Get Mystery Box with random crypto!

💕 ፍቅርን በቃላት 💕

የቴሌግራም ቻናል አርማ fkrn_be_kalat — 💕 ፍቅርን በቃላት 💕 ፍ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fkrn_be_kalat — 💕 ፍቅርን በቃላት 💕
የሰርጥ አድራሻ: @fkrn_be_kalat
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.03K
የሰርጥ መግለጫ

💝 ፍቅርን በቃላት 💝
♥️ይህ ነው ለእኔ ፍቅር💟 ማለት፤
➣ ያለምላሽ ወዶ መገኘት፤
➣ በንፁህ ልብ ጠልቆ መዋኘት፤
➣ ይህ ነው ለእኔ ፍቅር ማለት💟
💞የፍቅር ቃላት ሁሌም አሸናፊ ናቸው💞
For any promotion ➢ @Naolviva ✌
For spam 👇
@fkrn_be_kalat_bot

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-25 21:19:00 ፍቅርን በቃላት

እውነተኛ__ታሪክ
============
ከእለታት አንድ ቀን ልጅና አባት በፍቅር፣በደስታ በተሞላበት ቤት አብረው ይኖራሉ። ፍቅራቸው መቼም ከሌሎች የተለየ ነበር ምክንያቱም አንዱ ካንዳቸው ተነጥለው መኖር የሚችሉ አይመስሉም ። ከዕለታት አንድ ቀን ልጅ ትታመማለች አባት ልጁን ይዞ ሀኪም ቤት ሄደ።

ሀኪም መፍትሄ አልሰጣትም። ልጅት አሁንም አልተሻላትም
ልጁን ይዞ ወደ ፀበል ወሰዳት መፍትሄ የለም የሳይኮ ሎጂ ባለሙያ አማከራ፣ያልሄደበት የለም በቃ,,,,,,,,,,,
ልጅት ግን ልትተርፍ አልቻለችም ልጁ ሞተች ። አባት አንጀቱ ተቆረጠ፣ የሚይዘው ፣ የሚጨብጠው አጣ ተስፋ ቆርጦ ቤት ዘግቶ እራሱን በሀዘን መቅጣት ጀመር። ሌት ተቀን ማልቀስ ማልቀስ በእንባ ሲታጠብ ይውላል፣ያድራል።
የሰፈሩ ሰዎች ሊያፅናኑት፣ ሊያበርታቱ ቢሞክሩም እሺ አላለም ባሰበት ሀዘኑ ።

አንድ ቀን በህልሙ ሰማይ ላይ ያሉ ህፃናት ልጆች ውድድር ይቀርባሉ ለሁሉም ሻማ፣ ጧፍ ተሰጡ እና አሁን ሁላችሁም አብሩት ተባሉ ሁሉም አበሩት። ነገር ግን የሱ ልጅ ሻማው አልበራላትም አለ ብትለው፣ ብትለው ,,,, ልጄ የሁሉም እየበራ ያንች ይጠፋል ለምንድን ነው ብሎ አባት ጠየቃት?
ልጅም አባዬ የኔ የማይበራው እኮ አንተ ሁልጊዜ ስለምታለቅስ እንባህ ነው የሚያጠፋብኝ አለችው።
አባት ከዛ ቀን ጀምሮ ከሀዘን ወጣ፣ ከማህበርሰቡ ጋር በደስታ፣በፍቅር ተቀላቀለ።

ስለዚህ ብዙ ማዘን እኛን ብቻ ሳይሆን ፣ የሞተውንም ሰው ነፍሱን እንረብሸዋለን ማለት ነው ። በሀዘን ላይ ብዙ መቆየት ተገቢ አይደለም ። ፀሎት በማድረግ ለተለየን ሰው ምህረት መጠየቅ ነው ትልቁ ነገር እንጂ የእኛ ሀዘን ማብዛት ምንም እሚጨምረው ነገር የለም።

ይሄ ምክር የሚያስፈልጋቸው ብዙ አሉና ሼር ያድርጉት
┄┉┉✽‌»‌ ✿ »‌✽‌┉┉┄



አሁኑኑ ሼር አድርጉ

@fkrn_be_kalat
ፍቅርን በቃላት
........... ••● ●•........ ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌ ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌
885 viewsከማን ገጥመሽ ይሆን ✧ŊąøŁą ✧, 18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 17:15:59 ‹‹ይቅር ስላልሺኝ በጣም አመሰግናለው..እርግጠኛ ሁኚ በቀሪው ህይወታችን እክስሻለው….ምርጥ ባል ነው የምሆንልሽ››
‹‹ምርጥ ባል እንድትሆንልኝ አይደለም የምፈልገው ምርጥ ልጅ እንድትሆንለኝ ነው የምፈልገው.እናትህ መሆን ነው የምፈልገው.የእንጀራ እናትህ››
‹‹እያሾፍሽብኝ ነው እንዴ?›
‹‹አይ እውነቴን ነው …ታውቃለህ በጣም የማፈቅረውን ሰው በሞት ተነጥቄያለው.እሱን መመለስ አልችልም…ግን ደግሞ በህይወት ያሉት አባትህን አፈቅራቸዋለው ….እሳቸውን ማግባት ነው የምፈልገው››
‹‹እየተበቀልሺኝ ነው?››
‹‹እሱን እንደፈለክ ተርጉመው..ግን ይቅር ተባብለናል ያልነው የእውነታ ከልባችን ከሆነ ስለበቀል ማውራት ከእኛ የሚጠበቅ አይደለም››
‹‹እና አባትህን ላግባ ማለት ሌላ ምን ትርጉም ልስጠው እችላለው?ለመሆኑ እኔ እሺ ብልሽ አባዬ በዚህ እብድ ሀሳብሽ የሚስማማ ይመስልሻል.?ነው ወይስ እናቴን እንደምትመስይ ደጋግሞ ሲነግርሽ ተምታታብሽ››
‹‹አንተ እንዲስማማ ታደርገዋለህ ››
‹‹ጭራሽ እኔው..?››
‹አዎ አንተው.አባትህን ትሄድና እኔና አንተ ያለንን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ በስምምነት እንዳቋረጥን ..እና እስከአሁንም ቃል ከመገባባት በዘለለ ምንም የፈፀምነው ፃታዊ ትስስር እንደሌላ ታስረዳቸዋለህ.፡፡በተጨማሪም አኔ እሳቸውን ማግባት እንደምፈልግ ትነግራቸዋለህ…..እናም ለአንተ ሲሉ እንደያደርጉት እሺ እስኪሉህ ድረስ እግራቸው ስር ወድቀህም ቢሆን ትማፀናቸዋለህ፡
‹‹ማይሆነውን?››
ስልኳን አወጣች…ጎረጎረችና የሆነ ነገር ላከችለት
‹‹ምርጫ የለህም…የላኩልህን ነገር እየው…ይሄ እኔ ጋር ብቻ ሳይሆን ጠበቃዬ ጋርና በጣም የማምናቸው ሌሎቸ ሰዎች ጋር በተጠበቀ የሚስጥር እቃ ተቀምጧል..እኔ አንድ ነገር ብሆን ወይም አንተ በዚህ ሀሳቤ የማትስማማ ከሆነ ወዲያውኑ ፍርድ ቤት ይቀርባል….ከዛ የሚሆነውን መገመት ቀላል ነው፡፡›
ተስገብግቦ ሞባይሉን አወጣና የላከችለትን ፎልደር ከፈተው….ወዲያው ደንግጦ ዘጋው..መልሶ ከፈተው..ወደ .ጆሮው ለጥፎ አዳመጠው.ይህ ቀጥታ ለእድሜ ልክ ዘብጥያ የሚያስወረውረው መረጃ ነው፡፡
‹‹ከየት አገኘሽው?›
‹‹እሱ ምን ደያደርግልሀል…አንተም ብቻ አይደለህም እኮ እስማርት…››
‹‹አሁን መሄዴ ነው››
‹‹አንድ ሳምንት ሰጥቼሀለው››
ምንም አልመለሰላትም በተቀመጠችበት ጥሏት አንገቱን እንዳቀረቀረ በተሰበረ ቅስም….ሆቴሉን ለቆ ወጣ፡፡
.
.
.
ተፈፀመ


