Get Mystery Box with random crypto!

GRACE FAMILY

የቴሌግራም ቻናል አርማ familyofgrace1 — GRACE FAMILY G
የቴሌግራም ቻናል አርማ familyofgrace1 — GRACE FAMILY
የሰርጥ አድራሻ: @familyofgrace1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 307
የሰርጥ መግለጫ

CHRISTIAN EVANGELICAL MOVEMENT
#YOUTH_4_CHRIST
በዚህ ቻናል
#Christian_radio_program
#sermons
#praise_hour
To any comment
@its_written

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-07 09:24:01 ኑዛዜ

አቤቱ ጌታዬ ሆይ በጣም ደከምኩኝ ከኅጢአት ጋር ግብግብ አዛለኝ እምነቴም ሲፈተን ተሰማኝ ውስጤ ሰላም በማጣቱ ተንኮታኩቻለው ድሮ የነበረኝ ግለት አሁን ላይ የት እንደገባ ግራ ገብቶኛል

ዳዊት እንደፀለየው "የማዳንህን ደስታ መልስልኝ" ብዬ እኔም እቃትታለው ያኑን ግለት በራሴ ልመልሰው እንዲሁ እጣጣራለው ግን ጌታ ሆይ ፈፅሞ አልቻልኩም አው ጌታዬ ሆይ በራሴ እንደማልችል በደምብ ተረድቼአለው

ደሞስ ክርስትናስ እኔ አልችልም ማለት አይደለምን? ምርኩዜ ሆይ ለመቆም ዝያለውና እባክህን በምህረትህ ድገፈኝ ወናነት ሲሰማኝ በሀልወትህ ሙላኝ ባዶነቴን ምትሞላልኝ ብቸኛ መድህኔ አንተ ነህና ዝም አትበለኝ

ደሬ እንደዘመረው አክሊሌን በደምህ እንድሽሸገው እርዳኝ የቆሰለው ልቤን በቁስልህ አክምልኝ የተዋረደን ልብ ስጠኝ ጉልበቶቼን ከዙፋንህ ደጆች ጋር አጣብቅልኝ ሌላ ሌላ እንዳላይ ለአይኖቼ ልጓም አበጅላቸው

ትምክህቴ ሆይ እመካብሀለው ፈፅሞ እንደማትጥለኝ አስረግጬ አውቃለው ግን ዝም ያልከኝ ሲመስለኝ ልቤ ይጨነቃልና በማስተዋል እንድመላለስ በእርጋታ መቀመጥ እንድችል አቤቱ ጌታዬ እርዳኝ
33 viewsAbrahamggrace, 06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 07:37:59 ክረምቱ መጥቶ ወደ ሰማይ ሽቅብ አንጋጥቼ ስመለከት የጠቆረው ዳመና ልቤን ያስታውሰኛል ጭጋጉንም ሳይ ኅጢአት ያጠለሸው ልቤ ፊቴ ላይ ድቅን ይላል ከዛ ደግሞ እርጥበቱ ሞልቶ የዝናብ ነጠብጣቦች ሲወርዱ በንስሀ ልብ ያፈሰስኳቸውው እንባዎቼ ትዝ ይሉኛል

ለጥቆም ዝናቡ ሲያበቃ የጠቆረው ዳመና ቀለል ብሎ ሳየው ከንስሀ በኃላ የሚሰማኝን እረፍት ያስታውሰኛል ከሰዓታት በኋላ ግን መልሶ ሰማዩም ይጠቁራል የእኔ ልብም እንዲሁ።

በዚህ የማያልቅ ዑደት ውስጥ ኅጢአቴ ደጋግሞ በብርድ አንዘፈዘፈኝ ግን የሚያሞቀኝ አንድ ፅኑ ተስፋ አለኝ በዚህ ውጥንቅጥቅ ውስጥ እንኳን አቅንቶ የሚያቆመኝ። "እሄዳለው ወደዛች ሀገር ወደ በጉ ከተማ" የሚል ፅኑ ተስፋ

