Get Mystery Box with random crypto!

ሰበር ዜና ETHIOPIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioseberzina — ሰበር ዜና ETHIOPIA
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioseberzina — ሰበር ዜና ETHIOPIA
የሰርጥ አድራሻ: @ethioseberzina
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 181
የሰርጥ መግለጫ

አላማችን መረጃን በአግባቡ በጥራት በፍጥነት ማድረስ ነው፡፡ @Ethioseberzina

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-10 22:31:39
#ጋና

" የእኔን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎች ደመወዝ በ30 በመቶ ቀንሷል " - የጋና ፕሬዜዳንት

የጋናው ፕሬዝደንት ናና አዶ ዳንኩዋ አኩፎ-አዶ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ቀውስ ሳቢያ የራሳቸውን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎቻቸው ደመወዝ በ30 % እንዲቀንስ መደረጉን አስታውቀዋል።

ይህን ያስታወቁት ትላንትና የዒድ አል-አድሃ በዓል ሲከበር ባሰሙት ንግግር ነው።

የ30% ቅነሳው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን፣ የመንግስት ኤጀንሲዎችን እና መምሪያዎችን ወጪ ይነካልም ተብሏል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ መንግስት እያሽቆለቆለ ያለውን ኢኮኖሚ ለመታደግ በሚያደርገው ጥረት ጋናውያን መስዋዕትነት እንዲከፍሉ ተማጽነዋል።

" አሁን ያለውን ችግር ለመቅረፍ ሁላችንም መስዋዕትነት መክፈል አለብን " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ መምሪያዎች እና ኤጀንሲዎች ወጪ በ30 በመቶ ቀንሷል። የእኔን ጨምሮ የሁሉም ተሿሚዎች ደመወዝም በ30 በመቶ ቀንሷል " ብለዋል።

የነዳጅ ኩፖን ምደባ በ50 % መቀነሱን እንዲሁም ሌሎች ወጪዎች መታገዳቸውን ገልፀዋል።

ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ጋናውያን እንዲታገሷቸው አሳስበዋል።

ፕሬዝዳንት ናና አዶ አኩፎ አዶ እኤአ ሰኔ 1/2022 የገንዘብ ሚኒስትሩ ኬን ኦፎሪ-አታ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር ይፋዊ ግንኙነቶችን እንዲጀምሩ አዘው ነበር።

የIMF ድጋፍ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በቅርቡ የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ እያጋጠሙ ያሉ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመፍታት ከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ ነው ተብሏል።

Video Credit : Citi TV, Ghana
5 viewsedited  19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 21:10:06 " እንወጣም " - ተቃዋሚዎች

የስሪላንካ ጉዳይ ዓለምን ማነጋገሩ ቀጥሏል።

የስሪላንካ ፕሬዜዳንት ከስልጣን ወርዳለሁ ቢሉም ተቃዋሚዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ለቀን አንወጣም ብለዋል።

የስሪላንካ ፕሬዜዳንት ጎታባያ ራጃፓክሳ መኖሪያ ቤትን የተቆጣጠሩት ተቃዋሚዎች ዛሬም ፕሬዝዳንታዊ መኖሪያውን እንደማይለቁ ገልፀዋል።

ተቃዋሚዎቹ የፕሬዜዳንቱን መኖሪያን ከተቆጣጠሩ በኃላና ፕሬዝዳንቱ በባህር ኃይል ታግዘው ከሸሹ በኃላ ከስልጣን እወርዳለሁ ቢሉም ተቃዋሚዎች ግን እስካሁን አልተቀበሉትም።

የተማሪዎች ንቅናቄ መሪ የሆነው ላሂሩ ዋራሴካራ ለጋዜጣኞች በሰጠው መግለጫ " ትግላችን ግና አላበቃም እሱ እስካልተወገደ ድረስ ትግላችንን እናቆምም " ሲል ተደምጧል።