የመወያያ ግሩፑን ይቀላቀሉን
@ethio_lifes_group

https://t.me/+Bpbeik0Cf-45ZWU0
╔═══❖• •❖═══╗
@fkrn_be_kalat
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@fkrn_be_kalat_bot ❥❥________⚘_______❥❥
1.5K viewsከማን ገጥመሽ ይሆን ✧ŊąøŁą ✧, 14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 17:15:25 //
6 ሰዓት ሁለቱም በተቃጠሩት ሆቴል ፊት ለፊት ተቀምጠዎል።እሷ አሁንም ጥቁር በጥቁር እንደለበሰች ነው።ቢሆንም ከሰሞኑ ጉስቁልናዎ ቀስ በቀስ እያገገመች መሆኑን ጠቅላላ ሁኔታዎን አይቶ መገመት አይከብድም...እሳቸው ነጭ በነጭ የባህል ልብስ ለብሰው በቀኝ እጃቸው ነጭ ጭራ ይዘው በሌላ እጃቸው የተንዠረገገ ነጭ ፂማቸውን እያፍተለተሉ ላያቸው የሆነ የመላዕክትን ገፀ_ባህሪ ለመጫወት ዝግጅ የሆነ ባለግርማ ሞገስ ተዎናይ ነው የሚመስሉት።
"ናፍቀሺኝ ነበር...ማለቴ በጣም"
"እኔ ደግሞ ሳዬት ነው ናፍቀውኝ እንደነበር ያወቅኩት"
"ያንን በመስማቴ ደስ ብሎኛል"
"ደግሞም አምሮቦታል "አስባበት ሳይሆን ምላሶን አዳልጧት የተናገረችው ነው።
"ለአንቺ ያለኝን ክብር እንዲያስረዳኝ ነው እንዲህ መዘነጤ ...ለመሆኑ አንቺስ እንዴት ነሽ?*

‹‹ሰላም ለመሆን እየመኮርኩ ነው..ግን ደግሞ በጣም እየናፈቀኝ ነው።"

"አውቃለው… ንግስቴ ጥላኝ ከሄደች ብኃላ እኔሞ በጣም ትናፍቀኝ ነበር።አዎ ናፍቆቱ ስቃይ አለው...ቢሆንም እንድረሳት ስለማልፈልግ ህመሙን እችለዎለው።እንደውም ከቆይታ ብኃላ በናፍቆቱ ምክንያት ልብሽ ላይ የሚሰማሽ ስቃይ ሱስ ይሆንብሻል።..ነገሩ እኔ ካንቺ በተሻለ እድለኛ ነበርኩ››

"እንዴት ጋሼ?"
‹‹ብቻዬን ጥላኝ አልነበረም የሄደችው...ሁለት ልጇቾን ጥላልኝ ነበር የሄደችው ..እነሱም አንድ መፅናኛዎቼ ነበሩ
"ጋሼ"
"አቤት ንግስቴ"
‹‹ለአባቴም ገና ያልነገርኩትን አንድ ዜና ልንገሮት"

"ልስመዎ"

ቀኝ እጇን አነሳችና ሆዶ ላይ አስቀመጠች..አሻሸችው።አይናቸው ተበለጠጠ..‹‹.ምን እያልሺኝ ነው..?
"አዎ ለእኔም ትቶልኝ ነው የሄደው..አርግዤያለው"
‹‹እኔ አላምንም..››ከመቀመጫቸው ተነሱ .ጠረጳዛውን ዞሩና ወደእሷ በመቅረብ አገላብጠው ሳሟት…እሷ እርሷ ማርገዞን የሰማች ቀን በእሳቸው መጠን የፈነጠዘች መሆኗን አታስታውስም፡፡.ወደመቀመጫቸው ተመልሰው ተቀመጡና፡፡
‹‹..እና እግዚያብሄር በፀጋው ዳብሶሻል ማለት ነው?››
‹‹እንግዲህ መሆኑ ነዋ››
‹‹ነው እንጂ…በጣም እድለኛ ነሽ.፡፡በይ አሁን ወደቀልብሽ ተመለሺ፤ የውስጥሽንም ሀዘን ለመቆጣጠር ሞክሪ ፡፡.በማህፀንሽ ለተሸከምሽው በረከት ስትይ…በዛ ላይ የእሱም መንፈስ በቅርብ ሆኖ ያይሻል
‹‹እውነቷትን ነው››
‹‹አዎ ጨክነው ጥለውንማ አይሄዱም…..ልክ እንደከዚህ ቀደሙ ተመልሰው እስኪመጡ ድረስ መንፈሳቸው ይጎበኛናል፡፡
‹‹ለሶስተኛ ጊዜ ተመልሶ የሚመጣ ይስሎታል?፡፡››
‹‹ለሁለተኛ ጊዜ ተመልሶ መምጣቱን አምነሻል ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ አርሶ ስላሉኝ ነው…እርሶን ደግሞ አምኖታለው››
‹‹እንግዲያው አዎ አንቺና እሱ የተመቻቸ ዘመን በተመቻቸ ሁኔታ ላይ ተፈጥራችሁ በስርእት መጋባትና በፍቅር አብሮ መኖረ እስክትችሉ ድረስ በተለያየ ትውልድ ደጋግማችሁ ትፈጠራላችሁ...ይህ ነው የእኔ እምነት››
‹‹እኔም እንደዛ ማመን እፈልጋለው›አለች…እውነቷን በውስጧ የሚሰማትን ነው የተናገረችው..አንድ በጣም በነፍስ እንጥፍጣፊ ጭምር የሚያፈቅሩትን ሰው እስከወዲያኛው ለዘለለሙ ነው ያጣውት ቡሎ ማሰብ በጣም ተስፋ አስቆራጭና ጨለማ ሀሳብ ነው..በሆነ ተአምር ዳግም ስጋ ለብሶ በዚህ ምድር ይከሰታል እኔም እንደዛው አደርጋለው...እናም መልሶ በእይታው ለመደንገጥ.. በአይኑ ጥቅሻ ለመቅለጥ..ከዛም በሙቀቱ ለመቃተት እና በፍቅሩ ለመስከር እድል ይኖረኛል ብሎ ማለም ..እጅግ በውስጣችን ብርሀንን የሚረጭ ፋንታሲ ነው፡፡እና እንደዛ ለማመን መንገድ ላይ መሆኗ ተመችቷታል…ምን አልባት ከእሳቸው በላይ የዚህ እምነት ዋና አቀንቃኝ እንደምትሆን ከአሁኑ እየታወቃት ነው፡፡
‹‹ንግስቴ››
‹‹አቤት ጋሼ››
‹‹የዚህ ልጅ የጡት አባት ወይም የክርስትና አባት መሆን እፈልጋለው..ቀሪ ዘመኔን ልንከባከበው እፈልጋለው፡፡የእሷን ልጅ ተንከባክቤ እንዳሳደኩ ሁሉ የአንቺን ልጅ ድንቅ ድንቅ ተረቶች እየነገርኩ ጭንቅላቱን በፍቅር እያሻሸው ማሳደግ እፈልጋለው፡፡አውቃለው ባል ታገቢያለሽ..ባልሽ እንደልጁ ሊንከባከው ይችላል….ብዙ ሞግዚቶች ልትቀጥሪለትና እነሱ ሊንከባከቡት ይችላሉ፡፡.ግን እመኚኝ የእኔን ያህል ልምድ አይኖራቸውም.፡፡በዛ ላይ እንደዛ ማድረጌ እድሜዬን ያረዝምልኛል… አዎ ለራሴ ብዬ ነው››
‹‹ጋሼ…ወንድ ነው እንዴ? ››
‹‹ማ ?››
‹‹ልጁ..በሆዴ ያለው?››
‹‹እኔ እንጃ …ወንድም ሆነ ሴት ምን ለውጥ አለው…ዝም ብዬ አፌ ላይ ለምዶብኝ ነው››
‹‹ገባኝ››
‹‹እና ያልኩሽን ምን አልሺኝ..የጡት አባት ወይስ የክርስትና አባት..የትኛው?››
‹‹አይ እኔ የልጄ ብቻ ሳይሆን የሁለታችንም ጠባቂ አባት እንዲሆኑ ነው የምፈልገው…የእኔም የልጄም.››
‹አግኝቼ ነው..ሄኖክን ልተገቢው ነው እንዴ?ያው እሱን ካገበሽ ለሚወለደው ልጅ አያት ላንቺ ደግሞ አማች ስለምሆን ያው ጠባቂያችሁ ሆንኩ ማለት ነው››
ኮስተር አለች‹አይ በፍፅም እሱን አላገባም››
‹‹ታዲያ እንዴት ለሁለታችሁም ጠባቂ መሆን እችላለው?››ግራ በመጋባት ጠየቋት፡፡
‹‹ምነው እርሶ አያገቡኝም?...ማለቴ ..በፈለግሺው ጊዜ መሸሸጊያሽ እሆናላሁ ብለውኝ አልነበር ?››
‹‹አዎ ብዬሻለው ...ግን እንዴት ነው የሚሆነው?ግራ ገብቶኝ እኮ ነው››
‹‹ልክ ቅዱስ ዮሴፍ ለድንግል ማርያም እንደሆነት አይነት….ልክ እየሱስንም እናቲቱንም በፍጽም ንፅህና እና ቅንነት እንደጠበቀው አይነት…››
‹‹ተአምረኛ ልጅ ነሽ…ከቤተሰቦችሽና ከማህበረሰቡ የሚደርስብሽኝ ጫና የሚሸከም ጫንቃ ካለሽ እኔ ከዚህ በፊት እንደነገርኩሽ ሁሌም ያንቺው ነኝ፡፡›አሏት በፈግታ ተሞልተው፡፡
‹‹እንግዲያው እኔ ቤት ነው የምንኖረው…ከፈለጉ ሰርግ መደገስ እንችላለን፡፡››
‹ሁሉም አንቺ እንደፈለግሽ ይሆናል .. እኔ ካንቺ ጎን ከመኖር ውጭ ምንም ሌላ ፍላጎት የለኝም…የእኔ አንድ ጭንቀት በዚህ ጉዳይ ልጄን ማሳመን እንዴት እንደምችል ብቻ ነው….አባት የልጁን ፍቅረኛ ነጥቆ አገባ ሲባል ለሰሚው ከባድ ነው…›
‹‹ጋሼ የሄኖክነ ነገር ምንም አይጨነቁ ..የማናግረው እኔ ነኝ….››
‹‹እንደዘ ይሻላል?››
‹አዎ .ስለእሱ ምንም አይጨነቁ….እርሷን ሳይቀየም ፍቃደኛ ይሆናል፡፡››
‹‹እሺ እንዳልሽ….ግን ከዚህ ቡኃላም ጋሼ እንዳልሺኝ ነው የምትቀጥይው›
ፈገግ አለች…‹‹እስኪ በሂደት እንዴት ማስተካከል እንደምንችል እናስብበታለን፡፡››
‹‹ልቀልድ ብዬ ነው እንደፈለግሽ››
///
አሁን ልክ ከቀኑ 11 ሆኗል ፡፡እናም ሲፈን ሶስተኛው ቀጠሮዋ ላይ ተገኝታለች.፡፡ሄኖክም ከፊት ለፊቷ ተቀምጧል፡፡ይሄኛወ ቀጠሮዋ ከአጀማመሩም ውጥረት ያለበት ነው፡፡
‹‹ሲፈን እንድንገናኝ ስለፈቀድሽ በጣም ደስ ብልኛል››
‹‹የግድ ስለሆነ ነው የተገናኘነው››መለሰችለት፡፡
‹አዎ…የግድ ነው…በጣም ብዙ ጠብቄያለው…በመራራቃችን በመከከላችን ብዙ ብዙ ችግሮች ተፈጥረዋል…አሁን ግን ያን ሁሉ ከኃላችን ጥለን ቁስለታችንን በማከም ወደፊት መቀጠል ነው ያለብን፡፡››አለ ምን ትመልስልኝ ይሆን በመሚል ፍራቻ ፈራ ተባ እያለ..
‹‹ትክክል ብለሀል…አሁን በትክክል አድምጠኝ ፤እኔ ላለፈው ጥፋትህ ማለቴ በእኔ ላይ ለሰረሀው በደል ሁሉ ይቅር ብዬሀለው .አንተም ያስቀየምኩህ ነገር ካለ ይቅር እንድትለኝ እፈልጋለው፡፡››
1.0K viewsከማን ገጥመሽ ይሆን ✧ŊąøŁą ✧, 14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 17:15:07 ነፍስ ስታፈቅር

