Get Mystery Box with random crypto!

{ብሒለ አበው ወ ሕይወት መንፈሳዊ}

የቴሌግራም ቻናል አርማ finoteabew — {ብሒለ አበው ወ ሕይወት መንፈሳዊ}
የቴሌግራም ቻናል አርማ finoteabew — {ብሒለ አበው ወ ሕይወት መንፈሳዊ}
የሰርጥ አድራሻ: @finoteabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.16K
የሰርጥ መግለጫ

ይዘቱ
፩ ➛ብሒለ አበው(የአባቶችን ለሕይወትታችን መርህ የሚሆኑ ብሒሎች)፣
፪ ➛የቅዱሳን ምክር ተግሳጽ
፫ ➛ለመንፈሳዊ ሕይወት የሚጠቅሙ ትምህርቶች
፬ ➛ ወቅቱን የጠበቁ ትምህርቶች
አላማው
የአባቶቻችንን ፍኖት (መንገድ) ማወቅና መከተል
መንፈሳዊ ህይወት መኖር
ከቅዱሳን ታሪክ ተሞክሮ መውሰድ
።።።።።።።
ሀሳብ አስተያየት ካሎት ➙ 0994794784

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-07 06:47:19
428 views03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 22:14:53 #ዝክረ ቅዱሳን

ሰኔ 30 ፦ መጥምቀ መለኮት
ቅዱስ ዮሐንስ ልደቱ

ዮሐንስ ማለት ‹‹ፍሥሐ ወሐሴት፣ ርኅራኄ›› ማለት ነው፡፡ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ጠራጊ የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ የብሉይ ኪዳን የመጨረሻው የሐዲስ ኪዳን ደግሞ የመጀመሪያው ነቢይ ነው፡፡ ስለ ወላጆቹ ስለ ካህኑ ዘካርያስና ስለ ቅድስት ኤልሳቤጥ በቅዱስ ወንጌል ላይ እንዲህ ተብሎ ተመስክሮላቸዋል፡፡ ‹‹በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስሟም ኤልሳቤጥ ነበረ። ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ።›› ሉቃ 1፡5-6፡፡
እግዚአብሔር ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ዘካርያስ ልጅ እንደሚወልድ ይነግረው ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ላከው፡፡ መልአኩም በመጀመሪያ በመሠዊያው በስተቀኝ በኩል ተገልጦ ለዘካርያስ ታየው፡፡ ለሰይጣን ቀኝ የለውምና መልአኩ ግን ብርሃናዊ የማናዊ ነውና መልአክ እንደሆነ እንዲታወቅ በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ አንድም ሰው ሁሉ ወደ የማናዊ ግብር የሚመለስበት ዘመን ደረሰ ሲል በቀኝ በኩል ታየው፡፡ አንድም ሰውን ሁሉ መክሮ አስተምሮ ወደ ቀኝ ወደ መንፈስ ቅዱስ ሥራ የሚመልስ ልጅ ትወልዳለህ ሲለው በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ ነገር ግን ዘካርያስ የእርሱም ሆነ የሚስቱ
ዕድሜአቸው ስለገፋ የሚስቱን የመፀነሷን ነገር አላምን ቢል መልአኩ ድዳ አድርጎታል፡፡ ዮሐንስም ሲወለድ ‹‹ስሙን ማን እንበለው?