Get Mystery Box with random crypto!

❤️ዕፀ ፍህሶ ወዕፀ መአዛ❤️

የቴሌግራም ቻናል አርማ etsemeaza — ❤️ዕፀ ፍህሶ ወዕፀ መአዛ❤️
የቴሌግራም ቻናል አርማ etsemeaza — ❤️ዕፀ ፍህሶ ወዕፀ መአዛ❤️
የሰርጥ አድራሻ: @etsemeaza
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.02K
የሰርጥ መግለጫ

የአባቶች ጥበብ ይተነተንበታል ። 🔰የቀደምት አባቶቻችንን እውቀት እና ጥበብ ሳይበረዝ እንደወረደ ይቀርባል። የአያቶቻችን የእጽዋት ጥበብ ፣ በህይወትዎ ላይ ለሚያጋጥሙ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ፣ ክፉ መናፍስትን እንዴት ማራቅ እንደምንችል🦅፣ የብራና መጽሐፍት እና ጥቅማቸው በዚ ይዳሰሳሉ።
➫የተለያዩ መድሀኒቶችን
➫ለተለያዩ በሽታ መፍትሄ
➫የተለያዩ የብራና መፅሀፍት
@fihsoBot

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-18 18:18:20 እንኳን አደረሳችሁ! <ነሐሴ ፲፫/13>
[በዓለ ደብረ ታቦር ወልደቱ ለሙሴ ወብንያም ወጋልዮን መስተጋድል]

=> የዕለቱ ግጻዌ

ምስባክ ዘነግህ
ደብር ርጉዕ ወደብር ጥሉል።
ለምንት ይትነሥኡ አድባር ርጉዓን።
ደብር ዘሠምሮ እግዚአብሔር የኀድር ውስቴቱ።
ትርጉም፦
የጸና ተራራና የለመለመ ተራራ ነው።
የጸኑ ተራራዎች ለምን ይነሣሉ?
እግዚአብሔር ያድርበት ዘንድ ይህን ተራራ ወደደው።
(መዝ ፷፯ : ፲፭ - ፲፮ /67:15-16)

+ ወንጌል ዘነግህ
የማቴዎስ ወንጌል ፲፯ : ፩ - ፲፬ /17:1-14

ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው።

በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።

እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።

ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን፡— ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ፡ አለ።

እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው፡— በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት፡ የሚል ድምፅ መጣ።

ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር።

ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና፡— ተነሡ አትፍሩም፡ አላቸው።

ዓይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም።

ከተራራውም በወረዱ ጊዜ ኢየሱስ፡— የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያያችሁትን ለማንም አትንገሩ፡ ብሎ አዘዛቸው።

ደቀ መዛሙርቱም፡— እንግዲህ ጻፎች፡— ኤልያስ አስቀድሞ ሊመጣ ይገባዋል ስለ ምን ይላሉ? ብለው ጠየቁት።
፲፩
ኢየሱስም መልሶ፡— ኤልያስማ አስቀድሞ ይመጣል ሁሉንም ያቀናል፤
፲፪
ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ኤልያስ ከዚህ በፊት መጣ፤ የወደዱትንም ሁሉ አደረጉበት እንጂ አላወቁትም፤ እንዲሁም ደግሞ የሰው ልጅ ከእነርሱ መከራ ይቀበል ዘንድ አለው፡ አላቸው።
፲፫
በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ስለ መጥምቁ ስለ ዮሐንስ እንደ ነገራቸው አስተዋሉ።

+ መልእክታት:-
1. ወደ ዕብራውያን ፲፩ : ፳፫ - ፴ /11:23-30
2. ፪ኛ ጴጥሮስ ፩ : ፲፭ -ፍጻሜ /1:15-ፍጻሜ
3. ግብረ ሐዋርያት ፯ : ፵፬ - ፶፩ /7:44-51

✞ ምስባክ ዘቅዳሴ
ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌሥሑ
ወይሴብሑ ለስምከ።
መዝራእትከ ምስለ ኃይል።
ትርጉም፦
ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል።
ስምህንም ያመሰግናሉ።
ክንድህ ከኃይልህ ጋር ነው፤
(መዝ ፹፰ : ፲፪ - ፲፫/88:12-13)