ምዕራፍ - 24

ደራሲ- ዘሪሁን ገመቹ
.
.
.
የቢላል ህይወት ካለፈ 15ቀን ቢያልፈውም ሲፈን ግን ዛሬም ወደቤቷ አልተመለሠችም።ወላጆቾ ቤት እዛው ክፍሏ ነው ያለችው።ይህ የሆነው ከደረሰበት የሀዘን ስብራት አባቷ እንዲያፅናናት ወይም እናቷ ጉያቸው ሸጉጣ ተስፋ እንዲሰጧት ፈልጋ አይደለም።እዛ ቤት የመሸገችበት ብቸኛው ምክንያት ክፍሏን ፈልጋ ነው ።እዛች ክፍል ውስጥ ቢላል ከ20ቀን በላይ ኖሯል...በሰፊው አልጋ ላይ ከዳር እስከዳር ተንከባሎበታል..እያንዳንድን የክፍል ወለል እየደጋገመ ረግጦታል ፤በሻወር ቤቱ ደጋግሞ ተጠቅሞል....የጠጣባቸው ብርጭቆዎች፤ የተመገበባቸው ሳሀኖች ፤እዛ ክፍል ይገኛሉ።እያንዳንድንን ቢጃማዎን ፤ሠፋፊ ቀሚሶቾን :ቲሸርቶቾን እየቀያየረ ለብሶቸዎል..።አሁንም ሙሉ ክፍሉ..እጅ ያረፈባቸው እቃዎች በጠቅላላ የእሱን ጠረንና ትዝታ አዝለዎል..እና የእሷ እዛ ክፍል በራሷ ላይ ጠርቅማ ስትተክዝና ስታልም መዎል ምክንያቱ ይሄ ነው።

ይሁን እንጂ ጉዳዩ ቤተሠቦቾን በተለይ አባትዬውን ክፍኛ አሳስቧቸዎል።እና ዛሬ ሊያናግሯት ወስነው ክፍሎ ድረስ መጥተዎል።

"ልጄ...አይበቃም...እስከመቼ እራስሽ ላይ ዘግተሽ?"
‹‹አባ አንድ ክፍል ውስጥ ታፍኖ መቀመጥን አንተ እኮ ነህ ያስጀመርከኝ..."
"ለአንቺው አስቤ እኮ ነበር ...ይገድላታል ብሎ ሄኖክ ሲያስፈራራኝ ምን ማድረግ ነበረብኝ...?"
"ቢሆንም የእኔንም ፍላጎት ከግምት ልታስገባ ይገባ ነበረ....ከማታውቀው ሰው ምክር ከመቀበል ይልቅ እኔ ልጅህን ብትማከር ይሻል ነበረ"

‹‹"እሱስ እውነትሽን ነው ...እንደዛ አድርጌ እራሱ መች አዳንኩሽ...እንደው ልጅ እግዚያብሄር ይባርከውና እንደተባለው አድርጎ ቢሆን ኖሮ ምን ይውጠኝ ነበር...?እኔ ያቆምኮቸውን ወጠምሾች አልፎ ክፍልሽ ገብቷል..ከመግባትም ለቀናት ኖሯል....እና እዛው በገዛ ክፍልሽ አንቆሽ ቢሆን ኖሮ...አረ በስመአብ.."ግሽግሽ አሉ፡፡

" ....ግን አላደረገውም...በጣም ስለሚያፈቅረኝ ምን አልባት በበሽታው ተፅዕኖ አንድ ቀን እንዳይገድለኝ በመፍራት ብቻ ቀድሞ እራሱን አጠፋ...ከራሱ ሊጠብቀኝ እራሱን ገደለ ፤ይሄንን ሰው ነበር ሁለታችሁም ስታሳድዱት የከረማችሁት››

"አዎ ልጄ ትክክል ነሽ አጥፍተናለ..ብቻ ነፋሱ በአፀደ ገነት ትረፋ.."

ረጂም ዝምታ.....
"ልጄ"
"አቤት አባዬ"
"አንድ ሌላ ነገር ልነግርሽ እፈልጋለው..."አሉና እጃቸውን ወደጃኬት ኪሳቸው በመስደድ አንድ ወረቀት አወጡ....
"ይሄ ያንቺን ጋብቻ በተመለከተ ተዋውለን የነበረ ውል ነው...ቀነ ገደብ ሊገባደድ አንድ ወር ብቻ ነው የቀረው.."

ፊቷን በንዴት አጨማደደች"አባዬ አሁን ስለዚህ ጉዳይ ለማውራት አቅሙ የለኝም"

"አውቃለው ልጄ "ብለው ሁለት ቦታ ከዛም አጥፈው አራት ቦታ ቀዳደዱና ወለሉ ላይ በተኑት...ሲፈን በጣም ደነገጠች
"እንዴ አባዬ!! ምን እየሰራህ ነው?"