ተቃዋሚዎቹ በፕሬዜዳንቱ አቅም ማነስ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ውድቀት መከተሉን እና ሙስና መንሰራፋቱን ይገልፃሉ ፤ በሀገሪቱ ለተፈጠረው የመድሃኒት ፣ የነዳጅ፣ የምግብ እጥረት እና ለድሃው ህዝብ ኑሮ መመሰቃቀልም ፕሬዜዳንቱን ተጠያቂ ያደርጋሉ።

በሌላ በኩል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን " የሩሲያ ወረራ " ሲሪላንካ ውስጥ ለተፈጠረው ቀውስ አስተዋጽኦ ሳይኖረው አይቀርም ብለዋል። ብሊንከን " የሩሲያ ወረራ ያስከተለው ችግር በየቦታው እየታየ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

መረጃው፦ ከአሶሼትድ ፕሬስ ፣ አርቲ እና ዶቼቨለ የተገኘ ነው።
15 views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 20:27:23
#ሰበር
ለሶስት አመታት በኤርትራ ሲሰለጥኑ የነበሩ የሱማሊያ መከላከያ ሰራዊት አባላት በዛሬው ዕለት የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሱማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼህ መሐመድ በተገኙበት ተመረቁ።
በዚህ የተነሳግብጽ እና የሱዳን ፖለቲከኞች በተለያዩ ሚዲያዎች ብስጭታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ። "አዲሱ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት በኤርትራ ያደረጉት የስራ ጉብኝት.....የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ፍጥነቱን ቀንሶ ቢራመድ ጥሩ ነው ከፋርማጆ ብዙ ነገር ሊማር ይገባል" በማለት ዛቻ አዘል አስተያየቶች እየሰጡ ነው።
17 views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 19:48:36
ባለሃብቱ ለወጣቶች ስራ ፈጠራ 10 ሚሊዮን ብር አበረከቱ !

ኢትዮጵያዊው ባለሀብት አቶ በላይነህ ክንዴ ፤ #ለወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸው ተሰማ።

አቶ በላይነህ ለሰከላ ወረዳ ወጣቶች ነው የስራ ዕድል መፍጠሪያ የሚውል 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ያደረጉት፤ ድጋፉንም ሰከላ ወረዳ ግሽ ዓባይ ላይ ተገኝተው ለወጣቶቹ አስረክበዋል።

ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ በርክክብ ፕሮግራሙ ላይ ለወጣቶቹ የህይወት ተሞክሯቸውን እና ምክር አካፍለዋል።

አቶ በላይናህ ክንዴ በርክክብ መድረኩ ላይ ፦

" መንግስት ብቻ ሳይሆን ባለሀብቱ #ለወጣቶች የስራ ዕድል እንዲፈጠር ትልቅ ሀላፊነት አለበት።

ወጣቶቻችን የስራ ዕድል ካልተፈጠረላቸው እና ሀብት ማፍራት ካልቻሉ የባለሀብቱ ዕድገትም ይገታል። ስለሆነም ለወጣቶቻችን የስራ ዕድል በመፍጠር ተያይዘን ማደግና ሀገር መለወጥ ይገባናል።

ለእኛ ሀብታችን ወጣቶቻችን ናቸው ፤ ወጣቶች በገቢ እራሳቸውን ችለው ለቤተሰብና ለሀገር እንዲተርፉ እንደ ዜጋ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።

ወጣቶችም የትኛውንም ስራ ሳይንቁ መስራት አለባቸው። እኔ ከዝቅተኛ ስራ እና ከትንሽ ገንዘብ ተነስቼ ነው እራሴን እየለወጥኩ የመጣሁት።

