Get Mystery Box with random crypto!

Grace Commission (የጸጋ ተልዕኮ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ gracecom — Grace Commission (የጸጋ ተልዕኮ) G
የቴሌግራም ቻናል አርማ gracecom — Grace Commission (የጸጋ ተልዕኮ)
የሰርጥ አድራሻ: @gracecom
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር እንዲታረቁ በክርስቶስ የሚለምን አገልግሎት ነው!!  (2ኛ ቆሮንቶስ 5፥20)
ለጥያቄዎ እና ለአስተያየትዎ፦
@Talkinggrace2023

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-04 05:54:01
እግዚአብሔርን የመምሰል ምስጢር _ ቀጣዩን ድንቅ ትምህርት ጊዜ ወስደው ይማሩ!. #የእግዚአብሔር #ጸጋ #ያሳድጋል!.
13 viewsBarnabas Zemene, edited  02:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 03:11:43
መዝሙር አትቀይር!

እግዚአብሔር ለዘላለም ይቅር እንዳለህ የማይሰማህ ከሆነ፣ በአንዳንድ ድካሞችህ ይቅርታውን የሚሰርዝብህ መስሎ ከታየህ፣ ቀድሞውኑ በማን ይቅር እንዳለህ አልገባህም! እግዚአብሔር በራስህ ብቃት ሳይሆን በክርስቶስ ይቅር እንዳለህ አስታውስ!.

ዘማሪው ዳዊት የእግዚአብሔርን ምሕረት አስቦ "ምሕረቱ ለዘላለም ነው" ብሎ ዘመረ። አንተስ? ከገባህ እንደዚህ ዘምር!. ካልገባህ ግን ዝም በል እንጂ መዝሙር አትቀይር!

"ምሕረቱ ለቀናት ነው! ምሕረቱ ለሳምንት ነው! ምሕረቱ ለወር ነው! ምሕረቱ ለዓመት ነው! ምሕረቱ እስከማጠፋ ነው!" እያልህ የራስህን መዝሙር አትድረስ!

እንደ ቃሉ ዘምር! ቃሉ ❝እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥❞ ይላል። (ዕብ.10:12) ስለዚህ ሥራው ተሠርቶ አብቅቷል! መዝሙርህ በክርስቶስ ከተሰራው እንጂ ከሥራህ አይነሳ!

ቃሉ ❝ኃጢአታቸውንና ዓመጻቸውን ደግሜ አላስብም ይላል።❞ ብሏል። (ዕብ.10:17)። "ደግሜ አላስብም" ይህ ለአብ ፊደል አይደለም!  በደላችንን ልጁ ላይ ከቆጠረ በኋላ ነው፤ "ደግሜ አላስብም" ያለው። ኃጢአታችን አንድ ጊዜ ኢየሱስ ላይ ስላሰበው እኛ ላይ ደግሞ አያስበውም።

ስለዚህ መዝሙርህ እንደ ቃሉ ይሁን። ስሜትህን ሳይሆን ቃሉን ዘምር!!

ኤፍሬም ተምትም
Grace Minister @
The #Way #Reformation #Ministry

ለሌሎች አካፍሉ፦
ቀጣዩን ሊንክ ለ10 ሰዎች በመላክ አገልግሉ!

#Grace #Commission
https://t.me/gracecom
https://t.me/gracecom
139 viewsBarnabas Zemene, 00:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 03:10:07
#የኃጢአት #ይቅርታ

መቼም በደል በሌለበት ስለ ይቅርታ ማሰብ አይቻልም። ስለ እርቅ በትክክል ለማወቅ ከፈለግን ስለ በደል እና ኃጢአት እንዲሁም ስለ መዘዛቸው ከመረዳት መጀመር የግድ ነው። መፅሐፍ ቅዱሳችን የኋላ ታሪካችንን ሲያወሳን "በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ።" በማለት ነው (ኤፌ 2:1-2)። ኃጢአታችን ከእግዚአብሔር ለይቶን እንደነበርም በዚሁ ክፍል ተነግሮናል። (ኤፌ 2:12)። ሮሜ 6:20 ላይም መፅሐፍ ቅዱሳችን "የኃጢአት ባሪያዎች ሳላችሁ ከፅድቅ ነፃ ነበራችሁ" እንዳለን እኛ ሰዎችን ኃጢአት ከእግዚአብሔር ለይቶ የራሱ አድርጎን ቆይቶአል።

