧል።
.https://telegram.me/gracewins
#በፀጋው ባለጠግነት ውስጥ በደሙ በተደረገ ቤዛነት የበደላችንን ስርየት አገኝተናል። ቤዛነት ማለት ምትክ መሆን ማለት ሲሆን ውድ ልጁ በምትክችን ሞቶልን የበደላችንን ስርየት አግኝተናል። ለእኛ ሞቶ ህይወት የሰጠበት ተዋርዶ ያከበረንበት ሀጢያት ሆኖ ፅድቅ የሆንበት መንገድ ቤዛነት ይባላል። በይስሐቅ ፈንታ የሚሞት በግ እስከ ተገኝ ድረስ ይስሀቅ በህይወት የመኖር መብት እንዳለው ሁሉ በእኔ ምትክ የሚሞት የእግዚአብሔር በግ እስከተገኘ ድረስ በህይወት የመኖር መብት አለኝ። ደም ፈሶልኛልና በህይወት መኖሬ ግድ ነው ደም ፈሶልኛልና የበደሌን ይቅርታ ማግኘት ግድ ነው
. https://telegram.me/gracewins
#"...ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥..." (የዮሐንስ ራእይ 1:5-6)
#“ከኃጢአታችን በደሙ ላጠበን” ሀጢያተኞች መሆናችንን ትላንት የነበረ እውነት ሲሆን በደሙ መታጠባችን ግን የዛሬና የዘለዓለም እውነታ ነው፡፡ “በደሙ”ይህ ከሀጢያታች ለመታጠባችን ቁልፉ “ደሙ” መሆኑን ይናገራል፡፡ ምክንያቱም ደም ሳይፈስ የሀጢያት ስርየት የለምና፡፡
“ላጠበን” የሚለው መፈታት λούω (louō) የሚል የግሪክ ቃል ፍቺ አለው፡፡ በውስጣችን ያለው የሀጢያት ሀይል በደም ተወግዶ ከሀጢያታች ተፈተናል፡፡አንድ ሰው በክርስቶስ ኢየሱስ ሲያምን ከዲያብሎስ ፅኑ እስራት ነፃ ይወጣል፡፡ ይህ ማለት ከነበረበት የጨለማ እና የእስራት ህይወት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመኑ ምክንያት ወጥቷ በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ መግባት እና በክርስቶስ መሰወር ሆኖለታል።
. https://telegram.me/gracewins
#ደሙን አፍስሶ ስጋውን ቆርሶ ሞልቶ የፈሰሰውን የሀጢያት ፅዋዬን አስወግዶ ሞልቶ የተትረፈረፈውን ህይወቱን ሰጠኝ፡፡ በደሙ መርዛማውን የሀጢያት ሀይል አስወግዶ ህይወት የሰጠኝ እርሱ ነው፡፡ በድካሙ ያበረታኝ በእጆቹ ቀዳዳ ውስጥ የፍቅርን ጥግ ያየሁ በድካሙ የበረታው በውርደቱ የከበርኩ በማጣቱ ባለጠጋ የሆንኩት እንዳይጠማኝ ተጠማሁልህ ያለኝ እዳልወጣ እንዳልወርድ ጨረስኩልህ ያለኝ እኔ በእርሱ ምህረት ያገኘሁ ነኝ፡፡ ስለ እኔ የተቅበዘበዘ ሁሉን አለም ደግፎ የያዘው ስለ እኔ አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ እስኪል ደጋፊ ያጠው ለእኔ ነው፡፡ አዎ ፍቅሩ ዘላለማዊ ነው፡፡ “እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።”ኢሳይያስ 53፥5
https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
አገልጋይ Dave khc
1.9K views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 12:06:43 #መንፈሳዊ_ባለጠግነት_5 (የኤፌሶን 1፡5-6ጥናት )
#መወለድ_የመኖር_የመንቀሳቀስ_መጀመርያ_ነው።
“በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን ።” ኤፌ. 1 ፡ 5 ።
.