+ ወንጌል ዘቅዳሴ
የሉቃስ ወንጌል ፱ : ፳፰ - ፴፰ /9:28-38
፳፰
ከዚህም ቃል በኋላ ስምንት ቀን ያህል ቈይቶ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ያዕቆብንም ይዞ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ።
፳፱
ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ።

እነሆም፥ ሁለት ሰዎች እነርሱም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር፤
፴፩
በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር።
፴፪
ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ።
፴፫
ከእርሱም ሲለዩ ጴጥሮስ ኢየሱስን። አቤቱ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነውና አንድ ለአንተ አንድም ለሙሴ አንድም ለኤልያስ ሦስት ዳሶች እንሥራ አለው፤ የሚለውንም አያውቅም ነበር።
፴፬
ይህንም ሲናገር ደመና መጣና ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ።
፴፭
ከደመናውም። የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
፴፮
ድምፁም ከመጣ በኋላ ኢየሱስ ብቻውን ሆኖ ተገኘ። እነርሱም ዝም አሉ። ካዩትም ነገር በዚያ ወራት ምንም ለማንም አላወሩም።
፴፯
በነገውም ከተራራ ሲወርዱ ብዙ ሕዝብ ተገናኙት።

✞ ቅዳሴ ~ ዘእግዝእትነ / ዘዲዮስቆሮስ {በዕዝል ዜማ ቀድስ}

በቅዱሱ ተራራ መለኮታዊ ክብሩን ለቅዱሳኑ የገለጸ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ለእኛም ዕውቀቱን ይግለጽልን ጥበቡን ማስተዋሉን ያድለን። በመንግሥቱም ያስበን። የክብርት እናቱ ምልጃም አይለየን።

፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠
498 views15:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 18:26:33 ነሐሴ ፲፪/12
[ቅዱስ ሚካኤል አስተርአዮ ለቈስጠንጢኖስ፥ ወነግሠ ቈስጠንጢኖስ በሮሜ፥ ወ፳ወ፻ ሰማዕታት ማኅበራነ ፋሲለደስ]

የዕለቱ ግጻዌ

❖ ምስባክ ዘነግህ
በቅድመ መላእክቲከ እዜምር ለከ፣
ወእሰግድ ውስተ ጽርሐ መቅደስከ።
ወእገኒ ለስምከ፤
ትርጉም፦
በመላእክት ፊት እዘምርልሃለሁ።
ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤
ስምህንም አመሰግናለሁ።
( መዝ ፻፴፯ : ፩-፪ /137:1-2 )

❖ ወንጌል ዘነግህ
ማቴዎስ ፳፭ : ፴፩-ፍጻሜ /25:31-ፍጻሜ

መልእክታት:-
➊. ፩ኛ ቆሮንቶስ ፱ : ፲፯ - ፍጻሜ /9:17-ፍጻሜ
➋. ይሁዳ ፩ : ፰ - ፲፬ /1:8-14
➌. የሐዋ/ሥራ ፳፬ : ፩ - ፳፪ /24:1-22

+ ምስባክ ዘቅዳሴ
እግዚኦ ኲነኔከ ሀቦ ለንጉሥ።
ጽድቀከኒ ለወልደ ንጉሥ።
ከመ ይኰንኖሙ ለሕዝብከ በጽድቅ።
ትርጉም፦
አቤቱ፥ ፍርድህን ለንጉሥ ስጥ፥
ጽድቅህንም ለንጉሥ ልጅ፥
ሕዝብህን በእውነት ይዳኝ ዘንድ።
(መዝ ፸፩ : ፩ /71:1)

+ ወንጌል ዘቅዳሴ
የማቴዎስ ወንጌል ፳፪ : ፩ - ፲፭ /22:1-15

ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ።

መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች።

የታደሙትንም ወደ ሰርጉ ይጠሩ ዘንድ ባሮቹን ላከ ሊመጡም አልወደዱም።

ደግሞ ሌሎችን ባሮች ልኮ። የታደሙትን። እነሆ፥ ድግሴን አዘጋጀሁ፥ ኮርማዎቼና የሰቡት ከብቶቼ ታርደዋል፥ ሁሉም ተዘጋጅቶአል፤ ወደ ሰርጉ ኑ በሉአቸው አለ።