"ልጄ ሀሳቤን ሁሉ ሰርዤዎለው...በፈለግሽ ሰዓት የፈለግሽውን ማግባት ካለበለዚያም አለማግባት ትቺያለሽ...እኔ ልጄ ደስተኛና ጤነኛ ብቻ እንድትሆን ነው የምፈልገው....ካንቺ የሚበልጥብኝ ምንም ነገር የለም"አሉና ከመቀመጫቸው በመነሳት ግንባሯን በመሳም ወደ ውጭ መራመድ ጀመሩ።

"አባዬ..በጣም ነው የማመሠግነው..ደግሞ ቃል ገባልሀለው…በጣም በቅርብ አስደሳች ዜና አሰማሀለው"አለች ሆዷን በቀኝ እጇ በስሱ እየዳበሰች።
"ይሁን ልጄ..ይሁን...በእኔ በኩል ምንም ብታደርጊ ቅሬታ የለኝም ...ለሁሉም ነገር ከልቤ መርቄሻለው... ደህና ሁኚልኝ..."ወጥተው ሄድ።
///
በማግስቱ…..
በጥዎት ነው ከእንቅልፏ የተነሳችው፡፡ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ ቀለል ብሏታል።አዎ በሀዘን የጎበጠ ትከሻዎ ቀና ማለት ፤የደፈረሱ ዓይኗቾ መጥራት፤ የተሠነጣጠቀ ልቧ ክፍተቱን ማጥበብ ጀምሮል ...ለዚህ ደግሞ የሄኖክ አባት ድርሻ ቀላል አልነበረም....ቢላል ከሞተ ብኃላ በራሷ ፍላጎት ስልክ አንስታ በመደወል የምታዋራቸው ብቸኛ ሰው ናቸው።እና በደወለችላቸው ጊዜ ሁሉ ከልስልስ አንደበታቸው እየሾለኩ በጆሮዎ የሚሰርጉ የምክር እና የማፅናናት ቃላት በትክክል ልቧ ላይ እያረፉ ሲቀልጡና ከሰውነቷ ሲዎሀድ ይታወቃት ነበር...በዛ ላይ በየሰዓቱ ልዩነት በሚሴጅ የሚልኩላት አጫጭር መልዕክቶች ለተሠበረ መንፈሶ መታሻ ቅባቶች ሆነውላታል።

ዛሬ ግን ከእሷቸው ጋር የምሳ ቀጠሮ አላቸው።ከሁለት ወር ብኃላ ነው በአካል የሚገናኙት።ከዛ በፊት ግን ቀርስ ላይ ከፕሮፌሰሯ ጋር ለመገናኘት ወደ ቤቷ ትሄዳለች..ስለልጅ ልጇ ማውራት ፈልጋለች.በዛ ላይ አራት ሰዓት አብረው ሀኪም ቤት ይሄዳሉ የፅንሱን ጤንነት ለማወቅ.፡፡..የዛሬዎ ቀጠሮ በዚህ አያበቃም 11ሰዓት ደግሞ ከሄኖክ ጋር ትገናኛለች።ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ፊት ለፊት አግኝታው ስለወደፊታቸው እልባት ለመስጠት ስለፈለገች ነው ላግኝህ ያለችው፡፡እሱም በደስታ እየፈነጠዘ ነበር ቀጠሮውን የተቀበለው፡፡

ብቻ ዛሬ ህይወቷን አዲስ አቅጣጫ የምታሲዝበት ቀን ነው።ለዚህ ደግሞ በዙሪያዋ በአውንታም ሆነ በአሉታ ተፅዕኖ ያላቸውን ሰዎች የምታናግረውን አናግራ የምታማከረውን አማክራ የመጨረሻ የመፍሰሻ አቅጣጫዎን ትወስናለች።
///
ወደኘሮፌሰሯ ቤት እየሄደች ሳለ ቤቷ ጋር ስትደርስ መኪናዋን አቆመችና ክላክሱን አንጫረረች…ተዘራ በራፉን ከፈተና ዱላውን እየወዛወዘ ወደእሷ ቀረበ…

"እንዴ እትይ ..እንደው ለመሆኑ ሰላም ነሽ.?.ስልኪቱን ብደውልም እኮ አታነሺም››
‹‹ምነው ችግር ነበረ እንዴ?››አለቸው በመስኮት አንገቷን አውጥታ እጇን ወደእሱ በመሰንዘር እየጨበጠችው፡፡
‹‹ኸረ እዚስ ሰላም ነው...ግን እትይ የአንቺ ነገር በጣም አሳስቦኝ ነው?"
‹‹እኔ ሰላም ነኝ...ከሳምንት ብኃላ ሙሉ በሙሉ ወደቤቴ እመለሳለው"
"ውይ እትዬ እባክሽ ተመለሽ...እባክሽ...መሽቶ ከልነጋ አለኝ እኮ...እንደው እትዬ አትታዘቢኝና በራፍ ከፍቼልሽ ስትገቢና ስትወጪ የምምገው ሽቶሽ እራሱ ናፈቀኝ ልሞት ነው››...ፈገግ አለች"ምን አለ ሰው ሁሉ እንደአንተ የዎህ ቢሆን? አለች በውስጧ
‹‹ደሞዝ ገብቶልሀል አይደል?"
‹‹አይ እትዬ ...አዎ ገብቶልኛል...አንቺ ጋር እየሠሩ የብር ችግር የት አለ..?.ብቻ አንቺ ሀዘኑን በልክ አድርገሽ ..ቃል እንደገባሽው ወደቤትሽ ቶሎ ተመለሺ"
‹‹እሺ ..አሁን ቸው..."መኪናዎን አስነስታ ሄደች።
///
ፕሮፌሰር ቤት ስትደርስ 3 ሰዓት ሆኖ ነበር።እንደምትመጣ ስለሚታወቅ ጠረጰዛው በምግብ ተሞልቶ ነበር የጠበቃት።አቀባበላቸው ደማቅ፤ መስተንግዶቸው ልብ ሚያሞቅ ፤እንክብካቤያቸው ልክ እንደንግስት ነበር.፡፡
.ከቁርስ ቡኃላ ሁለቱም ሳይነጋገሩ ተያይዘው ቢላል ክፍል በመግባት ዕቃዎቹንና ስዕሎቹን እያዩና እዳበሱ ሲያለቅሱ እና እርስ በርስ ሲፃናኑ አረፈዱ.፡፡በመጨረሻም አንድ የተቀደሰ ሀሳብ በሁለቱም ተከሰተላቸው .በእምሮ ህመምተኞች ላይ የሚሰራ ፋውንዴሽን በስሙ ለማቋቋምና በዛ ፋውንዴሽንም ስራዎቹን ቋሚ ስፍራ እንዲያገኙ ለማድረግ አብረው ሊሰረሩና ሙሉውን ወጪ የሲፈን ካማፓኒ ሊሸፍን ተስማሙ፡፡በዚህም ሁለቱ ከብዙ የሀዘን ቀናት ቡኃላ ደስ ተሰኙ፡፡.አምስት ሰዓት ሲሆን አብረው ሲፈን ለፅንሱ ክትትል ወደምታደርበት የግል ሆስፒታል ሄዱ፤
887 viewsከማን ገጥመሽ ይሆን ✧ŊąøŁą ✧, 14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 17:14:47 ..ልጄ ፍፀም ልዩ ሰው ሆኖ ነበር የመጣው.ያው ታውቃለህ የእምሮ በሽተኛ ስለሆነ ሁኔታው ሁሉ ወሰድ መለስ ነበር የሚያደርገው...በዛን ቀን ግን እንደዛ አልነበረም….መልኩ ጥርት ያለ …አለባበሱ ጠርት ያለ…ንግግሩ ጥርት ያለ ነበር…፡፡ተደሰትኩ፤ተስፋ አደረኩ፤ጓጓው…በውስጤ ለአንድ ሺ ጊዜ ደጋግሜ ፈጣሪን አመሰገንኩ…ልጄ ሙሉ በሙሉ እየዳነልኝ ነው አልኩ….በደስታ እየተጫወተንና እየተቃለድን ቁርስ በላን..እማዬ ጸጉርሽ ተንጨብርሯል አለና ፀጉሬን ፈቶ ሲያበጥርልኝ ..መልሶ እየጎነጎነ ሲሰራልኝ …አቤት የተደሰትኩት መደሰት.ለካ እሱ እየተሰናናተኝ ነበር.ለመቸረrሻ ጊዘዜ ሰውነቴን እዳበሰኝ ነበር…የልጅ እጅ ሰውነትህ ላይ ሲያርፍ የሚሰማህን ስሜት ታውቀዋለህ…?በምንም ሊገለፅ የማይችል ልዩ ነው....እንደዚህ እንደዚህ እያልን አምስት ሰዓት ተኩል ሆነ፡፡
‹‹.ከዛ በቃ እማዬ ክፍሌ ናፍቆኛል ››አለኝ
‹‹እሺ ግባ እኔም እስከዛ ቆንጆ ምሳ በራሴ እጅ ሰራልሀለው›› አልኩና እሱን ወደክፈሉ ሸኝቼ ወደኪችን ገባው፡፡ ከዛ ሚወደውን ምግብ ሁሉ አንድ ሳላስቀር ሰርቼ ጠረጳዛውን ሞላውና ወደክፍሉ ሄጄ አንኳኳው መልስ የለም…እስኪደክመኝ አንኳኳው ‹እንቅልፍ ወስዷት ይሆን?› የሚል ጥርጣሬ ገባኝ…‹‹እንደለመደው ወጥቶ በመሄድ ጠፈቶብኝ ይሆን? ›ስልም ተጠራጠረርኩ…ቁልፍ አስመጣውና ከፍተን ስንገባ ..ልጄ በሰማያዊ ሲባጎ እራሱን አንጠልጥሎ በድኑ በአየር ላይ እየተሸከረከረ ነበር፡፡
ማንኛዋም እናት በእኔ የደረሰው ሀዘን አይድረስባት…ያው አሁን እኔም በህይወት መኖሬን እርግጠኛ አይደለውም…ውስጤ ደክሟል..ተስፋዬ መክኗል…ለህይወት ያለኝ ጉጉተት ጠፍቷል..የምበላው ምግብ ጨው ይኑረው አይኑረው እራሱ መለየት ትቼያለው…የምጠጣው ውሀ ይሁን በረኪና ግድ አይሰጠኝም…የዩኒቨርሲተ አስተማሪ ልሁን የፅዳት ሰራተኛ እርግጠኛ አይደለውም…ፕሮፌሰር ብለው ሲጠሩኝ እራሱ ማንነው? ብዬ መደንገጥ ጀምሬያለው..እኔ ይሄ ሁሉ ቀርቶብኝ እናት ብቻ ነበር መሆን የምፈልገው… የቢላል እናት መሆን…፡የቢላል እናት በሚል በፀጋ በተሞላ አስደናቂ ስም መጠራት.፡፡

