Get Mystery Box with random crypto!

Ethio University

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University
የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversty1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.85K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አይነት የማስታወቂያ ስራ እና ክሮስ(Cross)
💰💰 @Cozboy0 💰💰
ያናግሩን🎫🎟🎪🎪🎪🎪

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 29

2022-11-02 05:16:54 #BulehoraUniversity

በ2015 ትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ድግሪ ትምርታችሁን በቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ የምትከታተሉ ነባር መደበኛ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲዉ ሴኔት ሰወሰነዉ መሰረት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በህዳር 5 እና 6/2015 ወደ ትምህርት ገበታችሁ እንድትመለሱ ዩንቨርሲቲው ጥሪዉን አስተላልፏል።
66 views02:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 01:56:19 #MizanTepiUniversity

የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ እና ድህረ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች መግቢያ ቀን ተገለፀ።

የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ (ተመራቂ የነርሲንግና የፋርማሲ ት/ት ክፍሎች ተማሪዎች ውጭ) ለሁሉም የቅድመ እና ድህረ-ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2015 ዓ.ም ትምህርት ምዝገባ የሚካሄደው ህዳር 5 እና 6 /2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ተመራቂ ተማሪዎች የሆኑ የነርሲንግና የፋርማሲ ትምህርት ክፍሎች ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜያ ታህሳስ 3 እና 4 መሆኑ ተገልጿል።

ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ ተብሏል።

* ከተገለጸው ጊዜ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ ዩኒቨርሲቲው አያስተናግድም።
356 views22:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 21:14:59 ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከ10 ሺሕ የሚበልጡ ነባር መደበኛ ተማሪዎችን ሕዳር 5 እና 6/2015 ዓ.ም እንደሚቀበል አሳወቀ።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መማክርት ጉባኤ (ሴኔት) በዛሬው ዕለት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መክሯል።

መማክርት ጉባኤው ተወያይቶ ውሳኔ ካስተላለፈባቸው ጉዳዮች የ2015 ዓ.ም አካዳሚክ ካሌንደርን ገምግሞ ማጽደቅ አንዱ ነው።

የ2015 ዓ.ም አካዳሚክ ካሌንደር በሬጅስትራርና አልሙናይ ጉዳዮች ዳይሬክተር በሆኑት መ/ር ሳሙኤል ሳርካ ቀርቧል።

በቀረበው አካዳሚክ ካሌንደር መሰረት በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች ዩኒቨርሲቲው ነባር መደበኛ ተማሪዎችን ሕዳር 5 እና 6/2015 ዓ.ም እንደሚቀበል ተገልጿል።

ነባር መደበኛ ተማሪዎች ሕዳር 5 እና 6/2015 ዓ.ም ምዝገባ እንደሚያካሄዱ፤ የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ (DOCO) ሕዳር 07 እንደሚጀምር፤ የካቲት 17/2015 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስቴር ማጠናቀቂያ እንደሆነ እንዲሁም ከየካቲት 20/2015 ዓ.ም እስከ መጋቢት 01/2015 ዓ.ም ድረስ የሴሚስቴር ማጠቃለያ ፈተና እንደሚሰጥ በቀረበው አካዳሚክ ካሌንደር ተብራርቷል።

ዩኒቨርሲቲው በሦስቱም ካምፓሶቹ በሁሉም የትምህርት ፕሮግራም ከ10 ሺህ የሚበልጡ ነባር መደበኛ ተማሪዎችን በመቀበል የመማር ማስተማር ሂደትን እንደሚያስቀጥል በመድረኩ ተጠቁሟል።

ነባር መደበኛ ተማሪዎችን ለመቀበል ከቀለብ፣ ከመኝታ ቤት፣ ከሕክምና፣ ከካውንስሊንና ጋይዳንስ (ከስነ-ልቦና ምክር) እንዲሁም ከስፖርትና መዝናኛ አንጻር በቂ ዝግጅት መደረጉ በመድረኩ ተመላክቷል።

መማክርት ጉባኤው የቀረበውን አካዳሚክ ካሌንደር ገምግሞ በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን፤ ነባር መደበኛ ተማሪዎች ሕዳር 5 እና 6/2015 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲው በመግባት ምዝገባ እንዲያካሄዱ ተወስኗል።