እነርሱ ግን ቸል ብለው አንዱ ወደ እርሻው፥ ሌላውም ወደ ንግዱ ሄደ፤

የቀሩትም ባሮቹን ይዘው አንገላቱአቸው ገደሉአቸውም።

ንጉሡም ተቈጣ፥ ጭፍሮቹንም ልኮ እነዚያን ገዳዮች አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።

በዚያን ጊዜ ባሮቹን። ሰርጉስ ተዘጋጅቶአል፥ ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤

እንግዲህ ወደ መንገድ መተላለፊያ ሄዳችሁ ያገኛችሁትን ሁሉ ወደ ሰርጉ ጥሩ አለ።

እነዚያም ባሮች ወደ መንገድ ወጥተው ያገኙትን ሁሉ ክፉዎችንም በጎዎችንም ሰበሰቡ፤ የሰርጉንም ቤት ተቀማጮች ሞሉት።
፲፩
ንጉሡም የተቀመጡትን ለማየት በገባ ጊዜ በዚያ የሰርግ ልብስ ያለበሰ አንድ ሰው አየና። ወዳጄ ሆይ፥
፲፪
የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት ወደዚህ ገባህ? አለው እርሱም ዝም አለ።
፲፫
በዚያን ጊዜ ንጉሡ አገልጋዮቹን። እጁንና እግሩን አሥራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል አለ።
፲፬
የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።

+ ቅዳሴ - ዘእግዝእትነ ወይም ዘዮሐንስ አፈወርቅ
507 views15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 12:01:21
• ነሐሴ ፲ (10) •

+ ምስባክ ዘቅዳሴ
ተዘከር ማኅበረከ ዘአቅደምከ ፈጢረ።
ወአድኃንከ በትረ ርስትከ።
ደብረ ጽዮን ዘኃደርከ ውስቴታ።
ትርጒም፦
አስቀድመህ የፈጠርሃትን ማኅበርህን አስብ።
የተቤዠሃትንም የርስትህን በትር።
በርስዋ ያደርህባትን የጽዮንን ተራራ።
[ መዝ ፸፫ ፥ ፪ /73 ፥ 2 ]

+ ወንጌል ዘቅዳሴ
(የሉቃስ ወንጌል ፲፮፥፱-፲፱ / 16፥9-19

እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ።

ከሁሉ በሚያንስ የታመነ በብዙ ደግሞ የታመነ ነው፥ ከሁሉ በሚያንስም የሚያምፅ በብዙ ደግሞ ዓመፀኛ ነው።
፲፩
እንግዲያስ በዓመፃ ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ እውነተኛውን ገንዘብ ማን አደራ ይሰጣችኋል?
፲፪
በሌላ ሰው ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ የእናንተን ማን ይሰጣችኋል?
፲፫
ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል። ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።
፲፬
ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።
፲፭
እንዲህም አላቸው። ራሳችሁን በሰው ፊት የምታጸድቁ እናንተ ናችሁ፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ልባችሁን ያውቃል፤ በሰው ዘንድ የከበረ በእግዚአብሔር ፊት ርኵሰት ነውና።
፲፮
ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ነበሩ፤ ከዚያ ጀምሮ የእግዚአብሔር መንግሥት ይሰበካል፤ ሁሉም ወደ እርስዋ በኃይል ይገቡባታል።
፲፯
ነገር ግን ከሕግ አንዲት ነጥብ ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ሊያልፍ ይቀላል።
፲፰
ሚስቱንም የሚፈታ ሁሉ ሌላይቱንም የሚያገባ ያመነዝራል፥ ከባልዋም የተፈታችውን የሚያገባ ያመነዝራል።

+ ቅዳሴ፦ ዘእግዝእትነ (በግዕዝ ዜማ)
445 views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 21:40:53 ጌራ መዊዕ ጸሎት ያለው አለ?
439 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 11:25:53 “ንዑ ናስተብጽአ ለማርያም

 ኑና ማርያምን እናመስግናት

ነገረ ማርያም (Mariology) በቅድስት ቤተክርስቲያን ሰፊ ትምህርት ሲሆን፤ እመቤታችን በነገረ ድኅነት(soteriology) በነበራት ሱታፌ (ድርሻ) ምክንያት ነገረ ማርያም ከሁሉም ትምህርት ጋር የተያያይዘ ትምህርተ ሃይማኖት ነው። በተለይ በነገረ ሥጋዌ። ለዛሬ ቀዳሚት ሔዋንን እና ዳግሚት ሔዋን እመቤታችንን  በንጽጽር እናያለን።