ብርድም ሙቀትም ወደ ሌለበት ክርስቶስ ብቻ ወደሚያበራበት ሀገር በእሱ ወደሚደምቀበት ደመና እና ጭጋግ ክረምት እና በጋ ቀን እና ማታ ፍፁም ወደ ሌለበት ወደ በጉ ከተማ ልሄድ እጅግ ናፍቄአለው በቃ የኅጢአት ደመና ልቤ ላይ አይደምንም እንዴት ደስ ይላል!

Macarthur አንዴ እንዲህ ብሎ ነበር "መንግስተ ሰማይን ሳስብ የሚያጓጓኝ በወርቅ የተለበጡት በእንቁ የተዋቡት መንገዶች ሳይሆኑ የኅጢአት አለመኖር ነው" የእኔም ጉጉት ይሄ ነው ኢየሱስ ቶሎ ና
38 viewsAbrahamggrace, 04:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 21:13:21 ጌታ ለአገልግሎት ሲጠራኝ ጭንቅ የሆነብኝ ምንም አልነበረም የእናቴ ነገር እንጂ። በጣም ነበር የሷ ጉዳይ የከበደኝ... በመጨረሻም እንዲህ አልኩት "ታስታውሳለህ ያኔ መስቀል ላይ ሳለህ የእናትህ ጉዳይ ግድ ብሎህ ለዮሐንስ አደራ ስትሰጠው? አሁን አንተ መስቀል ላይ አይደለህም። እኔ ለማገልገል እወጣለሁ። እባክህ የእናቴን ነገር አደራ።"


ወንጌላዊ ያሬድ ጥላሁን (paraphrased)
150 viewsAbrahamggrace, 18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 20:32:08
191 viewsAbrahamggrace, 17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-05 21:13:47 Imagine how its gonna be so beautiful ቸርቾቻችን ውስጥ ስብሀት ለአምላክ ብንዘምር ኖሮ?
256 viewsAbrahamggrace, 18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-11 22:50:16 "መርሳት እና ማስታወስ"
.
.
.
'ጠቅላይ ሚኒስትሩ' ሲባል ምን ትዝ ይለናል? ንግግራቸው? ፈገግታቸው? አመራራቸው? ሰላምታቸው? ወይስ ምናቸው? የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንዳ ሞዲ ትዝ አይሏችሁም መቼስ።
አትሌት ኃይሌ ገ/ ስላሴ ሲባልስ ምን ትዝ ይለናል ሩጫው? ዝናው? ሃብቱ? ሆቴሉ? ሜዳሊያው? ሳቁ? ንግግሩ? ወይስ
"ዌል እንግዲህ?" ሁ ?
እንዲህ የሚባል ኢትዮጵያዊ አትሌት አላወቅም የሚለኝ ይኖራል ?

ስለ ሁለቱም የምናወቀው የተወሰነ ነገር በመኖሩ ... ፈጥኖ ወደ ጭንቅላታችን የሚመጣ ማንነት አላቸው በትክክል ይግለፃቸውም አይግለፃቸውም።
እግዚአብሔር ሲባል ምን ትዝ ይለናል? ሰማይ? ምድር? ጨረቃ? ፀሐይ? ሰው?ቤተክርስቲያን ?
በምኑ ይሆን የምናስታውሰው?
የሆነ ጊዜ እንዲህ አለ ...
"ከተሰማሩ በኋላ ጠገቡ በጠገቡም ጊዜ ልባቸው ታበየ ስለዚህ … ረሱኝ"
እነዛ ረሺዎች " እግዚአብሔር" ሲባሉ
ምን? ማን? የቱ? ብለው ሌላ ከስሙ ሌላ ማስታወሻ ምልክትን ይሻሉ ፡፡
ሌላ ቦታ ላይ ደግሞ "ቆንጆ ጌጧን ሙሽራ ልብሷን (ቬሎዋን አለ አንዱ ሰባኪ በደንብ ሲያስረዳ) ትረሳለች? ህዝቤ ግን ለማይቆጠሩ ወራት ረሳኝ"አለ
የጥር ማለቂያ ላይ ስለ ቬሎ ብናወራ ሩቅ አይሆንብንም
ቬሎ ምንድነው ? ማነው ያመጣው ? ሴት ሙሽራ ሁሉ ቬሎ ትልበስ ያለው ማነው? ለመቆም አይመች ለመቀመጥ ... ለመነካት ተፈርተሽ ለመታቀፍ እርቀሽ ... ብቻ መቼም ይምጣ ሙሽራን ያለ ቬሎ ማሰብ ይከብዳል ወይም ሌላ የሙሽራ ልብስ

