Get Mystery Box with random crypto!

ታደሰ ደምሴ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopia2123 — ታደሰ ደምሴ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopia2123 — ታደሰ ደምሴ
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopia2123
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

ሥነ_ግጥም
ግጥሞችን በዩቱብ ለመከታተል👇👇👇
https://youtube.com/@maryam2116

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-07 07:19:13
ሀገር ስጪኝ...
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ለጠየቅሽኝ እንቆቅልሽ ፣ ሲጠፋብኝ እኔ መልሱ
"ሀገር ስጠኝ" የምትዪኝ ፣ መልስ አታውቂም አንቺ ራሱ!
።።
ሁሉ ሀገሩን ተከፋፍሎ፣ ክልሎችን እያጠረ
ኬ'ት አምጥቼ ሀገር ልስጥሽ ?፣ ሀገር ማለት "ሰው" ነበረ።
ሰውም በዘር ተከፋፍሎ ፣ ሀገር መሆን አቅቶታል
ገድሎ ሚኖር ተበራክቶ ፣ ሞቶ ሚያኖር ካገር ጠፍቷል!
።።።
ይህን እውነት እያወቅሽው ...
"ሀገር ስጠኝ" አትበዪኝ ፣ በእንቆቅልሽ ልትለውጭኝ
ክልልና ዘር ነው ያለኝ ፣ እሱን ወስደሽ ሀገር ስጭኝ!

@ethiopia2123
@ethiopia2123
@ethiopia2123
214 viewsዴር 33, edited  04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 08:13:33
ጨረቃየ....

"ነጋልኝ" ስል ጨለማው ሀይል እያጋተ ቢያስቸግረኝ
"ቀን አለ" ስል ቀን ተሳልቆ ቢሰወረኝ

በመዳፌ የጨበጥሁት፣
ከህይወት ክር ጋዝ ነክሬ ያያያዝሁት
ከመቅረዜ ዘይት ነጥፎ
ከምችለው ጽዋ ተርፎ
ከሲኦል በር የበረታ የጽልመት ዶፍ ቢያገሳብኝ
ከጨለማው ሞገስ ሸሽት "ደጀን" ያልሁት ቢያመነታኝ

ለብቻየ...
ከእራስ ደጀን የገዘፈን ቀፋፊ ቀን እንጋጋጥ ግድ ቢለኝ
የጥፋት ክንድ ከማንቁርቴ አፈፍ አርጎ ቢያስወነጨኝ
ከተራራ_ትክል ድንጋይ ቢያጣብቀኝ
ከመሬት ልብ ቢደፍቀኝ...


ከሞት አፋፍ ነፍስ የመክተብ ተስፋ ያለኝ
የሾተላይ የሴራ ድር የማያስረኝ
ቀን ጨክኖ ሲቧጨቀኝ
አፈር ልሼ የምነሳ ብርቱ ሰው ነኝ

እባክሽን ጨረቃየ...
ማንነትሽን ዝገኝና ከእኔነቴ ሰሌዳ ላይ አስማሚልኝ
ተራ ሲደርስ መወደድን፣
ከዕልፍ አዕላፍ ጋር መፈንደቅን፣ ከህይወት ልምድሽ አስተምሪኝ

(ታደሰ ደምሴ)

@ethiopia2123
@ethiopia2123
@ethiopia2123
270 viewsአ.ቡ.ጊ.ዳ.., 05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 10:40:35 በቀፋፊ ቀን ላይ
ቀፋፊ ፊት አየሁ።
ቀን ነርቶኝ ሳልድን
በሰው ግምባር ቆሰልሁ።
በሰው አይን ተወጋሁ።
በሰው ምላስ መረርሁ።

ይበለኝ...!
ይበለኝ...!
ሰው ለምዱ ሲገፈፍ አውሬ ስለመሆኑ ብሒሉ ሳይጠፋኝ።
ለጥቃቅን ሰበብ ማን ተላመድ አለኝ።

እዝጎ

@ethiopia2123
266 viewsዴር 33, 07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 20:17:15 Watch "ሰቆቃወ ወለጋ! በአማራነቴ ተዋርጄ በኢትዮጵያዊነቴ የምመካበት ስብዕና የለኝም! " on YouTube