የጽሑፌ ዓላማ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቀደሙት ቅዱሳን አበው አንደበት እና ትምህርት ማየት ሲሆን፤ ከዚኽ በፊት “ማርያም ማለት” በሚል ጽሑፌ የስሟን ትሩጉ ከመሠረታዊው ትምህርት ጋር ማስነበቤ ይታወሳል።

 ቅዱስ ጳውሎስ በቀዳሚ በቆሮንቶስ መልእክቱ ስለ ጌታችን መድኅኒታችን ሲናገር ይኽውም በቀዳሚው አዳም የሆነብንን ውድቀት፤ መረገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ስላዳነን ሲናገር “ሁለተኛ አዳም” ብሎታል። “አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል። ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና” 1ቆሮር.15:21-22 

በዘፍጥረት ላይ  ቀዳሚ ሔዋን ለሰው ውድቀት ምክንያት እንደሆነች እናነባለን። በመሆኑም ኢየሱስ ክርስቶስ የሁለተኛውን አዳምን ቦታ ከወሰደ ማለትም ሁለተኛ አዳም ከተባለ የሔዋንን ቦታ ማን ወሰደ የሚለው ጥያቄ ይነሳል።

የጥንት ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም  ይህንን ቦታ ትወስዳለች ይላሉ። ቀዳሚት ሔዋን ሰይጣንን አመነች፤ አዳምን ወደ ኃጢአት መራች ። ዳግሚት ሔዋን የመልአኩን ቃል አመነች። አምላክን በመውለድ መድኅኒትን ለዓለም ሰጠች ። ዳግሚት ሔዋን የሚለውን ጽንሰ ሐሳብ የቀደሙት የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት የገለጡበትና ያስተማሩበትን መንገድ በጥቂቱ እንግለጽ።

ሰማዕቱ ጀስቲን (100-165) መ/ክ/ዘ

ድንግል በምትሆን በቀዳሚት ሔዋን (ሔዋንን ከመውለዷ በፊት ማለት ነው)  የእባቡን ምክር ጸንሳ አለመታዘዝና ሞትን አመጣች። ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግሊቱ ሰው ሆነ። በዓለም የነበረውን አለመታዘዝ ወደ ቀዳሚ ክብሩ መለሰችው ይላል። እመቤታችን ተስፋን ተቀበለች። የመልአኩን ቃል በሰማች ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወደ እርሷ መጣ፤ የአርያም ክብር ከበባት፤ ከአንቺ የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ ነው ባላት ጊዜ እንደቃልህ ይሁንልኝ በማለት መለሰችለት። (Dialogue with Trypho, 100, A.D. 160)

ቅዱስ ኤሬኔዎስ (ከ130-201 ዓ.ም)

መናፍቃንን በተቃወሙት ጽኁፉ “ቀዳሚ ሔዋን ባለመታዘዝ ታሰረች (ማእሰረ ሔዋን)። የቀደመው የሔዋን አለመታዘዝ እስር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም  በመታዘዝ ተፈታ(የባርያይቱን መዋረድ አይቷልና እንዳለች) ጸሎተ ማርያም። ሔዋን በሳተው (መልአክ) እባብ ተመርታ ከእግዚአብሔር ፊት ተሰደደች፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ከመልአኩ ጋር በተነጋገረች ጊዜ ለዘላለማዊ ደስታ ማሰርያ ሆነች። ለቃሉም ታዛዥ ሆነች ። ድንግል ማርያም ለቀዳሚት ሔዋን ካሳ ሆነች በሔዋን ምክንያት የሰው ዘር በሞት ማሰሪያ ተይዞ፤ በዳግሚት ሔዋን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም  ምክንያት ዳግም ዳነ። የሔዋን ያለመታዘዝ ሚዛን በተቃራኒው በድንግል ማርያም ተስተካከለ” ይላል (Against Heresies, III.22.4, A.D. 180)

ተርቱልያን (ከ160-220 ዓ.ም›)