ሆኖም እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ይቅር ብሎ የራሱ ሊያደርገን ወደደ። ኃጢአት ከእግዚአብሔር ለይቶ የራሱ እንዳደረገን እግዚአብሔርም ከኃጢአት ለይቶ የራሱ ሊያደርገን ወሰነ። በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ሥራም ሀሳቡን አሳካ።
የኢየሱስ የመስቀል ሞት እኛን ከበደል አርቆ ወደ አምላክ ለማቅረብ ተብሎ የፈሰሰ ደም ነው፤ ከኃጢአት ለይቶ የእግዚአብሔር ለማድረግ የተከፈለ ዋጋ ነው፤ ከአመፃ ጋር አጣልቶ ከፈጣሪ ጋር ለማስታረቅ የተሰጠ መስዋዕትነት ነው። (ኤፌ 2:12-13፣ ቆላ 1:14፣ ሮሜ 6:6፣11)።

በክርስቶስ ኢየሱስ የመስቀል ሥራ ላመናችሁ ለሁላችሁም የምስራች! ከኃጢአት ተለይታችሁ የእግዚአብሔር ሆናችኋል። ከአመፃ ጋር ተጣልታችሁ ከአምላክ ጋር ታርቃችኋል፤ ከበደል ርቃችሁ ወደ ፈጣሪ ቀርባችኋል።

ቢኒያም በርሄ
የ"ከበፊት እስከ ወደፊት" መጽሐፍ ፀሐፊ

#መጽሐፉን #ማንበብ #የምትፈልጉ፦ ኢማና መ/ቤት (ቦሌ)፣ ቤሪያ መ/ቤት (4ኪሎ) እና መሰረተ ክርስቶስ መ/ቤት ስታዲየም ዙሪያ

ለሌሎች አካፍሉ፦
ይህን ሊንክ ለ10 ሰዎች በመላክ አገልግሉ፦

#Grace #Commission
https://t.me/gracecom
126 viewsBarnabas Zemene, edited  00:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 08:41:20
#ከሳሼ_እና_ክሱ

እንዴት እንደሚወደኝ አየሁ የፍቅር ጥጉን
ሀጥያት ያላወቀውን ለኔ ሀጥያት ማድረጉን
ፅድቄ ነው ስል ኢየሱስ ሰርቶልኝ ነው ስራዬን
ፀጋው በእምነት አድኖኝ አውቄያለሁ ዋጋዬን
ውዱ ነኝ ለክርስቶስ የሚወደኝ ስስቱ
ጥልቅ ፍቅር ከ'ኔ ይዞት ስለኔ ነው መቀጣቱ
በመስቀል ላይ ተንጠልጥሎ ስለነፍሴ አልፏል ነፍሱ
ከ'ግሬ በታች ተጥሎልኝ ከሳሼ ወድቋል እንኳን ክሱ

እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው

#በቃ_ፍቅሩ_ስለ_ስሙ_እያስለፈለፈኝ ነው!!
#ለኢየሱስ_ሲሆን_መለፍለፍ_የሚለው_ቃል_ራሱ_ደስ_ይላል!!
#ቀላል_እለፈልፋለሁ!!

ሄኖክ አሸብር
ፀሐፊ እና አማካሪ

ለሌሎች አካፍሉ፦
ቀጣዩን ሊንክ ለ10 ሰዎች በመላክ አገልግሉ!

#Grace #Commission
https://t.me/gracecom
https://t.me/gracecom
195 viewsBarnabas Zemene, 05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 05:16:29
#የእናቴ ወይስ #የሠራተኛችን #ልጅ ነህ?

