Get Mystery Box with random crypto!

# ምክረ አበው / አስተማሪ ታሪኮች / አትሊስት At least የሆነች አንዲት | {ብሒለ አበው ወ ሕይወት መንፈሳዊ}

# ምክረ አበው
/ አስተማሪ ታሪኮች /
አትሊስት At least
የሆነች አንዲት ሴት ከአንድ ካህን ጋር ክርክር ትገጥማለች ። ካህኑ '' መጽሐፍ ቅዱስን በንባብ ብቻ ማወቅ መረዳት ይከብዳል '' ሲሉ ልጅቱ ግን '' ትርጓሜ ምናምን አያስፈልግም መጽሐፍ በላ ካላ በላ ነው ፤ ሔደ ካለ ሔደ ነው '' እያለች የኑፋቄ ወግዋን ታብራራለች። ካህኑ ብልህ ነበሩና '' እስኪ ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አሰምተሽ አንብቢልኝ '' ሲሉ መጽሐፍ ቅዱሱን ገልጠው ሰጡዋት ጥቅሱ እንዲህ ይ ላል "፤ ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።"
(1ኛ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2:1)
ልጅቱ በንባቡ ግራ ገባት እንደምንም አንብባ ስትጨርስ ካህኑ ፈጠን አሉና '' ሐና ሳሙኤል እናት ቀንድ አላት ማለት ነው ?'' ሲሉ ጠየቋት እሷም ግራ መጋባቷን ለመደበቅ እየሞከረች '' አትሊስት '' ይሔ እንኳን ይተረጎማል አለች
➮ምንጭ ፦ ምጥን ቅመም ክፍል 3