ሔዋን ገና ድንግል ሳለች የጠላትን ማጥመጃ ቃል ወደ ጆሮዋ በገባ ጊዜ፤ የሞትን ግድግዳ ገነባ። በዳግሚት ሔዋን (እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም) በእግዚአብሔር ቃል ሕይወት ተመሠረተ። በሰው ዘር የሚተላለፈው ኃጢአት ያለወንድ ዘር በመጽነስ ወደ ድኅነት አመጣችው።  የጠብ ግድግዳ ፈረሰ። ሔዋን አባቡን እንዳመነች እመቤታችን መልአኩን አመነች። ሔዋን የእባቡን ቃል በማሕጸን አልጸነሰችውም፤ ነገር ግን የሐዘን እና ከገነት የመሰደድ ዘር ሆነባት በክፋት የሚጣሉ ልጆችን ወለደች (ቃየን አቤልን መግደሉን ሲያስታውስ)። እመቤታችን በተቃራኒው እስራኤልን የሚያድነውን  ወለደች ። በሥጋ የገዛ ወገኖቹ ግን ሰቀሉት። (The Flesh of Christ, 17)

ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት (213-270 ዓ.ም)

የሔዋንን አለመታዘዝ ሳስብ አለቅሳለሁ፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፍሬ ሳስብ እንደገና እታደሳለሁ። የማይሞተው ወደ እኛ መጣ፤ የማይታይ፡ የማይመረመር፤ ከዘመናት በፊት የብርሃናት ብርሃን የአብ የባህርይ አንድያ ልጁ የእግዚአብሔር ቃል ከእመቤታችን ሥጋን ለብሶ የሰው ዘር ከኃጢአት ፡ከብልየት(ከእርጅና) ያድሰው ዘንድ ዳግማይ አዳም በእመቤታችን እቅፍ ሆነ (Homily Concerning the Holy Mother of God Ever-Virgin, 1)

ቅዱስ ጄሮም

ሞት በሔዋን በኩል መጣ። ነገር ግን ሕይወት በድንግል ማርያም በኩል መጣ (Epistle 22, 21)

ቅዱስ ኤፍሬም (306- 373 ዓ.ም)

በሔዋን የገነት ደጅ ተዘጋ፤ ዳግመኛም በድንግል ማርያም  ተከፈተልን። (ወዳሴ ማርያም ዘሐሙስ)

አውግስጢኖስ (354-430 ዓ.ም)

ጌታ ወንድ ሆኖ መጣ ከዚህ ጀርባ ትልቅ ምስጢር አለ።ሞት በሴቲቱ በኩል ስለገባ ነው ይላል።
 እንግዲህ የቀደሙት ሊቃውንት እመቤታችን በነገረ ድኅነት ውስጥ ከቀዳሚ ሔዋን ጋር በማነጻጸር የተረጎሙበትን በአጭሩ መረዳት ያስፈልጋል። 

@etsemeaza
511 views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 18:02:20 ++ የጾመ ፍልሰታ ፪ኛ [ለክረምት ፱ኛ] እሑድ ++

❖ መዝሙር:- ዛቲ ይእቲ ማርያም ማኅደረ መለኮት እንተ ተሰምየት ሰንበተ ክርስቲያን። በከመ ይቤ ዳዊት በመዝሙር አንሣዕኩ አዕይንትየ መንገለ አድባር። አድባረ ድኁኃን ተሰምየት ዛቲ ይእቲ ቅድስት ድንግል። ተዐቢ እምኲሉ ፍጥረት ኢያውዓያ እሳተ መለኮት።

ትርጉም:- ለክርስቲያን ዕረፍት የተባለች የመለኮት ማደሪያ ማርያም ይህች ናት። ዳዊት በመዝሙር ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ እንደለ። የጸናች ተራራ የተባለች ይህች ድንግል ልዩ ናት። የመለኮት እሳት አላቃጠላትምና ከፍጥረት ሁሉ ትበልጣለች።

#የዕለቱ_ግጻዌ [መልእክታት፣ ምስባክና ወንጌል]

✞ መልእክታት:-
➊. ዕብራውያ ፲፩ : ፰-፲፱ /11:8-19
➋. ፪ኛ ዮሐንስ ፩ : ፩ - ፰ /1 : 1 - 8
➌. የሐዋ/ሥራ ፳፯ : ፴፩ - 38 /27:31-38

ምስባክ
አንሣእኩ አዕይንትየ መንገለ አድባር።
እምአይቴ ይምጻእ ረድኤትየ ።
ረድኤትየሰ እምኀበ እግዚአብሔር።
ትርጉም:-
ዐይኖቹቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ።
ረዳቴ ከወዴት ይምጣ።
ረዳቴ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።
[ መዝ ፻፳ : ፩ /120:1 ]