ጥሪ የተደረገላቸው ነባር መደበኛ ተማሪዎች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በተጠቀሱት ቀናት ምዝገባ እንዲያካሄዱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ አሳስበዋል።
381 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 22:37:05 #WolaitasoddoUniversity

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ እስካሁን ለመደበኛ ተማሪዎች ይፋዊ የሆነ የጥሪ ማስታወቂያ አላወጣም።

ዩኒቨርስቲው በ Facebook Page'ቸው የዘንድሮውን (የ 2015) የትምህርት Calendar ለጥፈው ነበር። በ ከለንደሩ መሰረት የተማሪዎች መግቢያ ህዳር 8 እና 9 ብሆንም ትክክለኛ የጥሪውን ማስታወቂያ እንጠብቃለን።

ዩኒቨርስቲው ይፋዊ ጥሪ ሲያደርግ እናሳውቃለን
526 views19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 20:21:42 #WoldiaUniversity

በ2014 በመደበኛው መርሀ ግብር ፈተና ጀምረው ያቋረጡ ነባር መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ህዳር 2-3/2015 ዓ/ም ነው።

በጦርነት ምክንያት ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በጊዜያዊነት ተመድበው ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ህዳር 12-13 /2015 ዓ/ም ነው።

* የተግባር ልምምድ ላይ የነበሩ የ4ኛ ዓመት የሲቪል ፣ የ4ኛ ዓመት የመካኒካል፣ የ4ኛ ዓመት የኬሚካል ምህንድስና ተማሪዎች መግቢያ ህዳር 2-3/2015 ዓ/ም ነው።
540 views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 15:52:37 #JinkaUniversity

ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2015 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ ኅዳር 05 እና 06/2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ትምህርት የሚጀምረው ➭ ኅዳር 07/2015 ዓ.ም

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
686 views12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:39:13 #የሥራማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥሩ ለሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ጀማሪ ባለሙያዎችን /Intern/ በኮንትራት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

በዚሁም መሠረት

- በህግ፣ በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ፣ በሶሺዎሎጂ፣ ሶሻል ወርክ፣ በህዝብ አስተዳደር፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን፣ በሰው ኃብት አስተዳደር፣ በቢዝነስ ሊደርሺፕ፣ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት፣ በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በግዢ እና ንብረት አስተዳደር፣ በጋዜጠኝነት እና ስነጽሁፍ፣ በግራፊክስ ዲዛይን፣ በፖለቲካል ሳይንስ እና አለምአቀፍ ግንኙነት እንዲሁም ተያያዥ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው/ያላት

- አማካይ የመመረቂያ ውጤታቸው 3.5 እና ከዛ በላይ የሆነ፤

- ጥሩ የሆነ የአማርኛ እና የእንግሊዘኛ ቋንቋን ክህሎት (መናገር፣ መጻፍ እና ማንበብ) ያለው/ያላት፤

- የማይክሮሶፍት ኦፊስ (MS Word, Excel, Outlook, and PowerPoint) እውቀት እና በአግባቡ የመጠቀም ችሎታ ያላት/ ያለው፤

- የተቋሙን ደንብና መመሪያ የሚያከብር/ የምታከብር፤

- የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፤

ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 7 ቀናት ውስጥ ከዚህ በታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ማመልከት የምትችሉ መሆኑን ቦርዱ ገልጿል።
696 views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 09:23:54
#DebraMarkosUniversity

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ2015 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ህዳር  08-09/2015 በመሆኑ ሁሉም መደበኛ የቅድመ ምረቃ እና 2ኛ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ በተገለፁት ቀናት በመገኘት እንድትመዘገቡ ዩንቨርሲቲው አሳስቧል።

       
642 views06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 09:23:00 ለደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ!

የ2015ዓ.ም የትምህርት ዘመን ነባር መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄድበት ቀን ህዳር 01 እና 02/2015 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን በተጠቀሰው ቀን በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ እንድትመዘገቡ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- ከተጠቀሰው ቀን ውጭ ዘግይቶም ሆነ ቀድሞ የሚመጣን ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
602 views06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 09:09:21 #OdaBultumUniversity

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የነባር የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2015 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ ኅዳር ዐ5 እስከ 06/2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ጥሪው የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት ያጠናቀቁ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች እና የሁለተኛ ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ተማሪዎችን ይመለከታል።

ትምህርት ኅዳር ዐ7/2015 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
584 views06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