እነዚህም "እግዚአብሔር" ሲባሉ
"ማን ነበር?" ብለው ይጠይቃሉ "ያ እንኳ ከግብፅ ያወጣን አምላክ" ሲባሉም የሚያስታውሱት አይመስለኝም
"ጥ ጥ ይቅርታ አላስታወስነውም" ይላሉ
"መናን ያበላን" እ እ የሆድ ጉዳይ ላይ በጥቂቱ ሊያስታውሱት ይሞክራሉ መልሰው ይረሱታል፡፡
እርሱ ግን ስለ እነርሱ ሲጠየቅ
"ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ" ይላል ደግሞም "ሴት ከማህፀኗ የወጣውን ትረሳለች እስከማታስታውሰውስ ትጨክናለች አዎ ትረሳ ይና እኔ ግ አልረሳሽም በእጄ መዳፍ ላይ ቀርጬሻለሁ" ነው መልሱ ።

የጉዳዩ እጅግ አስገራሚነት እዚህ ላይ ነው ይህ ትንሹ ሰው በዚህች ሚጢጢ ጭንቅላቱ ያቅሙን ያህል ጉዳይ አጭቆ ለማስታወስ እየጣረ ... ፎርሙላ እየሸመደደ ፤ የታክሲ መልስ እየተቀበለ፤ ቁርስ ምሳ እራቱን ሳይረሳ ፤ ከረቫት ማሰሩን ሳይረሳ ፤ ኩል መቀባቷን ሳትረሳ … እግዚአብሄርን ያህል ታላቅ እና ትልቅ አምላክ ሲረሳ፡፡

እሱኮ... ዩኒቨርስን ለአፍታ ሳይዛባ እየተቆጣጠረ ፤ የምድርን እና የሰማይን ፍጥረታት ስርአት አስይዞ እያስወጣ እያስገባ ፤ ለፀሀይ ቀንን ፤ ለጨረቃ ከዋክብት ለሊትን መድቦ ፤ ምድርን መስርቶ ፤ መስፈሪያዋን ወስኖ ፤ ለባህር ማእበል ገደብን አበጅቶ ፤ ዝናብን እያዘነበ ከዋክብተትን እያሰረ ሲፈታ … ምኑ ቅጡ! በዚህ ሁሉ ስራ በዚህ ሁሉ ፋታ ማጣት ትንሹን ሰው ማሰቡ አለመርሳቱ፤ "ረሳኋችሁ" ቢል እኮ በቂ ምክንያት አለው፡፡
"ለፈረስ ጉልበቱን ስሰጥ ፤ አንገቱን ጋማ ሳለብስ" ሊል ይችላል
"የሚያግዘኝ እንደሁ የለ ፅንስን በማህፀን ስገጣጥም" ረሳኋችኁ ቢል ያሳምናል፡፡
"እናንተ ደግሞ እነማን ናችሁ? መቼም በምድር ላይ ስንት እና ስንት ቢልዮን ህዝብ የሚጠጋ ህዝብ ነው የሚርመሰመሰው" ቢል እውነቱን ነው። ሰው ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሄር ግን አንድ ነው ፤ አልረሳንምና አላለም።

