Get Mystery Box with random crypto!

GRACE FAMILY

የቴሌግራም ቻናል አርማ familyofgrace1 — GRACE FAMILY G
የቴሌግራም ቻናል አርማ familyofgrace1 — GRACE FAMILY
የሰርጥ አድራሻ: @familyofgrace1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 307
የሰርጥ መግለጫ

CHRISTIAN EVANGELICAL MOVEMENT
#YOUTH_4_CHRIST
በዚህ ቻናል
#Christian_radio_program
#sermons
#praise_hour
To any comment
@its_written

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-01-07 18:19:28 በዓለ ልደቱ ለእግዚእነ

ዛሬ ይኸን ቃል እንደ ገና አነበብሁ። “እነሆ የመረጥሁት ብላቴናዬ፥ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ለአሕዛብ ያወራል። አይከራከርም፥ አይጮኽምም፥ ድምፁንም በአደባባይ የሚሰማ የለም። ፍርድን ድል ለመንሣት እስኪያወጣ፥ የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፥ የሚጤስን የጥዋፍ ክርም አያጠፋም። አሕዛብም በስሙ ተስፋ ያደርጋሉ” (ኢሳ. 42፥1-4)።
.

እንደምታውቁት፥ በኀጢአት ስንዋከብ ኖረናል። …

በሰው ልጆች መካከል የሚገማሸሩና ለትከሻ ቀርቶ ለጆሮ የሚከብዱ ሰቀቀናም የጥቃት፥ የበደል፥ የግፍና የርኵሰት ሸክሞችን መጥቀስ ይቻላል። ነገር ግን፥ የኾነውን ኹሉ ትተን፥ እኛ የምናውቀውን እንኳ መተረኩ ያደክማል። ዋናውን ጕዳይ ግን ዘልለነው አንኼድም፤ ከዚህ ኹሉ የመንኰታኰት አዘቅት ውስጥ ወርውሮ የዶለን ምንድን ነው? ኀጢአት ነው። በመተላለፍ ጦስና በዐመፃችን መታለል የተሰባበርን እንክልካዮች ኾነናል፤ በእግዚአብሔር መልክ የተሠራንበት ዐላማ ደምቆ እንዳያበራ በውድቀት ጦስ ተዳፍነን የምንጤስ ሻማዎች ነበርን። ሕግ የተሰጠውም ኾነ ሕግን በነቢይ ያልተቀበለው አረማዊ “ኹሉ ከኀጢአት በታች እንደ ኾኑ” በአንድነትና በይፋ ተከስሰዋል (ሮሜ 3፥9)። ማን ተርፏል?
.

የሕይወታችን ቅስም በዘላለም ብርታት እንዲታደስ ቤዝዎታዊ ትድግና አስፈልጎናል፤ እንደ ገና እንድንቆምና በብርሃኑም ብርሃንን እንድናይ ስለ እኛ ኾኖ የሚፈስ የሕይወትን ምንጭ ያስፈልገናል። ውርደታችን ጥልቅ ስለ ኾነ አዳኛችን ምርጥ መኾን አለበት። በብርቱ ስለ ተሰበርን ድንቀኛ በኾነ መንገድ መጠገን አስፈልጎናል። ይህን እውን ለማድረግም እግዚአብሔር ምርጡን ብላቴናውን አዘጋጅቶ ወደ ዓለም ልኮታል። “እኛም አይተናል፤ አባትም ልጁን የዓለም መድኀኒት ሊኾን እንደ ላከው እንመሰክራለን” (1ዮሐ. 4፥14)።
.

እግዚአብሔር ፍጥረት ኹሉ እንዲመለከትለት የሚፈልገው እውነት አለው። አስቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ በኋላም በሐዋርያው ማቴዎስ አማካይነት ትኵረታችንን በመቀስቀስ ዓለም ኹሉ ወደ ምርጡ ብላቴና እንዲመለከት ይጣራል። መሲሑ ከእልፍ አቻዎቹ መካከል የተገኘ አለቃ አይደለም፤ ብቸኛው ምርጥ ነው። ወደር የለሽ አንድያ ነው፤ አንድዬ ነው። እግዚአብሔር “ምርጤ” ብሎ ይጠራዋል። ለእኛም ዋጋ የማይተመንለት ውድ-ብርቅ-ድንቅ ዕሴታችን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኾነ።
.