ፖሊሱ ራሱ የሁሉቱ ሴቶች ሀዘን በጥልቀት ተጋባበት….ምንአይነት የተለየ ሰው ቢሆን ነው በዚህ መጠን ይወዱት የነበረ…?ሲል በውስጡ አሰበ….ከመሳቢያው ኪስ ውስጥ አንድ ወረቀት አወጣና ጠረጳዛ ላይ አሰቀመጠ….እና በሁለቱ መካከል ገፋ አደረገና አስጠጋላቸው.ሁለቱም እርስ በርስ ተያዩ
‹‹…ምንድነው ኢንስፔክተር?›ሲፈን ነች ጠያቂዋ
የቢላልን ክፍል ስንመረምር ያገኘነው ነው…ለሁለታችሁ ከመሞቱ በፊተ የተወላቸሁ መልዕክት ነው.፡
ሲፈን በፍጥነት አፈፍ አድርጋ አነሳችው….ድምፃን ከፍ አድርጋ ማንበብ ጀመረች፡፡

I hope you are blessed
With a heart like a wildflower
Strong enough to rise again
After being trampled on
Tough enough to weather
The worst of the summer
and even able to grow and flowrish
In the most broken of places
//
ማን ነበር እነዚህን የሀዘንና የተሰፍ እንጉርጉሮ ያንጎራጎረው.?.እኔ እንጃ ተረሳኝ/እማዬ….አንቺ የአለሞ ቁጥር አንድ እናት ነሽ...በጣም ነው የምወድሸ….ጤነኛም ስሆንም እዕምሮዬም በተቃወሰ ጊዜም ጭመር አንቺን ባለመቋረጥ እወድሻለው…እናም ደግሞ ከሞትኩ ቡኃላም እንደምወድሽ እንዳትጠራጠሪ፡፡ደምፅሽ እያወራሽኝ ሁሉ ይናፍቀኝ ነበር፤.ጠረንሽ ጉያሽ ተሸጉጬ እራሱ እራበዋለው…እማዬ ጥዬሽ ስለሞትኩ በጣም አዝናለው….ግን የግድ ማድረግ ስላላብኝ ነው፡፡አዎ በፍጥነት ውሳኔ ወስኜ እራሴን ካላጠፋው የምወዳትን ልጅ አጠፋለው….እሷን ገድዬም ደግሞ ብተርፍ አንድ ነገር ነበር …..ከገደልኮት ቡኃላ ደግሞ እራሴን ማጥፋቴ የማይቀር ነው..ሁለት ኪሳራ.፡፡..እና እማዬ ይቅር በይኝ…
ሲፈን ….አንቺ በነፍሴ የማፈቅራት ልዩ ሴት ነሽ….በጣም ልዩ ሴት..፡፡በንግግርሽ በጣም ከመደንዜ የተነሳ የእውነትም አንቺን ስለማግባት እያሰብኩ ነበር…ቃል እንደገባሽልኝ ገነት መሳይ በተፈጥሮ ያሸበረቀች ልዩ የብቻችን ቦታ ወስደሺኝ .እዛ ጎጆችንን ቀልሰን ..ልጆቻችንን ወልደን….ብርቱካንና መንጎ ከጎሮ እየቀነጠስና…ጥልል ባለ የወንዝ ውሀ ገላችንን እየታጠብን …በዝሆንና ቀጪኔ ጀርባ ላይ ሰርከስ እየሰራን..ብዙ ብዙ ነገር እንዳልም አድርገሺኛል….
ግን አንዳንዴ መራር ቢሆን እውነታን መጋፈጥ የጀግኖች ባህሪ ነው.እና እኔም ጀግና መሆን ወሰንኩ…፡፡ለአንቺ ህይወት የሚበጀውን ዘላቂ ነገር ማስብ እንዳለብኝ ወሰንኩ…አንቺን አንቄ ከመግደሌ በፊት እራሴን ማንጠልጠል እንዳብኝ ወሰንኩ…፡፡.እንደዛ ያደረኩት ለአንቺ አስቤ አይደለም፡፡.ጥዬሽም ለመሄድ አንጀቴ ጨካኝ ሆኖ አይደለም…አብረን ብንሞት እና አንድ መቃብር ብንቀበር ደስ ይለኝ ነበር…ግን እንደዛ ማደርረግ አልቻልኩም .፡፡ለምን? ለልጃችን ስል፡››
.ማንበቧን አቋረጠችና አንዴ ፕሮፌሰሯን አንዴ ኢንስፔክሩን እያፈራረቀች ተመለከተች‹‹..የምን ልጁ?››
ፕሮፌሰሯ ትከሻዋን በመነቅነቅ ‹እኔ ምን አውቄ ›የሚል መልስ ሰጠች..
እንስፔክተሩ ‹‹ማንበብሽን ቀጥይ ›› አለት
ማንበብ ቀጠለች…
‹እማዬ እና ሲፈን…እድለኛ ከሆንኩ አንድ የምስራች ልንገራችሁ…ማለቴ ይሄን ደብዳቤ ከማንባችሁ በፊት በሌላ መንገድ ዜናውን ካልሰማችሁ ማለቴ ነው፤እማዬ ልጅ ትቼልሽ ነው የሞትኩት…የልጅ ልጅ ሊኖርሽ ነው..ሲፈን እርጉዝ ነች የእኔ .ል..ጅ…..አርግዛ..ለች.›
ሲፈን ከመቀመጫዋ ተነሳች..ሆዷን በእጆቾ ዳበሰች..
‹‹ምን ማለት ነው.?››ማርገዜን እንዴት ነው ያወቀው…?እንዴት እንደዛ ሊሆን ይችላል?››
‹‹ምነው? ግንኘነት አልፈፀማችሁም እንዴ…?››ኢንስፔክሩ ነው የጠየቃት
‹‹አይ.. እሱማ ፈፅመናል..አዎ በደንብ ፈፅመናል..ግን ያልገባኝ እኔ ማርገዜን ሳላውቅ እሱ እንዴት..?ደሞ እኮ ምንም አይነነት የእርግዝና ምልክት እየታየብኝ አይደለም››
‹ኢንስፔክተር ይቅርታ አድርግልን ከፈለከን በሚመችህ ሰዓት ተመልሰን መምጣት እንችላለን ..አሁን ሆስፒታል ሄደን ይህንን ተአምር ማረጋገጥ አለብን.››ከመቀመጫዋ ተነስታ ሲፈንን እየጎተተች የኢንስፔክተሩንም ይሁንታ ሳትጠብቅ ይዛት ወጣች፡፡ወደ ሆስፒታል፡
///
አለም በምንም ጉዳይ ላይ ሚዛን የምትጠብቅበት የራስዋ የሆነ ስውር ቀመር አላት…፡፡ገፍትራ ከገደል አፍፍ ላይ ብትጥለንም ስንወድቅ ግን አስከመጨረሻው ተሰባብረን እንዳንደቅ ማረፊያችንን በተደላደለ የሰንበሌጥ ሳር አልብሰሳ ትጠብቀናለች ፡፡ድንገት ሳናስበው በአስፈሪ የአዞ አፍ ተሰልቅጠን ብንዋጥም ሆዱን ሰንጥቀን አረሳችን ነፃ የምናወጣበት ጩቤ ከጎናቸን እናገኛለን፡፡
ቢላለ በምን አይነት ተአምር እንዳወቀ ለሁለቱም እንቆቅልሽ ቢሆንባቸውም በምርመራ እንዳረጋገጡት ሲፈን የሶስት ሳምንት እርጉዝ ነች፡፡አዎ ከጭለማ ቡኃላ ብርሀን ይፈነጥቃል..ከምሽት ብሃል ንጊት አይቀሬ ነው….ከስቅለት ቡኃላ ትንሳኤም የሚጠበቅ ነው…በሁለቱ ሴቶች በሀዘን የደቀቀ ልብ ውስጥ የሆነች ብጣቂ ተስፋ ለመነቃቃት ስትንፈራገጥ ትታያለች፡፡

ይቀጥላል....