ይህ በድጋፍ የተሰጠ 10 ሚሊዮን ብር በተዘዋዋሪ ብድር መልክ ነው።

ወጣቶች አሁን የወሰዳችሁትን ገንዘብ ቁምነገር ላይ በማዋል አቅም እንድትፈጥሩ እና ብድሩን በመመለስ ለሌሎች ወንድሞቻችሁ የስራ ዕድል መፍጠሪያ እንዲሆን መስራት አለባችሁ " ሲሉ ተናግረዋል። (APP)
22 viewsedited  16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 19:48:36
#ጥንቃቄ

ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በተገኘ መረጀ በሐምሌ የመጀመርያዎቹ ሳምንታት ከፍተኛ የሆነ ነጎድጓዳማና በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ይኖራል።

በተከታታይ ቀናት የሚኖረው የዝናብ መጠን ጎርፍና የመሬት መንሸራተት ሊፈጥር ስለሚችል አስፈላጊው ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል፡፡

በአርብቶ አደር አካባቢዎች የሚገኘውን ውኃ በጥንቃቄ መያዝም እንደሚገባ ተገልጿል።

የሚፈጠረው ዝናብ ከመጠን በላይ ማሣ ላይ ውኃ እንዲተኛ ስለሚያደርግ በእርሻ እንቅስቃሴው ላይ አሉታዊ እንቅስቃሴ እንዳያስከትል የማጠንፈፊያ ቦዮችና የጎርፍ መከላከያ እርከኖች በመሥራት ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ከመደበኛ በላይና መደበኛ ዝናብ የሚጠበቅባቸው ቦታዎች ፦
- አፋር፣
- አማራ፣
- ትግራይ፣
- ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች መሆናቸውን ኢንስቲትዩቱ አሳውቋል።

በተለይም ለጎርፍ ተጋላጭ የሆኑ ማለትም ተዳፋትና ገደላማ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የክረምቱ የዝናብ ሁኔታ በሐምሌና ነሐሴ ወራት እንደሚጠናከር የሚጠበቅ ሲሆን መብረቅ፣ ጎርፍና የበረዶ ግግር ሊኖር ስለሚችል ማኅበረሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል ተብሏል።

መረጃውን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩትን ዋቢ አድርጎ ሪፖርተር ነው ያጋራው።
19 viewsedited  16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 18:40:03
የሶማሌ ክልል ፕሬዝደንት አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ዛሬ ለምረቃ ከበቁት የክልሉ ፖሊስ አባላት መካከል 400 ያህሉ ወደ ጅግጅጋ ከተማ ፖሊስ እንደሚቀላቀሉ ገለጹ፡፡

ርእሰ መስተዳዳሩ በአፍ ሶማሊ ቋንቋ በይፋዊ የማህበራዊ ድረገፃቸው ባጋሩት መልእክት እንደገለጹት ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ጋር በመሆን በጅግጅጋ ፖሊስ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከ2,100 በላይ አዳዲስ የፖሊስ አባላትን ዛሬ በተመረቁበት ስነ-ስርዓት ላይ መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ መልእክታቸውን ሲቀጥሉ በዛሬው እለት ከተመረቁት የክልሉ ፖሊስ አባላት መካከል 400 የሚሆኑት የመዲናዋን ፀጥታ ለማሻሻል ወደ ጅግጅጋ ፖሊስ ሀይል በቀጥታ የሚቀላቀሉ መሆኑን ጠቁመው ሌሎች የከተማ አስተዳደሮችም ልክ እንደ ጅግጂጋ ከተማ አስተዳደር የከተሞቻቸውን ፀጥታ ለማጠናከር የራሳቸውን ምልምል አባላት በቅርቡ ወደ ፖሊስ ማሰልጠኛው እንደሚልኩም ጠቁመዋል፡፡