ምርጡ መሲሕ ደግሞ፥ ሸክማቸው የከበደባቸው ሰዎች ወደ እርሱ እንዲመጡና እንዲያሳርፋቸው “በመንፈስ ድኾች” ለኾኑ ኹሉ በግልጽና በይፋ ጥሪውን አቅርቧል። ጥሪውም፥ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ኹሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ” (ማቴ. 11፥28) የሚል ነበር። “ተወለደ” ማለትን ስናስብና ስናከብር ይኸን እያሰላሰልን ነው። የዓለሙ ቤዛ ተወለደ። ሲወለድ ለቤዛነት ይሰቀል ዘንድ ነው። ሲሰቀልም እኛን ለማጽደቅና ለመሻር በትንሣኤ ክብር ይነሣ ዘንድ ነው። ትንሣኤውው ዳግመኛ መገለጡን ያረጋግጣል። እነሆ በቶሎ ይመጣል።
.

“ቤዛ ኵሉ ዓለም ዮም ተወልደ” እንደምንል ኹሉ “እግዚእ ኵሉ ዓለም ይመጽእ ካዕበ” እንለለን።
.

መልካም በዓል።
ሰለሞን አበበ
270 viewsAbrahamggrace, 15:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 10:56:06 ★*゚*☆*゚*★*゚*☆*゚*★
゚*☆*゚ ゜゚*☆*゚ ゜゚*☆*゚ ゜゚*☆*゚
┊ ┊ ┊ ┊ ┊ ┊
┊ ┊ ┊ ┊ ˚✩ ⋆。˚ ✩
┊ ┊ ┊ ✫
┊ ┊ ✩
┊ ⊹ ✯
ዓለም ላይ ያሉ ሕጻናት መኖርን ተስፋ አድርገው ይወለዳሉ። ኢየሱስ ብቻ ግን ለመሞት ተወለደ።
236 viewsAbrahamggrace, 07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 20:11:55 GRACE FAMILY CHRISTIAN EVANGELICAL MOVEMENT #YOUTH_4_CHRIST በዚህ ቻናል #Motivational_program #Christian_radio_program #sermons #praise_hour To any comment @abrahamggrace follow on instagram @its_written https://t.me/familyofgrace1
272 viewsAbrahamggrace, 17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 20:11:29 GRACE FAMILY
CHRISTIAN EVANGELICAL MOVEMENT
#YOUTH_4_CHRIST
በዚህ ቻናል
#Motivational_program
#Christian_radio_program
#sermons
#praise_hour

To any comment
@abrahamggrace follow on instagram
@its_written
https://t.me/familyofgrace1
350 viewsAbrahamggrace, 17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 19:05:10 "If you are fighting sin, you are alive. Take heart! But if sin holds sway unopposed, you are dead no matter how lively this sin makes you feel. Take heart, embattled Saint! “ John Owen
220 viewsAbrahamggrace, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 19:05:10 “አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም ኃይልህ ውደድ።”
— ዘዳግም 6፥5
“And thou shalt love the LORD thy God with all thine heart, and with all thy soul, and with all thy might.”
— Deuteronomy 6፥5 (KJV)

Deuteronomy 6:5. Thou shalt love the Lord thy God with all thy heart — And is this only an external commandment? Can any then say that the Sinai covenant was merely external? With all thy heart — It is not only the external action, but the internal affection of the mind that God requires; an affection which influences all our actions, in secret as well as in public. We must love him,

1st, #With #a #sincere #love; not in words and in tongue only; saying that we love him, when our hearts are not with him; but inwardly, and in truth, delighting ourselves with him.
2nd, #With #a #strong #love; the heart must be carried out toward him, with great ardour and fervency of affection.
3rd, #With #a #superlative #love; we must love God above any creature whatsoever, and love nothing besides him, but what we love for him, and in subordination to him.
4th, #With #an #intelligent #love, or with all our understanding, as it is explained Mark 12:33 : we must know him, and therefore love him, as those that see good reason for loving him. 5th, With an entire and undivided heart, the whole stream of our affections running toward him, and being united in his love. O that this love of God may be shed abroad in our hearts!r
215 viewsAbrahamggrace, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 19:05:10 “ኃጢአት ግን ምክንያት አግኝቶ ምኞትን ሁሉ በትእዛዝ ሠራብኝ”
— ሮሜ 7፥8
188 viewsAbrahamggrace, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-14 01:50:10
256 viewsAbrahamggrace, 22:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-12 20:10:06 ምስጋና...