›› ሲሉት በጽሑፍ አድርጎ ‹‹ዮሐንስ በሉት›› አላቸው፤ ያንጊዜም አንደበቱ ተፈታለት፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ‹‹ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል›› (ሉቃ 1፡13) ባለው ሰዓት አላመነም ነበር፡፡ አሁን ግን የልጁን ስም ‹‹ዮሐንስ›› ብሎ ሲለው ተዘግቶ የነበረው አንደበቱ ተፈቶለታል፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ጌታችንን በዕድሜ በ6 ወር ይበልጠዋል፡፡ ርጉም የሆነ ሄሮድስ መሢሕ ሕፃን ክርስቶስ መወለዱን ሲሰማ መንግሥቴን ይቀማኛል ብሎ በመፍራት በቤቴልሔም ያሉ ሁለት ዓመትና ከዚያ በታች ያሉ 144,000 (መቶ ዐርባ አራት ሺህ) የቤቴልሔም ሕፃናትን በሰይፍ ሲያስገድል ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ ስትሰደድ፣ ቅድስት ኤልሳቤጥ ደግሞ ወደ ሲና በረሃ ሄዳ ልጇን ዮሐንስን ከዚያ ደብቃዋለች፡፡ ከመሄዷ በፊት ግን ከባሏ ከዘካርያስ ጋር ሲሰነባበቱ የሚሆነውንም ሁሉ እርሱ ቀድሞ ያውቅ ነበርና ‹‹ሕፃኑን ልጄን ሲያጡ እኔን ይገድሉኛል፣ አንቺ ግን ወደ በረሃው ይዘሽው ሂጂና በዚያ ሸሽጊው›› ብሎ መክሯታል፡፡ እርሷም ከሄደች በኋላ የርጉም ሄሮድስ ጭፍሮች ዮሐንስን ባጡት ጊዜ ወደ ዘካርያስ መጥተው ‹‹ልጅህን ወዴት አድርሰኸው ነው? ወዴትስ ደበቅኸው? አሁን ከደበቅህበት አምጥተህ ፈጥነህ አስረክበን›› በማለት የፍጥኝ አስረው ካሠቃዩት በኋላ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ከሚሠዋበት በቤተ መቅደስና በዕቃ ቤት መካከል አንገቱን ቆርጠው ገደሉት፡፡ የዘካርያስም ደም እስከ ሰባት ዓመት ድረስ እየፈላ ደሙ ሲካሰሳቸው ኖረ፡፡
‹‹ቅድስት ኤልሳቤጥም ልጇን ዮሐንስን ይዛ ወደ በረሃ ከገቡ አምስት ዓመት በሆናቸው ጊዜ ዮሐንስ ዕድሜው ሰባት ዓመት ከመንፈቅ ከሆነው በኋላ እናቱ ኤልሳቤጥ ሞተችበትና ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም በሰፊዋ በረሃ ውስጥ በአራዊቶች መካክል ብቻውን ቀረ፡፡ ለዮሐንስ ግን በእርሱ ላይ ምንም መጥፎ ነገር ሳያደርጉ የቶራና የአንበሳ የነብርም ልጆች እንደ ወንድምና እንደ እኅት ሆኑት፡፡ አራዊቶችም ሁሉ ወዳጅ ሆኑት፡፡ ምግቡም የበረሃ ቅጠል ነው፤ መጠጡም ከተቀመጠባት ድንጋይ ሥር የፈለቀችለት ውኃ ነበረች፡፡ ዮሐንስ ሰውነትን አለምልመው፣ ሥጋን አለስልሰው፣ ገጽንና ፊትን የሚያሳምሩትን ምግቦች አልተመገበም፡፡ የበረሃ ቅጠሎችንም አልተመገበም፡፡ አንቦጣ ከተባለችው ከአንዲት የበረሃ ቅጠልና ከጣዝማ ማር በስተቀር ከሚበሉት ምግቦች ሁሉ ዮሐንስ ኅርምተኛ ሆኖ የተለየ ነበር›› ይላል ቅዱስ ገድሉ፡፡ ነገር ግን ‹‹አንቦጣ›› ተብላ የምትጠራ አንዲት የበረሃ ቅጠልንና የጣዝማ ማርን እየተመገበ ማደጉን ለመግለጽ ብዙ ጊዜ በተለምዶ ‹‹የዮሐንስ ምግቡ የበረሃ አንበጣ ነበር›› ተብሎ የተሳሳተ ነገር ሲነገር ይሰማል፡
የመጥምቀ መለኮትቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን
አዘጋጅ ፦ ኦብሳ ተፈሪ
https://t.me/Amde_Tewahedo_SS
510 views19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 14:53:10
ለጸሎት ፣ ቤተክርስቲያን ለመሄድ ፣ የቤተክርስቲያን ትምህርት ለመማር ጊዜ የለንም ለሚለው የአቡነ ሺኖዳ ምክር፦

አንተ በእየለቱ ጠዋት ጠዋት ስትነቃ የምትጨነቀው ስለምድነው ? የምትጨነቀው ፊትህን ታጥበህ፣ቁርስህን ለመብላትህ ልብስህን መልበስህ ና ለመሄድ መዘጋጀትህ የቀን ተቀን ሕይወትህ ነውን? ወይስ መጀመሪያ ጉዳይህ ዕለቱን በጸሎት በንባብና በተመስጦ ከእግዚአብሔር ጋር መጀመርህ ነው ? የአንተ ድርጊት የሚከናወነው እንዳንተ ፍልጎት ነው ። እንደዚህ አይነቱ ጉዳይ አለ አንዳንዶች ፦ << ለመጸለይ ጊዜ የለንኝም !>> ይላሉ ። እኔ ግን እንደዚህ ዓይነቱ ይቅርታ እውነተኛ ምክንያት ነው ብዬ ስለማልወስደው አልቀበለውም ።