የመወያያ ግሩፑን ይቀላቀሉን
@ethio_lifes_group


╔═══❖• •❖═══╗
@fkrn_be_kalat
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@fkrn_be_kalat_bot ❥❥________⚘_______❥❥
813 viewsከማን ገጥመሽ ይሆን ✧ŊąøŁą ✧, 14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 17:14:07 ነፍስ ስታፈቅር

ምዕራፍ - 23

ደራሲ- ዘሪሁን ገመቹ
.
.
.
ፀሀይ በደመቀ ብርሀኗ እና ለብ ባለው ሙቀቷ በፈገግታሽ ብትወጣም ሰዓቷን ጠብቃ መክሰሟና መጥለቋ አይቀሬ የተፈጥሮ ግዴታ ነው..ጨረቃም ምሽቱን ጠብቃ በዝግታ እየተሳበች በመውጣት ሰማዩ ላይ በመገማሸር ብርሀኗንም ውበቷንም ብተረጭም ንጊት ሲቃረብ መጥፋቷ የሚጠበቅና የግድ የሆነ የተፈጥሮ ግዴታ ነው፡፡ደጅ ላይ የተተከለ አበባም ፈንድቶ በማዓዛውም በውበቱም አካባቢውን አድምቆ ለንቦችም ለቢራቢሮዎችም የሚገባቸውን ምግብ ያለስስት ለግሶ የማታ ማታ ወይ በአንድ አድናቂው ተቀንጥሶ ወይ ደግሞ በራሱ የተፈጥሮ ኡደት ጊዜው ደርሶ መድረቁና መርገፉ የማይቀር ነው፡፡
ሰውም እንደዛ ነው፡፡ከተወለደ..መቼም ይሁን መቼ የሞት ዕጣ እንዳለበተ ቅንጣት የማያጠራጥር ንፅህ እውነት ነው፡፡እንደውም ለሰው መለቀስ ካለበት ተክክለኛው ወቅት ሲወለድ ነው፡፡ብልሁ ሰው ለሞት ቀለብነት እየተፈጠረ ነውና፡፡ዳሩ ሰው ሰው የሚሆነው ምንአልባት ለእናት ካልሆነ በስተቀር ለሌላው ሰው ቅርፅ የሚመዘን ውበት የሚኖረው ከተወለደ ብኃላ በእድገቱ እና በኑሮ ውጣ ውረዱ ከእያንዳንዱ ሰው ጋር በሚፈጥረው መስተጋብር ፤በእያንዳንዱ ነጠላ ገጠመኝ በየግለሰቦቹ ልብ ውስጥ ባለው ግዛት የሚገነባቸው የትዝታ ግንባታዎች አይነት ነው ፡፡
አንዳንዱ እድሜ ልክ አጠገባችን ኖሮ በውስጣችን ያለው ትዝታ ከእጅ መዳፍ የማይበልጥ ይሆናል...ሌላው ደግሞ ሶስት ቀን ስራችን ቆይቶ ሀገር የሚያህል ግዛት በልባችን ተመርቶ በደግነት ጡብ የታነፁ በፍቅር ልስን ያማሩ ለዘመነት የሚበቁ የትዝታ ግንብ ገንብቶ እናገኘዋለን፡፡
ቢላል በሲፈን ልብ ውስጥ የፈጠረው እንደዛ አይነት ታአምር ነው፡፡እንደውም ከዛም በላይ ነው.፡፡ለሰው ሊያስረድት ከሚችሉት በላይ...ለራስም አስበው ሀሳቡን ለመቋቋም ከሚችሉት በላይ…በመኖር እና ባለመኖር መካከል ያለች የሳሳች በጣም ቀጭን የህይወት ክር ላይ አንጠልጠሎ የሚያላጋ ስሜት ላይ የሚያስቀምጥ፡፡
ሙሉ በሙሉ ጥቁር ለብሳለች….ከለቅሶ ብዛት አይኗቹ ከተገቢው በላይ ማበጣቸው ካደረገችው ግዙፍ ጥቁር መነፅር እንኳን ሙሉ በሙሉ ሊከልላቸው አልቻለም፡፡ከሁለት ቀን እራስን የመሳትና የሆስፒታል ቆይታ ቡኃላ ነው እንደምንም ተደግፋ ቀብር ላይ የተገኘችው፡፡የፕሮፈሰሯ ሆነ የእሷ ቤተሰቦችና ወዳጇች በብዛት ተገኝተዋል፡፡ከዛም በላይ ወሬ ቃራሚ የሚዲያ ሰዎች ከለቀስተኛው ጋር በመመሳሰል ፤ አንዳንዱ መንነታቸውን የሚለይ ባጅ አንገታቸውን አንጠልጥለው በግልጽም ተገኝተዋል፡፡
የቀብር ፕሮግራሙ ብዙ ሀሜቶችና ጉረምርማተዎች የታጀበ ነበር....የአልቃሹ ቁጥር የአንድ ሰው የእጅ ጣት አይበልጥም…በሀዛን የተሰበሩት ፤.ከልባቸው በመንሰፍሰፍ የሚያለቅሱት ደግሞ ፕሮፌሰሯና ሲፈን ብቻ ናቸው….እርስ በርስ የእየተቃቀፉ..እርስ በርስ እየተደጋገፉ…እርስ በርስ እየተፅናኑ ይህንን የጨለማ ቀን ግዙፍ ተራራን ለመግፋት እየጣሩ ነው….ከገቡበት ጥቅጥ የብቸኝነት ጨለማ ዋሻ በእንዴት አይት ፅናት ገብተው ሳይፈራርሱና ማንነታቸውን ሳያጡ ከዚህ ክፉ ፈተና እንዴት ማገገም እንደሚችሉ በየልባቸው እየተማከሩ ነው፡፡
ቀብሩ ከተጠናቀ ብኃላ ያው በደንቡ መሰረት ቀጥታ ወደፕሮፌሰሯ ቤት ነው ያመሩት ፡፡ቤተሰቦቾም ሆኑ ሄኖክ ከሚከታተሏት ሰዎች ጋር የነበራቸውን ውል ሙሉ በሙሉ አቋርጠዋል፡፡እናም አሷ ግድ ባይኖራትም አሁን በየሄደችበት እየሄደ የሚከታተላት ሰው ከጀርባዋም ሆነ ከፊቷ የለም፡፡
///
..ቀብሩ ከተጠናቀ በሶስተኛው ቀን ቡኃላ ፕሮፌሰሯ እና ሲፈን ፖሊስ ጣቢያ ተጠሩና ሁለቱም በአንድላይ መርማሪ ፖሊስ ፊት ለፊት ቀረቡ፡፡
‹‹ከቢላል ጋር ያላችሁን ዝምድና ወይም ግንኙነት?››የፖሊሱ ጥያቄ ነበር
‹‹ሁለቱም ተራ በተራ አብራሩ››
‹‹ሲፈን ..ቢላልን ለመጨረሻ ጊዜ ያየሽው መቼ ነው?››
‹‹ከሞቱ ከስድሰት ወይም ከሰባት ሰዓት በፊት››
‹‹የት ?››
‹‹እቤቴ ማለት አባቴ ቤት እኔ ክፍል››
‹‹ምን ሊሰራ ነበር የመጣው ..?››
‹‹ያው እደነገርኩህ ቤላል ጓደኛዬ ነው…ድንገት ከተሰወረ ከ22 ቀን ቡኃላ ለሊት ላይ የቤታችን ጣሪያ ቀዶ ነበር የገባው…እና ያንን በማደረጉ በነፍሴ ጭምር ነበር የተደሰትኩት፡፡ ከዛ ቡኃላ በተከታታይ ሀያ ለሚሆኑ ቀናት ከዛ ክፍል አልወጣም ነበር.››