#የእግዚአብሔር የመስቀሉ ስራ ዋናው አለማ መልኩን የምንመሰል ባህርይውን የምንካፈል ርስቱን የምንወርስ ልጆቹ እንድንሆን ነው። ለእኛ ለመሞት ራሱን ለመስጠት ያስገደደው ማንም የለም የሰው መልካምነት የለም በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ ነው እንጂ። የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ከጊዜ ወይም ከቆይታ በኃላ የመጣ ወይም ዘመን የወለደው ሳይሆን ዘላለማዊ ማንነቱ ነው። ስለዚህ ለእርሱ ልጆች እንድንሆን የተወሰነው ልጆች የምንሆንበት መስዋዕትነት የተወሰነው ከዘላለም ነው።
ይህ ልጅነት አለም ሳይፈጠር የተወሰነ አምላክ ሰው የሆነበት መከራን የተቀበለበት በመስቀል ላይ የሞተበት ሀጢያት የሆነበት ትልቅ ዋጋ የተከፈለበት በመስቀሉ ጣር የተወለድንበት እንጂ ማደጎ የሆንበት አይደለም።
ዮሐንስ 1:12 ሮሜ 8:16-17 1ዮሐንስ 3፡1-2 5፡2
.https://telegram.me/gracewins
#ሰው ዳግመኛ ሲወለድ ከዘላለም ዘመናት በፊት የተወሰነው በመስቀሉ በኩል የተረጋገጠው የልጅነት ስራ ሙሉ ያደርገዋል። በዚህ አለም ውስጥ ለመገለጥ ወይም ለመንቀሳቀስ መወለድ ግድ ነው። መወለድ የመኖር የመንቀሳቀስ መጀመርያ ነው። የትኛውም ልጅነት በውለደት ነው የሚመጣው። አሳዳጊ አጥቶ በጉዲፈቻ የሚያድግም የተወለደበት ዘር ወይም ምንጭ አለው። አስቀድሞ በሰው አለም ለመኖር የተወለደ ሰው በእግዚአብሔር አለም ለመኖር ከእግዚአብሔር መወለድ ይገባዋል። “ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።” ዮሐንስ 3፥3
ከማይጠፋው ከእግዚአብሔር ዘር ተወልደናል የመለኮት ባህሪው ወራሽ የርስቱ ተካፋይ አድርጎናል። የእግዚአብሔር ጉዲፈቻ ልጆች ነን የሚሉ አማኞች አሉ እንደ እምነታቸው ይሁን ነገር ግን ጉዲፈቻ ያሳዳጊው ዘርና መልክ የለውም። ወላጁን መመስል በትምህርት እንጂ በመወለድ ያላገኘ ሰው ነው ጉዲፈቻ። አማኝ ግን በመወለድ ኢየሱስን የመመስል በትምህርት ፍፁም ወደ መምሰል የሚያድግ ነው
.https://telegram.me/gracewins
“በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ።” ኤፌሶን 1፥6
#እግዚአብሔር አንድና ምትክ የሌለውን ልጁን ይሞትልን ዘንድ አደረገ። ሰው ምንም ደካማ ቢሆን ርካሽ አይደለም ውድ ነውና ሰው የሚድነው በውድ ልጁ በኩል ነው ። ከአምላክነት ወደ ሰውነት ከጌትነት ወደ ባርነት ከክብር ወደ ውርደት ያለ ልክ ዝቅ ያለው ያለ ልክ ከፍ ከፍ ሊያደርገን ነው። ሁለት ያለው አንድ ይስጥ ያለው አምላክ ያለውን አንድ የሚወደው ልጁን ሰጠን።
. https://telegram.me/gracewins
#ውድ የሆነውን እጅግ ከፍ ያለ ለሚያምኑት ህይወት የሆነ ከመላዕክት አለም የተለየ ከሰርዲዮን ከመርግድን ከሰንፒር እንቁ ይልቅ የተወደደው ኢየሱስን እንዲያው ሰጠን። እንዲያው ያደረገልን እርሱ ብቻ ይመሰገን ዘንድ ነው። የተደረገው ሁሉ የተደረገው የሆነውንም ሁሉ የሆነው የእግዚአብሔር የፀጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ነው። ብቻውን የሰራልን ብቻውን ይከብር ዘንድ ነው።
.
https://telegram.me/gracewins
https://telegram.me/gracewins
አገልጋይ Dave khc
859 views09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