አንተግን ጸሎትህንና ተመስጦህን ካስቀደምክ ያ አጣውት የምትለው ጊዜህን ታገኘዋለህ ። ስለሆነም በሁሉም ነገር ላይ ለእግዚአብሔር
ቅድሚያ ስጥ ።
@finoteabew
642 viewsedited  11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 11:58:38 # ምክረ አበው
/ አስተማሪ ታሪኮች /
አትሊስት At least
የሆነች አንዲት ሴት ከአንድ ካህን ጋር ክርክር ትገጥማለች ። ካህኑ '' መጽሐፍ ቅዱስን በንባብ ብቻ ማወቅ መረዳት ይከብዳል '' ሲሉ ልጅቱ ግን '' ትርጓሜ ምናምን አያስፈልግም መጽሐፍ በላ ካላ በላ ነው ፤ ሔደ ካለ ሔደ ነው '' እያለች የኑፋቄ ወግዋን ታብራራለች። ካህኑ ብልህ ነበሩና '' እስኪ ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አሰምተሽ አንብቢልኝ '' ሲሉ መጽሐፍ ቅዱሱን ገልጠው ሰጡዋት ጥቅሱ እንዲህ ይ ላል "፤ ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።"
(1ኛ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2:1)
ልጅቱ በንባቡ ግራ ገባት እንደምንም አንብባ ስትጨርስ ካህኑ ፈጠን አሉና '' ሐና ሳሙኤል እናት ቀንድ አላት ማለት ነው ?'' ሲሉ ጠየቋት እሷም ግራ መጋባቷን ለመደበቅ እየሞከረች '' አትሊስት '' ይሔ እንኳን ይተረጎማል አለች
➮ምንጭ ፦ ምጥን ቅመም ክፍል 3
733 views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 06:36:03
#በቅርብ ቀን
711 viewsedited  03:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 14:02:03
688 views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 13:57:45 በዓለ ጰራቅሊጦስ /ጰንጠቆስጤ Pentecost/

ጰንጠቆስጤ ማለት ቃሉ የግሪክ ቃል ነው። ትርጉሙም ሃምሳኛ ማለት ነው።ጰራቅሊጦስ ማለትም በጎን የሚቆም፣የሚረዳ፣የሚያፅናና ማለት ነው። በብሉይ ኪዳን ወቅት አይሁድ የፋሲካ በዓላቸውን ካከበሩ በኃላ ሃምሳውን ቀን የነፃነት በዓላቸው አድርገው ከሰነበቱ በኃላ ሃምሳኛውን ቀን በተለየ ሁኔታ ያከብራሉ ይህም ቀን በዓለ ሰዊት ይባላል። በእነርሱ ሃገር ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት ፀደይ(የእሸት ወራት) ነውና።
እንግዲህ ይህ በዓለ ሰዊት ጌታችን ባወቀ ለሐዲስ ኪዳን በዓል ሁለት ጥቅሞችን እንዲያስገኝ አርጎታል። የመጀመሪያው ለበዓለ ሃምሳ (ጰራቅሊጦስ) ምሳሌ፣መንገድ ጠራጊ፣መተርጎሚያ፣ማሳ፣አኛ መሆኑ ነው ሁለተኛው ግን በዓሉ እንዲከበር ዋናው ምክንያት የሆነው የመንፈስ ቅዱስ መውረድ(ርደተ መንፈስ ቅዱስ) ጌታችን ባረገ በ10ኛው ቀን በተነሳ 50ኛው ዕለት በዝርው የነበሩ አይሁድ ሁሉ ለበዓለ ፋሲካ እና ለበዓለ ሰዊት እንደተሰበሰቡ የተፈፀመ መሆኑ ነው። ይህ በዓልም(በዓለ ጰራቅሊጦስ) የቤተክርስቲያን የልደት ቀን በመባል ይታወቃል። በ1ቀን ብቻ በቅዱስ ጴጥሮስ ስብከት 3ሺህ ነፍሳት አምነው ተጠመቁ።
በሐዋርያት ትምህርት፣በህብረት እንጀራውንም በመቈረስ በጸሎት ይተጉ ነበር ይለናል መጽሕፍ ቅዱስ። ሐዋ2፥41-42