301 viewsአ.ቡ.ጊ.ዳ.., 17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 18:42:20 «እባክሽ ይሄ ከንቱ ሞተ ብለሽ እንባሽን አታባክኚ! ሞት መጥፎ ነገር ነው ያለ ማን ነው? ማን ያውቃል ከህይወት የተሻለስ ቢሆን! በህይወቴ አንድ ቁምነገር ሰርቼ ባልፍ ትይኝ አልነበር? መፃፋችንን ጨርሺው። ልጆቼን አደራ! ስወድሽ ኖሬያለሁ!!»
የሆነ ጊዜ ላይ ስለሞት ያወራኝን አስታወስኩት። ከ80 ዓመት በላይ መኖር አልፈልግም ይለኝ ነበር ሁሌ። ምክንያቱም መዝረክረክ ስለማይፈልግ!
«ሞትን እንደመጥፎ ነገር የምናየውኮ ማንም ከሞት በኋላ ያለውን ህይወት ስለማያውቅ ነው! ሰው ሲሞት በህይወት ያለው ሰው የሚቀርበውን ስለሚያጣ ሞትን ክፉ ነገር አድርጎ ያወራዋል። ለምሳሌ አስቢው በህመም ሲሰቃይ ለነበረ ሰው ሲሞት ማልቀስ ልክ ነው? ሰውየውኮ ስቃይ ላይ ነበር? የምናለቅሰው ሰውየው ስለተገላገለ ነው? ለራሳችን ነው ለሰውየው ነው የምናለቅሰው? ደግሞስ ከሞት በኋላ ያለው ምናልባት ከህይወት የተሻለ ሁላ ቢሆንስ?» ብሎኝ ነበር። ጭራሽ ድምፅ አውጥቼ እያለቀስኩ።
«እሺ ይሁንልህ! የተሻለ ይሁንልህ!» ብዬ በቂጤ መሬቱ ላይ ተዘረፈጥኩ!!


ጨርሰናል!!