‹‹ሀያ ቀን ሙሉ››
አዎ …ብዙ ነው እንዴ …?.ለእኛ ግን የሁለት ቀን ያህልም ርዝመት አልነበረውም….እንዴት መሽቶ እንዴት እንደሚነጋ አናውቅም ነበር…ዋናው ጭንቀታችን የእሱን እዛ መኖር እቤተሰቦቼ ወይም ሌላ ሰው እናዳያውቅ ማማረግ ነበር.ያም ተሳክቶልና.፡፡.በህይወቴ ትልቅ ትርጉም ያለው የሚገርም ጊዜ ነበር ያሳለፍነው….እድሜ ልኬን ከእዛ ክፍል የመውጣት እቅዱም ፍላጎቱም አልነበረኝም…የውጩን አለም ጠቅላላ ዘንግቼው ነበር..ምንም የሚናፍቀኝ ነገር አልነበረም…ስራዬ..ሀብቴ ሰሜ ..በእቅፌ ከነበረው ቢላል ጋ ሲነፃፀሩ ምንም ትርጉም አልነበራቸውም፡፡››ረጅም ትንፋሽ ወሰደችና በጉንጮቾ ላይ ያለከልካይ የሚፈሰውን እንባ በሶፍት መጠራረግ ጀመረች…ከዛ ፀጥ አለች
‹‹ቀጥይ ..እየሰማውሽ ነው››አንስፔክተሩ ነው በገለፃዋ እንድትቀጥላ ያበረታታት.ፕሮፌሰሯ በእንባ ከማገዝ ውጭ በዝምታ እንደተዋጠች ነው፡
‹‹ወደዋናው ነጥብ ልምጣልህና የሞተ ቀን ማለቴ አሁድ አብረን በደስታ አደርን ጥወታ በማለዳ ነቃንና ….ብዙ የደስታ ወሬዎች አወራን...ሳቅን.. .ተላፋን…..የምንወደውን ሙዚቃ በአንድ ኤሮፎን አዳመጠን….ሁለት ሰዓት ተኩል አካባቢ ልክ እንደሌሎቹ ቀናት የምንበላውን ቁርስ ለማምጣት በውጭ ቆለፍኩበትና ወደኪችን ሄድኩ፡፡ ብዙም አልቆየውም .. ከ10 ወይም ከ12 ደቂቃ ቡኃላ የምንበላውን ቁርስ ይዤ ስመጣ ክፍሉ ባዶ ነበር…ሻወር ቤት ፈልኩ ..አልጋ ስር ሳይቅር ፈለኩ…በጣም ደንገጥኩ.. ልጮህ ሁሉ ነበር፣.ቡኃላ ጠረጳዛ ላይ መልዕክት ትቶልኝ ነበር›
‹‹ምን ይላል መልዕክቱ?››
‹‹እማዬ ናፍቃኛለች…እሷ ጋር ሄጄያለው…በተለመደው መልክ ማታ ተመልሼ መጣለው…በጣም እወድሻለው›› ይላል፡
ከዛ ተረጋጋው.‹. ቢሆንም መንገድ ላይ አደጋ ያጋጥመው ይሆን…?› የሚል ስጋት ስላለብኝ ከአንድ ሰዓት ቡኃላ መሰለኝ ለፖሮፌሰር ደወልኩና ጠየቅኳት ..በደስታ እሷ ጋር እንዳለ ነገረችኝ..፡፡
ከዛ ቡኃላ በቃ ሰባት ሰዓት ላይ ተደውሎልኝ እራሱን አጥፈቷል ተባልኩ…መአት ነው የወረደብኝ…ከከረምኩበት ገነት የሆነ ክፉ አጋንንት በእንዴት አይነት ፍጥነት አሽቀንንሮ ሲኦል እንደጨመረኝ አልገባኝም…አለም ግን እንዴተ አስቀያሚ ነች….ጠንካራ አለት ነው ብዬ የቆምኩበት አፈር ነው ድንገት ተደርምሶ እንጦሮጦስ ወስዶ ያሰመጠኝ፡፡››በእንባዋ እየታጣበች በመሪር ሀዘን የነበረውን ነገር አስረዳችው፡፡
‹‹እሺ ፕሮፌሰርስ?››
‹‹እሷ እንዳለቸው ነው.ሶስት ሰዓት ሲሆን ሳሎን ቁጭ ብለን ቁርስ አየበላን ሳለ . በሩ በዝግታ ተከፈተ… አይኔን ወደዛ ስልክ የእኔ ምስኪን ልጅ ነበር..፡፡ብታይ አምሮበታል…እነዛ ሰማያዊ አይኖቹን እላዬ ላይ ሲያንከባልላቸው የተሰማኝ የደስታ ስሜት ልግልፃልህ አልችልም...ከአርባ ምናምን የጭንቅ ቀን ቡኃላ ነበር ልጄን ያቀፍኩት …እቤቱን በጪኸት አስነካውት፤ ግቢው ውስጥ ያሉት ሰዎች ሁሉ ተሰበሰቡ ፡፡
882 viewsከማን ገጥመሽ ይሆን ✧ŊąøŁą ✧, 14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 13:04:57 ‹‹አይ እውቴን ነው….››
‹‹እብድ አግብተሸ አንዴት እንዴት ልትሆኚ ነው..?በዛ ላይ ከእብድ መውለድ አለ…ነው ወይስ አሁን ጤና ስለሆንኩ ሁልጊዜ እንደዚሁ የሚቀጥል መሰለሽ›
‹‹ግድ የለህም ..ከእኔ ጋር ከተጋባህ ለዘላለም ጤነኛ ትሆናለህ…ባትሆንም ደግሞ ከጎኔ እስካለህ ድረሰ ግድ የለኝም…››5
‹‹አይ ሚሆን አይመስለኝም…..ቅድም እኮ ነገርኩሽ .አንቺ ብዙ ጣጣ ያለብሽ የአደባባይ ሴት ነሽ›
‹‹ለአንተ ስል ሁሉን ነገር ተዋለው.በእዕምሮህ ያለችውን አይነት ሴት ሆንልሀለው…እልም ያለ ገጠር እንገበለን በደን የተሸፈነ ፤እንስሳት የሚተረማመሱበት፤ ወፎች የሚደንሱበት ፤የሰው ግርግር የሌለበት አንድ አነስተኛ ገነት መሳይ ደሴት እንገዛና እዛ እንኖራለን….›
‹‹ወይ .ለዚህ እኮ ነው በነፍሴ የማፈቅርሽ..እና ደግሞ በጣም ነው ያስጎመዠሺኝ ….ግን ሌላ ሁለት ችግር አለ››
‹‹ምንና ምን?››
‹‹አንደኛው የአባትሽ ጉዳይ ነው…ጋብቻሽን በተመለከተ ስለተፈራረምሽው ውል አውቀለው››
‹‹አሱን ለእኔ ተወው የሆነ መፍትሄ አገኝለታለው…ሁለተኛውን ችግር ንገረኝ››
‹‹ሁለተኛው እረሴው ነኝ…እስከዛው ካልገደልኩሽ….›
‹‹ከገደልከኝማ ተገላገልን …ሁሉ ነገረ እዛ ላይ ይገባደዳል››
‹‹እንደዛ ከሆነ እሺ…ምን አልባት ልንጋባ እንችላለን…አሁን ደህ እደሪ››
‹‹ደህና አደርልኝ.››
‹‹ጭኑ መካከል አስገባትና ቅልፍልፍ ብለው ተኙ…ሁለቱም በደቂቃዎች ውስጥ ነበር ጭልጥ ያለ ሰላማዊ እንቅልፍ የወሰዳቸው፡፡