ከዚህ በተጨማሪም ከላይ እንደተጠቀሰው መንፈስ ቅዱስ የወረደበት፣በ3ሺህ ሰዎች ጥምቀት መስፋፋት የጀመረችበት፣ሐዋርያትም ፍሩሃኑ ጥቡዓን(ደፍሮች) ሆነው በእውቀት በልጽገው፣ በአእምሮ ታድሰው ዓለሙን ለመለወጥ ኃይል ያገኙባት እለት ነው። ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም
“መንፈስ ቅዱስ ባይወርድላት ኖሮ የቤተክርስቲያን ህልውና ኮስምኖ ቀጭጮ ይቀር ነበር። ስለዚህም በሚገባ አነጋገር ይህች ዕለት የቤተከርስቲያን የልደት ቀን ትባላለች።” በማለት ተናግሯል።
ከዚህ የተነሳ ሌሎች ሊቃውንትም ዕለቲቱን የበዓላት ሁሉ እመቤት እንደሚሏት ብፁዕ አቡነ ጎርጎሪዮስ ገልጸዋል። በዓለ ጰራቅሊጦስ ከትንሳኤ በ50ኛው ከዕርገት ደግሞ በ10ኛው ቀን ይከበራል። የትንሳኤ በዓልም የሚፈጸመው በዚህ ዕለት ነውና የትንኤው ቃለ እግዚአብሔር በዚህ ዕለት ይፈጸማል ። ይህ ክብረ በዓል የሚከብረው እንደ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሰረት ከዕለተ ሰንበተ ክርስቲያን (እሁድ) ውጪ ሊሆን አይችልም ።
ይህ በዓል ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ለቤተ ክርስቲያን “ከእናንተ ጋር ስኖር ይህን እነግራችኋለሁ አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኳችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል” እና “ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ ።” ሲል የገባው ኪዳን የተፈጸመበት ተደርጐም ይከበራል ።
ፍትሐ ነገሥትም ይህንን በዓል እንድናከብር ያዘናል ። “ ትንሳኤን ባከበራችሁ በሃምሳኛው ቀን ዕርገቱን ባከበራችሁ በአስረኛው ቀን በዓለ ጰራቅሊጦስን አክብሩ ደገኛ በዓልም ይሁንላችሁ ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዛን ዕለት በሶስት (3) ሰዓት መንፈስ ቅዱስን ሰዶልናልና ። በፈቃዱ መንፈስ ቅዱስን የተመለንበት፣ ጸጋውን ሀብቱን ያገኘንበት ፣ እርሱ በእኛ እንዳደረብን መጠን በ72 ቋንቋ የተናገርንበት ፣ ክርስቶስ እግዚአብሔር የባሕርይ አምላክ እንደሆነ ለአህዛብ ለአይሁድ ያስተማርንበት ቀን ነውና።”
ስለ አከባበሩም ተጨማሪ ሐተታዎችን ያትታል ። ይኸውም ትንሳኤን በመብል እና በመጠጥ እናዳከበርነው በዓለ ጰራቅሊጦስ ደግሞ በጾም እና በጸሎት እንድናከብር የሚል ነው።
የሰንበት መዝሙር
ሃሌታ (፫) በሰንበት ዓርገ ሐመረ ገሠፀ ባሕረ ወገሠፆሙ ለነፋሳት ወይቤሎሙ ኢትናፍቁ ወኢይምጻእ ኑፋቄ ውስተ ልብክሙ በከመ ፈነወኒ አቡየ አነኒ እፌንወክሙ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ቦቱ ካዕበ እመጽእ ወእነሥአክሙ ከመ ተሀልዉ ምስሌየ በመንግሥተ አቡየ ዘበሰማያት
ምስባክ
መዝ ፵፮ ቊ ፭-፮
ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ
ምንጭ ፦
https://t.me/Amde_Tewahedo_SS
604 viewsedited  10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 13:08:30 በዕድሜህ መጨረሻ ላይ ልታደርገው የምትሻውን ዛሬ አድርገው ። በዕድሜ መጨረሻ እንደ ሄኖክ ሁሉን ትተህ መኖር የምትፈልግ ከሆነ ዛሬ እንደ ኤልያስ ነቢይ የምናኔን ሕይወት መኖር ትችላለህ ። የሰው መጨረሻ ሰባና ሰማንያ ዓመት ሳይሆን ዛሬ ማታ ሊሆን ይችላል ። ዛሬ የጨበጥኸው ትላንት ሕልምህ ነበረ ፤ የዛሬ ሕልምህ ነገ እውን ይሆናል ። የልጅነት ወዳጆችህን ስታጣ የሽምግልና ዘመዶች ይሰጥሃልና በማያልቅበት እግዚአብሔር ደስ ይበልህ ። የተከፈቱ በሮች ከተዘጉ በማንኳኳት አይከፈቱምና ዕድሎችህን አክብር ። በየቀኑ የሚገጥሙህ መልካም ነገሮች ለትልቅ ኃላፊነት እንድትሾም የመጡ ፈተናዎች ሊሆኑ ይችላሉና አክብረህ ያዛቸው ። ነገር ካለፈ በኋላ መንቃት ፀሐይ ከጠለቀች በኋላ መሰማራት ነው ( ኖላዊ)