በዛሬው እለት የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ለ6 ወራት በሶማሌ ክልል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ስልጠና ሲሰጥ የነበረውን የፌደራልና የክልል ጥምር ፖሊስ ሰራዊት የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ፣ የኢፌዲሪ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደምመላሽ ገ/ሚካኤል፣ የሶማሌ ክልል የሰላምና ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙበሽር ዱበድ፣ የሶማሌ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መሀመድ አሊ፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ሀይል ዋና አዛዥ መሀመድ አህመድ እንዲሁም ሌሎች እንግዶች በተገኙበት መመረቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
23 views15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 16:48:43 የሶማሊያው አዲሱ ፕሬዝዳንት ወደ ኤርትራ ማቅናት ህወሃት ደጋፊዎች ስጋት መፍጠሩ እየተገለጸ ይገኛል።


ከዚህን በፊት በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ መካከል የተፈጠረው አጋርነት ስጋት ውስጥ ከቶቸው የነበሩ የህወሃት ሰዎች የፋርማጆ መሸነፍ ትልቅ ለውጥ ያመጣልናል ብለው ተስፋ አደርገው ነበር። ይሁን እንጂ አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት በተመረጡ ማግስት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተቀራርበው መስራት እንደሚፈልጉ መልዕክተኛ መላካቸው፤ የበዓለ ስሜታቸው እለትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድን ቁጥር አንድ እንግዳ አድርገው መጋበዛቸው፤ በትላንትናው እለት ደግሞ ወደ ኤርትራ በመሄድ ይፋዊ ጉብኝት ማድረጋቸው ለህወሃት ሰዎች ትልቅ ስጋት ፈጥሯል። በዚህም ሳያበቃ አልቡርሃን ከኢትዮጵያ ጋር ወደ ጦርነት መግባት ጣጣው ለከፋ ነዉ ስለዚህ አሸማግሉኝ ብለው ለኬንያ አማላጅ ሲልኩ መቆየታቸው ሲገለጽ ነበር። ይህንኑ በሚያጠናክር መልኩ በኢጋደ ስብሰባ ወቅት በአልቡርሃን ጥያቄ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ጋር በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ያዝ እንግዲህ ጁንታው አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱ ከዚህ በላይ ምን ምስክር ሊሆን ይችላል?
27 views13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 15:28:12
ወለጋ ላይ እንዲህ አስኬረን ማንሳት እና መቅበር እስኪሳናቸው ድረስ እያየን ነው። የሞተ ተጎዳ ማለት ይሄ ነው። በጣም ያሳዝናል።
30 viewsedited  12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 15:28:12 በፎቶው የምትመለከቱት ቢንያም ኢሳያስ ይባላል።
4 ዓመት ድረስ ፈታኝ ነው የሚባለውን የህክምና ትምህርት (ሜዲስን) ከተማረ በኃላ ግን ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በኃላ መማር አትችልም ሲል ገልጾለታል።