t..me/ethiopia2123
t.me/ethiopia2123
t.me/ethiopia2123
285 viewsBetslot markos, 15:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 18:36:28 የወጠረኝ ደም ሲበርድ የምፀፀት ነበር የመሰለኝ። በምትኩ የሆነ መገላገል አይነት ስሜት ተሰማኝ። የሚራወጥ ጭንቅላቴ እርግት እንደማለት።
«ቀንተሃል! ተናደሃል! በራስህ በሽቀሃል! ያን ግን እየተወጣኸው ያለኸው ትክክለኛ ቦታ አይደለም! በፊት እንደምታደርገው በመፅሃፎችህ ወይም በስራህ ራስህን ልትሸውደው ሞክረህ ሀሳብህ አልሰበሰብ ብሎሃል! ያን በወሲብ እየተካኸው ነው! የቀኑን ውጥረትህን ትቀንስበታለህ እንጂ ቋሚ መፍትሄ አይሆንህም! አንተ ራስህን ልትረዳው ካልፈለግክ እኔ ምንም ላደርግ አልችልም አዲስ መፍትሄው አንተጋ ነው!! ። ራስህን በጊዜያዊ እፎይታ ልትሸውደው አትሞክር! ውጥረት በተሰማህ ቁጥር ያን እፎይታ ፍለጋ በወሲብ ልትወጣው ትሞክራለህ! ስትደጋግመው ልክ እንደማንኛውም ድራግ ነው። የሚሰጥህ እፎይታ መጠን እየቀነሰ ይመጣና ዜሮ ይሆናል። ይሄኔ ውጥረቱ ብቻ ሳይሆን አንተ ባልሆነው ማነነትህ ብስጭትህና ፀፀት ይጨመሩበታል። ወይ ሌላ የምትተነፍስበት ሱስ ትፈልጋለህ ወይም ወደምትሸሸው ጨለማህ ትመለሳለህ!!» አለኝ ዶክተር የሆነ ቀን በሀኪም ለዛ ሳይሆን በአባት ቁጣ!!
በትክክል ሂደቱን ጠብቆ የተከሰተው ያ ነው። ደጋገምኩት! በደጋገምኩት ቁጥር እርካታን ሳይሆን የባሰ ጭንቀትን እያስታቀፈኝ መጣ!! እዚህጋ እሷንም ዘነጋኋት ራሴንም እንደዛው። ከወራት በኋላ ዶክተርጋ ሄጄ
«አሁን ዝግጁ ነኝ የሆንኩትን ሆኜ መዳን እፈልጋለሁ።» አልኩት። ደስ ብሎት ትከሻዬን እየመታ ተቀመጠ። ማውራት የጀመርኩኝ ቀን አስመለሰኝ ሁላ! የእናቴን አልፌ የመጀመሪያ የማዕረግ ክህደቷን አልፌ ሶስተኛው ጋር ስደርስ ተሰምቶኝ የነበረውን ዲቴል ማውራት ያቅተኛል። በየቀኑ ከመጀመሪያው እጀምራለሁ። በየቀኑ ትንሽ እየገፋሁ አቆማለሁ። በዚህ መሃል ለስራ ከከተማ ወጥቼ ስመለስ ነው መኪናዬ የተገለበጠው። እያሰብኩ እንደነበር አስታውሳለሁ ምን እንደሆነ ግን አላውቅም! ከፊቴ የሚመጣ መኪና ጡሩንባውን ሲያስጮኸው ነው እንደመባነን አድርጎኝ መሪዬን ያጠመዘዝኩት።»
«ለእኔኮ ግን እስከመጨረሻው ነገርከኝ አይደል? ያ ማለት?» አልኩት ካለፈው ስቃዩ የመዳን ምክንያት ሆኖት ከሆነ በሚል
«እናያለና!» አለኝ
«እሺ ቆይ በቃ? ከዛ በኋላ ያለውስ?» አልኩት ኮንፒውተሩን እያስቀመጥኩት።
«ከዛ በኋላ ያለውን አንቺ የማታውቂው የለም ራስሽ ትፅፊዋለሽ!» አለኝ በእርግጠኝነት
«እህ! ያንተን ስሜት ግን በትክክል ላሰፍረው አልችልም!»
«come on! ካንቺ በላይ የሚያውቀኝ ሰው የለም። በስሜት ደረጃ ከማንም ጋር መቆራኘት የማልፈልግ ሰው ዊልቸር ላይ ተቀምጬ በአካልም የሰው እርዳታ የምፈልግ ጥገኛ መሆኔ ምን እንዲሰማኝ እንደሚያደርገኝ ካንቺ በላይ የሚረዳ ሰው አለ? »