1.1K viewsedited  10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 18:38:43 ዕርገት
ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። ሐዋ ፩ ፥ ፱
‹ዕርገት› በግእዝ ቋንቋ ማረግ፣ ከታች ወደ ላይ መውጣት ማለት ሲኾን የጌታችን ትንሣኤ በተከበረ በዐርባኛው ቀን የሚውለው የጌታችን ዐቢይ በዓል ‹ዕርገት› ይባላል። በዓለ ዕርገት ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለዐርባ ቀናት በግልጽም በስውርም ለቅዱሳን ሐዋርያትና ለቅዱሳት አንስት መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትርጓሜ መጻሕፍትን፣ ምሥጢራትን፣ ሕግጋትንና ቀኖናተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተምር ቆይቶ ወደ ቀደመ ዙፋኑ ወደ ሰማይ በክብር በምስጋና ማረጉን በደስታ የምንዘክርበት ዐቢይ በዓል ነው፡፡ በዓለ ዕርገት በቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል፡፡ በዓሉ የሚውልበት ዕለት ሁል ጊዜ ሐሙስን ባይለቅም ቀኑ ግን የአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ቀመርን ተከትሎ ከፍ እና ዝቅ ይላል፡፡ ይህም ማለት ዘንድሮ ግንቦት 25 ቢውልም ሁሌ እንደዚሁ ይሆናል ማለት አይደለም።  
የጌታችን ዕርገት ከትንሣኤ በኋላ በአርባኛው ቀን (በስድስተኛው ሐሙስ) የሚከበረው ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ላይ “ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው” (ሐዋ. ፩፡፫) በማለት የጻፈውን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ቤተክርስቲያንም ይህንን ትምህርት “ኪዳን” ብላ ትጠራዋለች። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኋላ ለሐዋርያት የነገራቸው “መጽሐፈ ኪዳን” ይባላል፡፡
ከጌታችን የዕርገት በዓል(ዐርባኛው ቀን)  ጀምሮ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ ዋዜማ (ዐርባ ዘጠነኛው ቀን) ድረስ ያለው ወቅትም ‹ዘመነ ዕርገት› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዘመነ ዕርገት ውስጥ በሚገኘው እሑድ (ሰንበት) ሌሊት ሊቃውንቱ የሚያደርሱት መዝሙርም ‹‹በሰንበት ዐርገ ሐመረ›› የሚል ሲኾን ይኸውም ጌታችን በሰንበት ወደ ታንኳ በመውጣት ባሕርንና ነፋሳትን እንደ ገሠፀ፤ ሐዋርያቱንም ‹‹ጥርጥር ወደ ልቡናችሁ አይግባ፤ አትጠራጠሩ›› እያለ በሃይማኖት ስለ መጽናት እንዳስተማራቸው፤ እንደዚሁም ወንጌልን ይሰብኩ፣ ያስተምሩ ዘንድ በመላው ዓለም እንደሚልካቸው፤ በሰማያዊ መንግሥቱ ይኖሩ ዘንድም ዳግመኛ መጥቶ እንደሚወስዳቸው የሚያስገነዝብ መልእክት አለው (ሉቃ.፰፥፳፪-፳፬፤ ዮሐ.፲፬፥፪፤ ፳፥፳፩)፡፡