"I need a reason to sing" was a line I heard as a kid in a song. ክርስቲያን ስለመዘመርያ ሰበብ በእኛም ሀገር የሚጠቅሰውን ስናይ ምስጋና የፀሎት መክፈቻና ልዩ ለምንላቸው ትልልቅ ስኬቶች የምንከፍለው እዳ ወድያ እምብዛም የገባን ነገር አለመሆኑ ይታያል። 

"What can miserable Christians sing?"was an offensively true line I read somewhere. I hated how I related to it. Despite the misery in the world a Christian must fight for joy in God. And the joy of the Lord is our strength.

ስለመዝሙር ከተነሳ ክርስቲያን የሚዘምርበት ምክኒያት እልፍ ነው። መዝሙራችን የህይወታችን ነፀብራቅ ነውና ስለምድራዊ ኮተት ብቻ ካዜምን ምድራዊ ምቾት ማጣት ምስጋናችንን ይዘርፈዋል። በእርግጥ ስለ ለጋስ ስጦታውና መግቦቱ የሚያወሱ መዝሙሮች ሚና እንዳላቸው በቃሉ እናያለን።

".. ያልተቀበልኸው የራስህ የሆነ ነገር ምን አለ? .... አሁንስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ አግኝታችኋል... (1ኛ ቆሮ 4:7) የምንፈልገው ነገር ሁሉ ባይኖረንም እግዚአብሔር ለመረጠልን ህይወት የሚያስፈልገን ነገር ሁሉ ተሰጥቶናል። 

Everything we own, every friend, family, every pastor or significant person in your life has been a gift of God to you. You might think you are just likable because of your personality. Where do you think you got that from? Cant you see that God can take it all away in a heart beat ?

You might think you own stuff and take care of your health because you work hard to earn money but where do you think your energy , skill and creativity come from? Do you realize that God can just deprive you of sleep and that alone is enough to exhaust you enough to end your life let alone your job?

Our lives are filled with common grace. ለሚረግሙት፣ ለሚሰድቡት፣ ህልውናውን ለሚክዱት፣ በስሙ ምለው ለሚያጭበረብሩትም ሁሉ ከቸርነቱ እስትንፋስን ይቀጥላል፣ ፀሀይን ያወጣል። ቤቲ ተዘራ ስትዘምር
"ቸር ባይሆን ባለምህረት
አንዷ ነበርኩ ከሚጠፉት" እንዳለችው።

ውለታውን እየቆጠርን ማመስገን ስንጀምር ከህይወት ያጣነውን ነገር እያሰብን መነጫነጭ እንቀንሳለው። ደስታና እርካታን ፍለጋ የሚዞር ሰው ደስታ ይገባኛል፣ ከእግዚአብሔር በጎ እንጂ ክፉን አልቀበልም ብሎ የሚያምፅ ፀጋ ያልገባው ትዕቢተኛና ፈጣሪን በከንቱ ለማስገደድ የሚጥር ተላላ ነው።

 ከራዕይ 5:9 ላይ “..ምክንያቱም ታርደሃል" የሚለው የመላዕክት መዝሙር ሸለቆውንም ተራራውንም የሚያሳልፍ ፋሽን የማያልፍበት መዝሙር ነው። ሀጥያት ያላወቀው ለኛ ሀጥያት ታርዷል። ሰንበት በመጣ ቁጥር ትንሳዔውን እያሰብን እልል እንበል..መክፈል የማንችለው ዕዳ የተሻረልን ፣ ያልለፋንበት ፅድቅ የተቆጠረልን ፣ የማንረባ ሳለን እግዚአብሔር በልጁ የተወዳጀን ሁሉ የሁሌ መዝሙር አለን።
246 viewsAbrahamggrace, 17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-05 13:26:08
269 viewsAbrahamggrace, 10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