2022-08-19 12:37:51
ደብረ ታቦር (ቡኄ)
ደብርየሚለው ቃል የግእዝ ቃል ሲሆን ተራራ ማለት ነው ፤ ታቦር ደግሞ የተራራው ስም ነው።የታቦር ተራራ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ተራራ ነው።ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፊሊጶስ ቄሳርያ ለደቀመዛሙርቱ "ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?" ብሎ ጠይቋቸው ነበር።እነርሱም "አንዳንዶች ከእናቱ ማህፀን ጀምሮ ቅዱስ ነውና ኤርሚያስ ነው ይሉሀል፤ አንዳንዶቹ ድንቅ የሆነ ልደትህንና የምታጠምቀውን አዲስ ጥምቀት አይተው መጥምቀ ዮሐንስ ነው ይሉሀል፤ ሌሎች ደግሞ ለአባቶችህ ቤት ያለህን ቅናት አይተው ኤልያስ ነው ይሉሀል" እያሉ መልሰውለት ነበር። ጌታችንም መልሶ፦ "እናንተስ ማን ትሉኛላችው?" ብሎ ጠየቃቸው። ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስም "አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ነህ" ብሎ መልሷል። ጌታም "የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ በሰማይ ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይሄንን አልገለጠልህምና ብፁህ ነህ" ብሎታል።(ማቴ16)
ከዚህም በኃላ የሚደርስበትን መከራ ሁሉ ይነግራቸው ጀመር በዕለተ አርብ መገረፉን መሰቀሉን መሞቱን እንዲሁም ደግሞ በሶስተኛ ቀን ከሙታን ተለይቶ እንደሚነሳ ሲነግራቸው ሰይጣን በቅዱስ ጴጥሮስ አንደበት አድሮ እንዳያደርገው እንዳይሆን ይከራከረው ነበር ። ጌታችንም ይገስጸዋል ወደ ምድር የመጣው የገባውን ቃል ሊፈጽም ነውና።(ማቴ 16)
ይህ በሆነ በሰባተኛው ቀን ዘጠኙን በእግረ ደብር ትቶ ሦስቱን ደቀመዛሙርቱን ማለትም ጴጥሮስ ፣ዮሐንስ እና ያዕቆብን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ወጣ።እንዲሁም ሙሴ ና ኤልያስንም አመጣቸው ። በዚያም ክብረ መንግስቱ፤ ብርሃነ መለኮቱን ገለጠላቸው።ጴጥሮስም ለጌታ አንተ ብትወድስ አንዱን ላንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ ሶስት ጎጆ ሠርተን በዚሁ እንኑር አለው።ይህን ሲናገር ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው ። ወዲያውም "ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ወሎቱ ስምዕዎ'' በእሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እሱን ስሙት"የሚል ድምጽ ከሰማይ ተሰምቷል።እነ ጴጥሮስ ደንግጠው ወደቁ ''ተንሥኡ ወኢትፍርሁ'' ተነሱ አትፍሩ ብሎ አንስቷቸዋል።ከርእሰ ደብር ሲወርድ ያዩትን የሰሙትን እስከ ትንሣኤው ለማንም እንዳይናገሩ አዟቸዋል።(ማቴ17:3-9)
ምሥጢረ መንግስቱን ስለምን በታቦር ተራራ አደረገው?
ብዙ ተራሮች እያሉ ስለምን ታቦር ተራራን መረጠ ቢሉ ትንቢቱ እና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ ነው።
ትንቢቱ:- "
ታቦርና አርሞንየም በስምህ አምነው በተደረገላቸው ነገር ደስተኛ ይላቸዋል፤ስምህን ያመሰግናሉ፤ለስምህም ምስጋና ያቀርባሉ።" መዝ 88:12
ምሳሌውም:-
ስለምን ሦስቱ ሐዋርያትን ብቻ ይዞ ወጣ?ስለምን ዘጠኙን ሐዋርያት ከእግረ ደብር ትቶ ሦስቱን ብቻ ጴጥሮስ ፣ዮሐንስና ያዕቆብን ይዞዋቸው ወደ ተራራው ወጣ?