በበዓለ ዕርገት ሊቃውንቱ ሌሊት በማኅሌት፣ በዝማሬ እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ ያድራሉ፡፡ ሥርዓተ ማኅሌቱ እንዳበቃ የሚሰበከው የነግህ ምስባክም፡-  ‹‹ዘምሩ ለእግዚአብሔር ዘዐርገ ውስተ ሰማይ ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ ናሁ ይሁብ ቃሎ ቃለ ኃይል›› የሚለው የዳዊት መዝሙር ሲኾን፣ ቀጥተኛ ትርጕሙ፡-  ‹‹በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ (ላረገ) ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ የኀይል የኾነውን ቃሉን እነሆ ይሰጣል›› ማለት ነው (መዝ.፷፯፥፴፫)፡፡
ምሥጢራዊትርጕሙ፦ደግሞ  ‹‹ነፍሳትን ይዞ ከሲኦል ወደ ገነት ለወጣ፤ አንድም በደብረ ዘይት በኩል ላረገ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ›› የሚል መልእክት አለው፡፡ እንደዚሁም ጌታችን በዐረገ በዐሥረኛው ቀን ‹የኀይል ቃል› የተባለ መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት እንደ ላከላቸው፤ በተጨማሪም ጌታችን በሕያዋን እና በሙታን (በጻድቃን እና በኃጥአን) ላይ ለመፍረድ ዳግም እንደሚመጣ፤ እኛም ይህንን የጌታችንን የማዳን ሥራ እያደነቅን ለእርሱ ምስጋና፣ ዝማሬ ማቅረብ እንደሚገባን ያስረዳናል – ምስባኩ፡፡
 
ጌታችን ለሐዋርያት ነግሯቸው ያረገው የመጨረሻው ነገር “ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” የሚለውን ነው ። ጌታችን አርጎ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያቱ ላይ እስኪወርድ ድረስ ደቀ መዛሙርቱ ለሐዋርያነት የሚያበቃ በቂ የሆነ ጽናት አልነበራቸውምና ይህን ነግሯቸው ወደሰማይ ከፍ ከፍ አለ። ሐዋ ፩
አስቀድመው መላእክት፥ የልደቱን ዜና ለእረኞች ፣ የስደቱን ነገር ለዮሴፍ ፣ የትንሳኤውን ብስራት ለደቀ መዛሙርቱ ሲያደርሱ ከርመው የጌታችን የምድር ላይ የሥጋ ቆይታ ሲጠናቀቅ ደቀመዛሙርቱ ተሰብስበው ወደ ሰማይ በመመልከት ላይ ሳሉ መላእክት ስለሆነው ነገር እንዲህ አሏቸው ፥ “እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤  ደግሞም። የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደስማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሏቸው።”  ሐዋ ፩
እኛም ዕርገቱን እያሰብን ዓይናችንን ወደ ሰማይ እናነሳለን። የራሳችንንም ዕርገት ተስፋ እያደረግን ልባችንን ወደ ሰማያዊዉ ሕይወት ከፍ ከፍ እናደርጋለን። ዳግመኛ በመጣ ጊዜ በክብር ያረገ አምላክ ከትንሣኤ ሙታን በኋላ ያለውን ዕርገታችንን የክብር ያድርግልን።
" ጌታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር ሲመጣ፥ በአምላካችንና በአባታችን ፊት በቅድስና ነቀፋ የሌለበት አድርጎ ልባችሁን ያጸና ዘንድ፥ እኛ ደግሞ ለእናንተ እንደምንሆን ጌታ እርስ በእርሳችሁ ያላችሁን ለሁሉም የሚሆን ፍቅራችሁን ያብዛ ይጨምርም። " ፩ኛ ተሰ ፫:፲፪

አዘጋጅ ➣ ዲያቆን ወልደ አማኑኤል ብርሃኑ
https://t.me/Amde_Tewahedo_SS
717 views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