እንደ ዳዊት እጠይቃለሁ
"አቤቱ ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው
ትጎበኘውስ ዘንድ የሰው ልጅ ምንድነው?"
ለራሴም እጠይቃለሁ
"ሰው ሆይ እግዚአብሔርን ትረሳ ዘንድ አንተ ማነህ?"
ለአብረሃም እና ለዘሩ ለዘለአለም ምህረቱ ትዝ እያለው ቅዱሱን ኪዳን አሰበ። ቃሉን አሰበ። እውነቱን አሰበ፡፡
ካልካድን በስተቀር የእግዚአብሄርን አስታዋሽነት መፅሐፍ ቅዱስና ታሪክ ይነግሩናል፡፡
በአመፀኛ ትውልድ መካከል የተገኘው አንዱ ኖህ አምላኩን ሰምቶ በሰራው መርከብ ቤተሰቦቹን ካስመለጠ በኋላ ከእግዚአብሔር ቃል ኪዳንን ተቀበለ፡፡
ዳግመኛ በምድር ዘመን ሁሉ መዝራት እና ማጨድ ፤ ብርድና ሙቀት በጋ ክረምት፤ ቀን እና ለሊት እንዳያቋርጥ በልቡ ካሰበ በኋላ ለኖህ አለው፡፡ ቃል ኪዳኔን ከእናንት በኋላ ከሚመጣው ከዘራችሁ ጋ አቆማለሁ አለ፡፡
አዎ አቁሟል፡፡

ዘርቶ የማያጭድ ገበሬ ማን አለ? ክረምትና በጋ ቀንና ለሊትስ መቼ ተቋርጠው ያውቃሉ? እርሱ እግዚአብሄር ቃሉን አይረሳምና።
ከባርነት የወጡ እስራኤላውያን ...
'ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ' ማለቱን ዘንግተው ፤ የራሳቸውንም ቃል ረስተው ጥጃ ሊሰሩ ወርቆቻቸውን ከጆሯቸው ሲያወልቁ ግን ገና 40 ቀንና 40 ሌሊት ብቻ ነበር ያለፈው፡፡

"ህጉን እና ስርአቱን ባለመጠበቅ አምላክህ እግዚአብሔርን እንዳትረሳው ተጠንቀቅ" ቢባሉም አነርሱ ግነ ሊያስተውሱት ከቶ አልቻሉም። ከርሱ ይልቅ የግብፅ ዱባና ሽንኩርት ትዝ ይላቸውና ጣእሙም በአፋቸው መአዛው ባፍንጫቸው እየመጣ ምራቅ ያስውጣቸው ነበር ፡፡
እግዚአብሔር ግን እነርሱን ከማጥፋ በፊት ለአባቶቻቸው የማለላውን ባሪያዎቹን አብርሃምንን እና ይስሃቅ ፣ እስራኤልን አስቦ ራራላቸው፡፡ ዳግመኛ ማደሪያውን በመካከላቸው አደረገ። ምክንያቱም ሳሩ ይደርቃል አበባውም ይግፋ የአምላካችን ቃል ግን ለዘለአለም ፀንታ ትኖራለች፡፡

የ Solomon Abebe Gebremedhin "የዱባ ጥጋብ " መፅሐፍ ምርቃት ላይ የቀረበ !

ጽጌሬዳ ጎንፋ
311 viewsAbrahamggrace, 19:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-02 15:21:36 Subscribe
252 viewsAbrahamggrace, 12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-02 15:21:36



ተለቋል!
235 viewsAbrahamggrace, 12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-31 19:40:35
222 viewsAbrahamggrace, 16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 18:43:38 . መላዕክትከላይ ሰማን
Dave & Kingdom Sound
-4:26Min -4.1MB
275 viewsAbrahamggrace, 15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