ተለዋጭ ምስባክ
እስመ ኃረያ እግዚአብሔር ለጽዮን።
ወአብደራ ከመ ትኩኖ ማኅደሮ።
ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም።
ትርጉም:-
እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና።
ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዷልና።
ይኽች ለዘለዓለም ማረፊያዬ ናት።
[ መዝ ፻፴፩ : ፲፫ /131:13 ]

ወንጌል
ሉቃስ ፩ : ፴፱ - ፵፮ (1:39-46)
፴፱
ማርያምም በዚያ ወራት ተነሥታ ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥

ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት።
፵፩
ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥
፵፪
በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች። አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው።
፵፫
የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?
፵፬
እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና።
፵፭
ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት።

✞ ቅዳሴ ~ ዘእግዝትነ ማርያም (ጎሥዓ) በግዕዝ ዜማ

@etsemeaza
525 views15:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 22:01:01 ✣ ለማርያም_ድንግል
✣ ጴጥርቃ እና ~ቴክታ የሚባሉ ሰዎች በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው ይኖሩ ነበር፡፡ እነዚህም በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ደግ ሰዎች ነበሩ፡፡ :: ነገር ግን ልጅ አልነበራቸውምና መካን ነበሩ፡፡
✣ አንድ ቀን ጴጥርቃም ቴክታን እህቴ ሆይ ይህን ሁሉ የሰበሰብነውን ገንዘባችንን ምን እናደርገዋለን ልጅ የለን የሚወርሰን ፤ አንቺም መካን ነሽ እኔም ካንቺ በቀር ሌላ ሴት አላውቅም አላት፡፡ እርሷም ወንድሜ ሆይ አምላከ እስራኤል ለእኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ ብላ ብታሰናብተው እንደዚህ ያለ ነገር እንኳንስ ላደርገው በልቦናዬ እንዳላስበው አምላከ እስራኤል ያውቅብኛል አላት እሷም አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም ትላንትና ማታ በህልሜ ~ነጭ ጥጃ ከማህጸኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ~ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ 7ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ #ጨረቃዋም ~ፀሐይን ስትወልድ አየሁ አለችው::
✣ እርሱም በጠዋት ከህልም ፈቺ ዘንድ ሂዶ የነገረችውን ሁሉ ነገረው፡፡ ያም ህልም ፈቺ እግዚአብሔር በምህረቱ አይቷችኋል በሳህሉ መግቧችኋል 7 አንስት ጥጆች መውለዳቹ 7 ሴቶች ልጆች እና የልጅ ልጆች ትወልዳላቹ ከቤታቹ ሰባተኛይቱ ~ጨረቃ መውለዷ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ ~የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም አለው፡፡
✣ ከዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ~ሄሜን ብለው ስም አወጡላት ፤ ሄሜንም~ዴርዲንን፤ ዴርዴንም ~ቶናን ፤ቶናም ሲካርን፤ ~ሲካርም ሴትናን፤ ~ሴትናም ሄርሜላን ፤ ሄርሜላም ~ሃናን ወለደች:: ከጴጥርቃና ከቴክታ የተወለዱ 67 ወንዶች ልጆች አሉ የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ትውልድ ለመቁጠር ትንቢት አልተነገረላቸውም ሱባኤ አልተቆጠረላቸውምና አልተፃፈም፡፡ ይህቺም ሃና በስርዓት በቅጣት አደገች፡፡ ለአእምሮ ስትበቃ አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግስት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ እያቄም ጋር አጋቧት::
✣ !! እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄም እና ሃና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፤ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ሂደው ሲፀልዩ ሲያዝኑ ዋሉ፡፡ ሃዘናቸው እንዴትስ ነው ቢሉ ፡-
ኢያቄም:-"አቤቱ ጌታዬ ያባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ አትጣለኝ አትናቀኝ ፀሎቴን ስማኝ ፈቃዴን ፈጽምልኝ፤ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የሚሆን የተባረከ ወንድ ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ:፡
✣ ሃናም በበኩሏ "አቤቱ ጌታዬ የአባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ፤ ስማኝ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የምትሆነኝ የተባረከች ሴት ልጅ የማህፀኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለች፡፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት አይታ አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲፀልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ(ውሃ) ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ:: ዘካርያስም እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስእለታችሁን ይቀበልላችሁ ጻህቀ ልቦናችሁን ይፈጽምላችሁ ብሎ አሳረገላቸው።