የእናቴ ልጅ ወንድሜ ነህ ወይስ የሠራተኛችን ልጅ? እኔ የወለደችኝ ሣራ ናት። እርሷም ጨዋይቱ፣ ላይኛይቱ እና ነፃይቱ የተባለችው ናት። እኔ ልክ እንደ ይስሐቅ የተስፋ ቃል ልጅ ነኝ። ሕጋዊ ልጅ ነኝ። በተአምራት የተወለድኩ ልጅ ነኝ።

አንተስ? የእናቴ ወይስ የሠራተኛችን ልጅ ነህ? ሠራተኛችን እኛ ቤት የገባችው ተቀጥራ እንጂ አግብታ አይደለም። ለሥራ ገብታ ልጅ የወለደችው አጋር ሲና ምድረ በዳን (የሙሴን ሕግ) ትወክላለች። ልጅዋ እስማኤል ደግሞ  የሥራ እና የሰው ጥረት  ምሳሌ ነው።

ወዳጄ አንተ የነፃይቱ ልጅ ነህ? ወይስ የባሪያይቱ ልጅ ነህ? አንተ እንደ መንፈስ ፈቃድ ነው የተወለድከው ወይስ እንደ ሥጋ ፈቃድ?

ከባሪያይቱ የተወለደ በቤታችን ርስት የለውም። ቀድሞ ቢወለድም ወራሽ አይሆንም።

በጸጋ አምነው የዳኑ ሁሉ የጨዋይቱ የሣራ ልጆች ናቸው!!

(ገላትያ 4፥21_31 ተመልከት)


ዳዊት ጥላሁን አበበ
ሶቴሪያ ባይብል ስኩል ፕሬዚዳንት
ሔሴድ ኢን. ቤተክርስቲያን ዋና መጋቢ

ለሌሎች አካፍሉ፦
ይህን ሊንክ ለ10 ሰዎች በመላክ አገልግሉ!

#Grace #Commission
https://t.me/gracecom
https://t.me/gracecom
195 viewsBarnabas Zemene, 02:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 04:05:40

264 viewsBarnabas Zemene, 01:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 00:03:31
#ጸጋ #ለእኔ

“ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአል” (ቲቶ 2፥11) እንደሚል ቃሉ የተገለጠው ጸጋ ካዳናቸው ሰዎች አንዱ ነኝ!

“ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን" እንዳለ ጸጋው እግዚአብሔር የማይከብርበትን አኗኗር ካስጣላቸው፣ ከኃጢአት እስራት ከፈታቸው ሰዎች ዋናው ነኝ!

"ይህም ጸጋ ... የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤” (ቲቶ 2፥12-13) እንደሚል ቃሉ እንዲህ እየሆነላቸው ካሉ የጸጋ ተማሪዎች አንዱ ነኝ!

“ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ” (1ኛ ቆሮንቶስ 15፥10) እንዳለ ጳውሎስ አገልጋይነትን የተቀበልኩት በጸጋ ነው! በተገለጠው ጸጋ ለብዙዎች መትረፍ እና ማረፍ ምክንያት ከሆኑት አንዱ ነኝ!

ጥቅምት 2011 ዓም  "ያንተ መልእክት ጸጋ ነው" የሚል ምሪትን ከመንፈስ ቅዱስ ተቀብያለሁ!. ጸጋ የምኖርበት አቅም ብቻ ሳይሆን የምኖርለት መልእክቴ እንደሆነ የተረዳሁት ጸጋን እንዳሁኑ ባልተረዳሁበት ሁኔታ ነበረ!

ጸጋ መልእክቴ እንደሆነ ከተረዳሁበት ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ መንገዶች ከሁሉም የጸጋ አስተማሪዎች ተምሬያለሁ!

የጸጋን መልእክት በጸጋ ላለፉት 2 ዓመታት ብዙዎች ጋር አድርሻለሁ! በጸጋ ከመዳን ጀምሮ ጸጋን በመረዳት ወደ ማካፈል ያደገ ትውልድ አለኝ!

ጥቂት ከመባል የሚያልፉ አገልጋዮች የጸጋን ቃል ተቀብለው አገልግሎታቸውን እንዲያስተካክሉ ምክንያት ሆኛለሁ!

በቀሪው ዘመኔም በጸጋ እኖራለሁ! ለጸጋ እኖራለሁ!

በጸጋ የተጠቀማችሁ ቀጣዩን ሊንክ በመጠቀም ሌሎችን ጋብዙ!

በርናባስ ዘመነ
#Grace #Commission

https://t.me/gracecom
264 viewsBarnabas Zemene, edited  21:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