ለምን ? ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ ከህፃነቱ ጀምሮ የአካል ጉዳተኛ ነው፤ በዚህም ሳቢያ ነው 5ኛ ዓመት ከደረሰ በኃላ ዩኒቨርሲቲው አካል ጉዳተኛ ስለሆንክ ለዚህ ትምህርት አትመጥንም ብሎ እንዲወጣ የተደረገው።
ይህ ችግር እንዲስተካከል ብዙ ቢለፋም ምንም መፍትሄ አንተገኘም ፤ በዚህ ሁኔታ ትምህርቱን መከታተል የማይችል ከሆነ ለምን በቅድሚያ ትምህርቱን እንዲጀምር ተደረገ ለሚለው ? ዩኒቨርሲቲው መጀመሪያውኑ መመዘን እንደነበረበት ነገር ግን እንዳልመዘነ ገልጿል።
በሌላ በኩል በህክምና ትምህርት ሁለት እጅ የማይጠይቁ ስራዎች ላይ መግባት ችላለሁ ብሎ ተማሪ ቢንያም ቢጠይቅም (ሳይካትሪ፣ ፐብሊክ ሄልዝ ሌሎችም) ዩኒቨርሲቲው ግን ለመቀበል ፍቃደኛ አልሆነም።
ተማሪ ቢንያም ፥ " አጥብቀው ያነሱት ልጅ ማዋለድ፣ ደም የፈሰሰው ሰው ሲመጣ እሱን ማቆም ትችላለህ ? የሚል ጥያቄ ነው የጠየቁኝ፣ ከህፃንነት ጀምሮ አካል ቢጎድለኝም እጄ ይንቀሳቀሳል ይሰራ፣ ቀኝ እጄንም ይደግፈዋል፣ እኔን ለመርዳት ከፈለጋችሁ ስሰራ አይታችሁ እስካሁን ድረስ ትምህርት ስንማር ሁለት እጅ ለሚፈልጉ ስራዎች በራሴ መንገድ መስራት እችላለሁ በህክምና ውስጥ ያሉትንም ጠቅሼላቸዋለሁ ግን ፍቃደኛ አልሆኑም። አትችልም አትችልም ነው አሉኝ። መያዝ ይችላል፣ መደገፍ ይችላል፣ በሁለት እጄ መስራት እችላለሁ፣ እስካሁን ጥሩ ሄጃለሁ በኃላ ያ ሲመጣ በራሴ መንገድ መስራት እችላለሁ ብላቸውም ከእኔ ጋር አብሮ ለመስራት ፍቃደኛ አልሆኑም።
በአጥንት ክፍል evaluate እንድደረግ ላኩኝ ፤ ታህሳስ ውስጥ ነው የጀመረው እስከ ሰኔ ድረስ ቀጥሏል። እስካሁን ቀጥተኝ መልስ ሳይሰጡኝ ነው ያሉት " ሲል ተናግሯል።
አባት አቶ ኢሳያስ ገብረወልድ ልጃቸው በጣም ባለብሩዕ አእምሮ መሆኑን ገልፀው ከታች ጀምሮ በከፍተኛ ውጤት ዩኒቨርሲቲውን እንደተቀላቀለ ገልፀዋል።
አሁን ላይ የተደረገው ድርጊት እጅግ በጣም እንደጎዳቸው አመልክተዋል።
አቶ ኢሳያስ " እንደ አባት ሳይሆን በሙሉ ቤተሰብ ተጎድቷል፣ ከዚህ በፊት ያስተማጉት አስተማሪዎች በጣም ተሰምቷቸዋል፣ ምክንያቱም ይሄ ጉዳይ ያተነሳው ታህሳስ 1 /2014 ነው ቆይቶ ከ2 ወር በኃላ ያለምንም ወረቀት በቃል ነው እንዲወጣ ያሉት " ሲሉ ገልፀዋል።
ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ እንደሚናገረው ዩኒቨርሲቲው አሁን የወሰነው ውሳኔ ሌሎች ትምህርቶች ፋርማሲ፣ ሜዲካል ላብራቶሊ እና ራዲዮሎጂ ቴክኖሎጂ እንዲገባ ነው።
ነገር ግን ተማሪ ቢንያም እዛው አሁን ባለበት ቀጥሎ ሁለት እጅ የማይፈልጉ ስፔሻላይዜሽኖች ስላሉ ወደዛ መቀላቀል ነው ፍላጎቱ።
ይሄን ያህል አመት የለፋበትን ከግንዛቤ በማስገባት ወደዛ እንዳያስገቡት ነው የጠየቀው ፤ እነሱ ግን እንደዛ ማድረግ አንልችልም የሚል ምላሽ ነው የሰጡት።
ተማሪ ቢንያም እና ወልጅ አባቱ ከተፈጠረው ክስተት ጋር በተያያዘ ውሳኔውን ያሳለፉ ዩኒቨርሲቲው አካላት ንቀት በተሞላበት መልኩ እንዳስተናገዱት፣ እንደቀላልም እንዳዩት ቅሬታ አቅርበዋል።

(የቢንያም እና አቶ ኢሳያስ ቃል የተወሰደው ከሸገር ኢንፎ ከተሰኘ የዩትዩብ ቃለምልልስ ነው)
28 views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 15:28:12
26 views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