✣ ከዚያም በኋላ ቅድስት ሃና እና ቅዱስ እያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ራእዩም እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም 7ቱሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ አላት ፤ ወፍ የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባህሪው ነው ፤ ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ማለቱ ፤ የኢያቄምን ( የሰውን) ባህርይ ባህርይ እንዳደረገው እወቅ ሲል ነው ፤ 7ቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባህርይው፤ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩና መንግስቱ ናቸው፡፡
✣ ሃናም እኔም አየሁ አለችው፤ ምን አየሽ ቢላት፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕጸኔ ስትተኛ አየሁ አለችው:: ርግብ የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት:ነጭነቱ ንጽህናዋ : ቅድስናዋ ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ ማለቷ ብስራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መጽነሷን ነው፡፡ ይህንኑም ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው::
✣ እነሱም እንዲ ያለ ራዕይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም፤ ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሄዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሏት ብሎ ያበሰረ አምላክ ለኛስ ይልክልን የለምን? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ 7ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሐሴ ሰባት በሰባተኛው ቀን ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹህ ብሎ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለሃና ነገራት በፈቃደ እግዚአብሔር በብስራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እሁድ ዕለት ነሐሴ_7 ቀን ተፀነሰች፡:
✣ እመቤታችን ከተፀነሰች በኋላ አይሁድ ቀንተው ተነሱባቸው ቅናቱ እንዴት ነው ቢሉ፡፡ ሳሚናስ የሚባል የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካጎቱ ቤት ሄዶ ሞተ እነርሱም እንቀብራለን ብለው ባልጋ ይዘው ሲሄዱ ከመንገድ አሳረፉት ፤ የሃናም የአጎቷ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ ቆዩአት ፤ እርሷም አብራ እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነስቶ ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሃየ ጽድቅ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሃ ቤቱ ተፈስሂ ደስ ይበልሽ ብሎ ሰገደላት፤አይሁድ ከዛ ነበሩና ምነው ሳሚናስ ምን አየህ? ምን ትላለህ? ቢሉት ከዚች ከሃና ማህፀን የምትወለደው ሕፃን ሰማይ ምድርን እመቅ አየርን የፈጠረ አምላክን ትወልዳለች እያሉ መላእክት ሁሉ ሲያመሰግኑአት ሰማኋቸው እኔንም ያነሳችኝ የፈወሰችኝ ያዳነችኝ እርሷ ናት አላቸው ፤ በል ተወው ሰማንህ ብለው ቅናት ጀመሩ::
✣ እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም በተፀነሰች በ9 ወር ከአምስት ቀን የግንቦት መባቻ ዕለት ግንቦት 1 ተወለደች::



@etsemeaza @etsemeaza
455 viewsedited  19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 11:17:18
ስሞዖን ወአቅሌስያ ዘነበሩ በንሒሳ በኃጢአ ዉሉድ በከዩ መጠነ ዓመታት ሠላሳ።
ሥሉስ ቅዱስ ሶበ ነፍኁ በዉስተ ከርሣ
ተወልደ እምኔሆሙ ቀናዬ አናብስት ስሳ በኀይለ አምላኩ ዘይሠሪ አበሳ።
አብ በዘባኑ ወልድ በዘበኑ መንፈስ ቅዱስ በዘበኑ ዘሐዘልዎ በኪዳኑ ።
ገብረ መንፈስ ቅድስ ሠለስተ ገፃተ ዘይዜኑ ።
አዋክየ አዋክየ አዋክየ ሥኑ በኢትዮጵያ ዘተቀብረ በድኑ።
ኦ አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ዕቀበኒ ወአድኀነኒ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ሊተ ለሕዝበ ክርስቲያን
•✥• @etsemeaza •✥•
✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
❍ㅤ     ⎙ㅤ    ⌲ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
502 views08:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 10:57:28 ጥቅልል ብራናዎች
@etsemeaza
478 views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 22:21:18
228 views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