ይቀጥላል ....


ይሄው ነፍስ ስታፈቅር ክፍል 20 21, እና 22 (ሥስት ክፍል) በቃላችን መሰረት ተለቀዋል። ሌላም ሁለት ክፍል 23 እና 24 እንዲለቀቅ ጉሩፑ ላይ Add ማድረጋችሁን አትርሱ ። 250 ሰዉ Add ከተደረ ሁለት ክፍሎች ይለቀቃሉ ። ካልሞላ ግን እስኪሞላ ትጠብቃላቹ።ከስር በተቀመጠዉ ሊንክ ግሩፑ ላይ እየገባችሁ Add አርጉ ። ግሩፑን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑት

https://t.me/ethio_lifes_group
https://t.me/ethio_lifes_group
https://t.me/ethio_lifes_group


አመሰግናለሁ

ብዙ ፍቅር ለእናንተ
1.2K viewsከማን ገጥመሽ ይሆን ✧ŊąøŁą ✧, 10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 19:09:17 Eyoba

ስወድቅም ስነሳ ሳገኝ እና ሳጣ
አልተለየቺኝም ፍቅሬን አሰበልጣ...

➽#ለወዳጅዎ_ያጋሩ_SHARE
           
𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲ @fkrn_be_kalat ሼር

:¨¡.¡¨ : SHARE :¨¡.¡¨:
♡ ፍቅርን በቃላት♡︎

●▬▬▬▬๑۩♡۩๑▬▬▬▬▬● ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌ ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌
4.9K views16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 18:01:13 የግጥሜ ርዕስ #ኑሪልኝ_እናቴ

እማ ከዚያች ቀን ጀምሮ፤ ከተወለድኩባት
በቅፍሽ ተኝቼ አንቺን ካየሁባት .....
በስስት ስታይኝ በስስት ማየቴ.......
ላይፈታ ቅኔው ታስሮል በህይወቴ
የመኖሬ ክታብ የልብ አለም ውዴ
አንቺን ባላገኚሽ እኖር ነበር እንዴ


እግዜር ስራው ቅዱስ፤ ስጦታው በጋሻ
አንቺን አኖረልኝ የኔን መኖር ሲሻ....
ሚስጥር አለው አንቺን ሲሰጠኝ ስጦታ
የመኖሬን ቅኔ በኑሮሽ ሲፈታ....
በዛ ሁሉ ፍቅር በቅፍሽ ተኝቼ
ተመስገን እንድል ነው እማ አቺን አጊቼ


ለዚች አለም አንቺ አንድ ብትባይም
በፍጥረታት ግምት ልክሽ ባይታይም
አለሜ ነሽ ለኔ አቻሽ አይገኝም....
እናት ሲባል ስሟ በልጆቾ አደበት
ይጣፍጣል ልኳ ልክ ሲገኝለት


ትዝ ይልሻል እማ፤ ልጅ እያለው ድሮ
እጅጉን ቸግሮን ተጫጭኖን ኑሮ
የምበላው ጠፍቶ ቸግሮኝ ስታይኝ
የሰው ደጅ ጠናሽ እኔን ልታበይኝ
የእግዜር ስራ ረቂቅ ቸር ባህሪ ያለው


እማ አንቺን ለገሰኝ ለግሰኝ ሳልለው
ተመስገን አምላኬ ሌላ ምን እላለው
እማ እራስ ወዳድ ሆኖ ቢረሳሽም አለም
ላረሳሽ ቃል አለኝ እስከ ዘለአለም
6.7K views★ ŊąøŁą şəłəçŧívę ★, 15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 22:55:54 ‍ በጣም ነው ውስጤ የተጎዳው። አንተ ለህይወቴ መመሪያ እንዲሆኑ በወረቀት
ጫር ጫር አድርገህ በምትሰጠኝ መሳጭ ሀሳቦችህ እና ወደ
ውስጤ እንዳስብ በሚያደርገኘ ልዩ ፀጥታህ መንፈሴ
እንዲጓለብት አግዘኸኛል፡፡..ጋሽ በቄም በያንዳንዱ የስራ
እርምጃዬ በሀሳብም በገንዘብም እየረዳኝ በኢኮኖሚ እራሴን
እንድችል ከዛም አልፌ ለሰው እንድተርፍ አድርጎኛል፡፡ሙሉ
የሆንኩት በሁለታችሁ ጥምር ጥረት ነው፡፡….ብቻ አላውቅም
ጋሽ በቄን በማጣቴ በጣም ከፍቶኛል፡፡ የሆነ ነገር ብለህ
ብታፅናናኝ እወዳለው፡፡››በማለት ንግግሬን አቁሜ በመላ
ጉንጬ ላይ የተዝረከረከውን እንባዬን በሶፍት መጠራረግ
ጀመርኩ፡፡
አዳልሞቲም እኔ ገዝቼ ካመጣውለት ሙሉ እሽግ ልሙጥ
ወረቀት ላይ አንዱን አነሳና በሁለት ደቂቃ ውስጥ ለእኔ ማለት
የሚፈልገውን ፅፎ ሰጠኝ፡፡ወደ ቤት ሄጄ አልጋዬ ላይ ተኝቼ
ነበር ያነበብኩት፤ እንዲህ ይላል….
‹‹ የቅርባችን ሰው በሚሞትበት ጊዜ ስሜታችን ተነክቶ
የምናዝነው በእሱ ውስጥ ያለው እኛነታችንን ከራሱ ጋር
ይዞብን ወደ መቃብር ስለሚወርድ ነው፡፡አንድ ሰው ሞተ
ሲባል ብቻውን አይደለም የሚሞተው በውስጡ ያሉትን
ሚስቱን ፤ዘመዶቹን፤ ጓደኞቹን ጠቅላላ ዓለምን ከራሱ ጋር ይዞ
ጥርግ ይላል፡፡ለእኛ ነው እንጂ ለእሱ እስትንፋሱ
ከተቋረጠችበት ሰከንድ አንስቶ ጠፈር እና በውስጧ ያለውን
ሁለንተና በአጠቃላይ አብረውት ይጠፋሉ፡፡..በዚህም የተነሳ
ከወዲህ ማዶ ሆነን በእሱ ውስጥ የነበረውን የገዛ ራሳችንን
ሞት በውስጣችን እያሰብን በወዳጃችን ሞት እያመካኘን
ለራሳችን እናንጐራጉራለን…አኛም አንድ ቀን ተራችን ሲደርስ
ዓለምን ጠቅላላ ይዘን ጥርግ እንላለን፡፡ከዛም ይለቀስልናል፡፡
በቃ ህይወት እንዲህ ነች ..መወለድ… ማደግ……
መሞት..መወለድ ማደግ… መሞት…ሽክርክሮሽ ››ይላል፡፡
ልጆቹ ወደ መጡበት አገር ለመመለስ ስለቸኮሉ በ14ኛው ቀን
ኑዛዜው እንዲነበብ የአባታቸውን የነፍስ አባት
አሳመኑ፤ምክንያቱ ባይገባኝም እኔም እንድገኝ ተጋበዝኩ፡፡
እያንዳንዱ ንብረታቸውን ለሦስቱም ልጆቻቸው እኩል
አካፍለዋቸዋል፡፡ሆቴሉ ላይ ሲደርሱ ግን እንደሌሎቹ ንብረቶች
የሦስቱም የጋራ ንብረት ቢሆንም እኔ በቃኝ ብዬ እስካለቀቅኩ
ድረስ የቤት ኪራይ ሳይጨምሩብኝ እንድሰራበት፤ ልጆቹ
መሸጥ ከፈለጉ ግን ከ2 ሚሊዬን ብር ባልበለጠ ዋጋ እኔው
እራሴው እንድገዛው ከትልቅ አደራ ጋር መናዘዛቸው
በአደባባይ በሁሉም ፊት ተነበበ፡፡ በውስጤ ከፍተኛ እፎይታ
ተሰማኝ፤እኚህን ሰውዬ በህይወት እያሉ በጣም እወዳቸው
ነበር አሁን ሞተው ደግሞ ይበላጥ ወደድኳቸው፡፡
ንዛዜው ከተነበበ ከሁለት ቀን ቡኃላ ልጆቻቸውን ወደ
መጡበት ሲመለሱ ....በቅርብ በገዛዋት አባይ የቤት መኪና
አዲስአባ ድረስ ሸኘዋቸው፡፡ታዲያ ጉዞ ላይ እያለን‹‹የሆቴሉ
ጉዳይ እንዴት እናርገው?››ስል እየፈራው ጠየቅኳቸው፡፡
‹‹እኛ መሸጥ እንፈልጋለን..ሁለት ሚኒዬን ብር በሚኖርህ ጊዜ
ደውልልን እና አንዳችን መጥተን የህግ ጉዳዩን
እንጨርስልሀለን፡፡››
‹‹ግን እኮ ሆቴሉ አራት እና አምሰት ሚሊዬን ብር ሊያወጣ
ይችላል፡፡››
‹‹እናውቃለን፡፡አጐቴም አራት ሚሊዬን ሰጥቶን ነበር፡፡ግን
አስርም ሚሊዬን ቢሆን ከአባታችን ቃል አይበልጥም፡፡
አባታችን ምን ያህል እንደሚወድህ እናውቃለን ፡፡ስለዚህ
የእሱ ቃል መከበር አለበት..›› አለ ትንሹ ልጃቸው፡፡
በደስታ ተውጬ‹‹ሁላችሁንም አመሰግናለው››አልኩኝ ፡፡
‹‹ግድ የለም....ያው እኮ ትንሹ ወንድማችን ሆነኸል፡፡››አለኝ
ታላቅዬው፡፡…በደስታ ፈገግ አልኩ፡፡

ይቀጥላል....

የመወያያ ግሩፑን ይቀላቀሉን
@ethio_lifes_group


╔═══❖• •❖═══╗
@fkrn_be_kalat
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@fkrn_be_kalat_bot ❥❥________⚘_______❥❥
6.6K views★ ŊąøŁą şəłəçŧívę ★, 19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