በይሁዳ ምክንያት ነው።ኀጥእ ሰው የእግዘብሔርን ክብር እንዳያይ ያርቁታል እንዲል(ኢሳ.26:13)በዚያን ጊዜ ይሁዳ ከሐዋርያት መካከል ነበርና ያንንም የብርሃነ መለኮት ምሥጢር ማየት አልተገባውም ነበርና እሱን ብቻውን ትቶት ቢሄድ "ከምሥጢሩ ቢለየኝ ሞትን አሰብኩበት" እንዳይል ከእሱ ጋ ዘጠኙን ከዛው ትቷቸው ሄዷል።
➮ ሦስቱ ሐዋርያት የምሥጢር ሐዋርያት ናቸውና።
➮ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችን እሞታለው እሰቀላለው ባለ ጊዜ አይሁንብህ ብሎት ነበርና አብ በሰማይ እርሱን ልጄን ስሙት ብሎ ሲመሰክርለት ይህ ላንተ አይገባም አትበሉት አትቃወሙትእርሱ የሚላችሁን ስሙ ሲላቸው ነው
➮ ቅዱስ ጴጥሮስ የእግዚአብሔር ወልድ የባሕርይ ልጅነቱን መስክሮ ነበርና እግዚአብሔር አብም ሲመሰክርለት እንዲሰማ ወደ ተራራው ወስዶታል።
➮ ሦስቱም ለፍቅሩ ይሳሱ ነበርና ቅዱስ ጴጥሮስ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሳ አትሙት አትሰቀል ብሎታልና፤ቅዱስ ዮሐንስም በወንጌል "የጌታ ወዳጅ" ተብሎ ተጽፏልና፤ ቅዱስ ያዕቆብ ይኸዎም "እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችው?"(ማቴ 20:20) አዎ በማለት በሄሮድስ አግሪጳ ሰማዕት ሆኖ መሞቱ ማረጋገጫ ነው።
ኤልያስና ሙሴን ለምን አመጣቸው?ሙሴ እግዚአብሔር በሚያናግርበት ጊዜ እንዲህ ብሎት ነበር "በአንተ ዘንድ ባለሟልነት ማግኘቴ እውነት ከሆነስ ፊት ለፊት ተገልጸህልኝ ልይህና በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘቴን ልወቅ።" እግዚአብሔርም "ጀርባዬን ታያልህ ፊቴን ግን አታይም" ብሎት ነበርና ከብሔረ ሙታን አምጥቶ አሳይቶታል።
➣ ጌታች ነቢዩ ኤልያስን"በኃለኛው ዘመን ምስክር ትሆነኛለህ" ብሎት ነበርና ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶታል ታያለህ የተባለው ሙሴ አይቷል ትመሰክራለህ የተባለው ኤልያስም ጌታችን አምላከ ኤልያስ እንደሆነ መስክሮለታል።
➣ ጌታች በፊሊጶስ ቄሳር ሰዎች ማን እንደሚሉት በጠየቀ ጊዜ አንዳንዶች ሙሴ አንዳንዶች ኤልያስ ብለው ነበርና አምላከ ሙሴ አምላከ ኤልያስ እንደሆነ ሊያሳያቸው አምጥቷቸዋል።
➣ አይሁድ ፈሪሳውያን ጌታችንን እንደ ሕግ ተላላፊ አድርገውት ነርና ሕግን የሰራው ሙሴን ና ለሕግ ቀናተኛው ኤልያስን በማምጣት ሕግ አለማፍረሱን አረጋግጦላቸዋል።
➣ አምላካችን እግዚአብሔር በሙታንና በሕያዋን ላይ ስልጣን መኖሩን ለማጠየቅ ሙሴን ከብሔረ ሙታን ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቷቸዋል።
ፍጻሜው ግን
1,
ታቦር ተራራ የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ ነውተራራን በብዙ ችግር እንደሚወጡት መንግስተ ሰማያትም በብዙ ድካም እንደሚገቡባት ለመናገር
➣ በታቦር ከብሉይ ኪዳን ነቢያትና ከሐዲስ ኪዳን ሐዋርያት እንደተገኙ መንግስተ ሰማያት ነቢያትም ሐዋርያትም በአንድ ላይ ይወርሷታልና።
➣ በታቦር ተራራ ሞተው ከተቀበሩት ሙሴ በብሔረ ሕያዋን ከሚኖሩ ኤልያስ እንደተገኙባት በመንግስተ ሰማያትም በሞተ ሥጋ የተለዩ ሕያው ሆነው እንደ ኤልያስ ፣ እንደ ሄኖክ የኖሩትም በአንድ ላይ ይገቡባታልና
2. ታቦር የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው።
በብሉይ ኪዳን የክርስቶስን መገለጥ የተናገሩ ነቢያት በሐዲስ ኪዳን የተገለጠውን የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅነት የሰበኩ ሐዋርያት በአንድ ላይ የተገኙባትና ያመሰገኑባት ናትና።በየዓመት ውጥስ ነሐሴ 13 ቀን ቤተክርስቲያናችን የምታከብረው ከዘጠኙ ዐበይት የጌታችን የመድኃኒታችን በዓላት አንዱ የሆነው የደብረ ታቦር በዓል የዚህ ታሪክ መታሰቢያ ነው።በዚህም ዕለት ሕፃናት ጅራፋቸውን ገምደው ያስጮሀሉ። ይኸውም ጅራፍ ሲጮህ እንደሚያስደነግጥ ሁሉ ከጌታ ጋር የነበሩ ሦስቱ ሐዋርያት አብ በደመና ሆኖ ሲናገር የመደንገጣቸው የመውደቃቸው ምሳሌ አንድም የጅራፉ ድምጽ ከሰማይ የተሰማው የእግዚአብሔር አብ ድምጽ ምሳሌ እንዲሁም ሙልሙል መጋገሪ(መሰጠቱ) ችቦ የመብራቱ በዚያን ጊዜ የሚጠብቁ እረኞች የመለኮትን ብርሃን ሲበራ ገና ያልመሸ መስሏቸው በዚያው ሲቆዮ ቤተሰቦቻቸው ችቦ አብርተው እንዲሁም ሙልሙል ዳቦ ይዘው ሊፈልጓቸው የመውጣታቸው ምሳሌ።
➣ አዘጋጅ ፦ መሠረት ዳኜ
#ዐምደ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህረትቤት
https://t.me/Amde_Tewahedo_SS
215 views09:37