«የሰውን ድጋፍ ማግኘትኮ ሁሉም ሰው በሆነኛው የህይወቱ ጊዜ የሚገጥመው ነው! አንተ ሰዎችን ትረዳ የለ? ሰዎች ሲረዱህ ውድቀት የሚሆንብህ ለምንድነው?»
«በቃ እኔ ነኛ! (ትከሻውን ምን ላድርግ አይነት እየሰበቀ) በሰው ድጋፍ የምንቀሳቀስ ሰው መሆን ሞቴ ነው! ያን ታውቂያለሽ!! ለዘመናት የለፋሁትኮ በስሜትም በአካልም በገንዘብም ማንንም ያልተደገፍኩ ነፃ ለመሆን ነው» አለኝ የእርሱ ባልሆነ ማባበል ድምፅ! አላውቅም ምን እንዳሰብኩ ማጅራቴ ላይ ያለ እጁን ስቤ ሳምኩት። ሲጠብቀው የነበረ እርምጃ ይመስል አስከትሎ ከንፈሬን ሳመኝ። እየሳመኝ ያወራ ጀመር እንደበፊቱ ወሬው ግን የቀን ውሎአችንን አይነት አይደለም። ጆሮዬን ማመን እስኪያቅተኝ አዲስ በፍቅር ቁልምጫ ስም እየጠራኝ ነው። ደንግጬ ለሰከንድ በርግጌያለሁ ሁላ! ረዥም ሰዓት ከተሳሳምን በኋላ አቁሞ እንደመሳቅ ነገር እያለ
«ንግስቴ እንደምታደርጊኝ ካላደረግሽኝኮ እግሬን አላዘውም!» አለኝ አባባሉ ውስጥ <አየሽ ለዚህ እንኳን ያንቺን እርዳታ መጠየቅ ግድ ሲለኝ?> አይነት የመሰበር ድምፀት አለው። ሶፋው ስላልተመቸን ምንጣፉ ላይ ወርደን ማላብ ጀመርን! ከላይ ሆኜ እያየሁት እሱ በሚጠራኝ የፍቅር ቁልምጫ ሁሉ ልጠራው እፈልጋለሁኮ! ግን ከአፌ አይወጣም! አንዴ ቢለኝ ብዬ አምላኬን የለመንኩትን ቃል አለኝ። «ልትገምቺው ከምትችዪው በላይ እወድሻለሁ!» አለኝ። ስሰማው እፈነጥዛለሁ ብዬ ያሰብኩትን ያህል አላስፈነጠዘኝም! ንግስቴ ፣ ፍቅሬ ፣ ልዕልቴ ……….. ያላለኝ የለውም። ለዓመታት ያላለውን ማካካስ የሚመስል ፍቅር ……. ስንጨርስ አጠገብ ላጠገብ ተኝተን ዝም ተባባልን። ከሴክስ ስሜት ውጪ ያ የተስገበገብኩለት ፍቅር ስጨብጠው ምንም አልመስልሽ አለኝ ብዬ እውነቱን ነው የምነግረው ወይስ እንደዚሁ እንቀጥላለን ? በተጎዳው ላይ ጉዳት መጨመር መሰለኝ! ምናልባት ሽባ ስለሆንኩ ነው የጠላችኝ ይለኛል እያልኩ ሳስብ
«ይሰማኛል ብለሽ ያሰብሽውን ስሜት ውስጥሽ አጣሽው?» አለኝ
«ለምን እንደእሱ አልክ?»
«አውቅሻለሁ እኮ! በደንብ።»
«ታዲያ ካወቅክ?» ብዬ እንዴት መጠየቅ እንዳለብኝ ግራ ሲገባኝ
«ፍቅርሽን ከጨረሽ እንደቆየሽ አውቃለሁ። ከዛ ሁሉ በደል በኋላ ያ ስሜት ሊኖር አይችልም!»
«የበደልከኝንኮ ግን ትቼልሃለሁ!»
«አውቃለሁ! ይቅር ስትዪኝ ላለፍኩት መንገድ አዘንሽልኝ። ፍቅርን እና ሀዘኔታን ነው ያልለየሽው!»
«እሺ ካወቅክ ለምን?»
«ምንም እንዳልቀረብሽ እንድታውቂ!! ከተመኘሽው ምንም እንዳይጎድልብሽ!» አለኝ።
መኝታ ቤታችን ገብተን አቅፌው ተኛሁ። ነጋችንን እንዴት እንደምንኖረው እያሰብኩ እንቅልፍ ወሰደኝ። አይኖቼን ስገልጥ አንዳች ሸክም ከላዬ እንደተነሳ ቅልል ብሎኝ ነበር። አይኖቹን እንደጨፈነ ነው። ተገላብጬ ደረቱ ላይ ተጠግቼ ተኛሁ።
«አዲስዬ ! አዲስዬ!» ልቀሰቅሰው ሞከርኩ «ዛሬ እኔ ስራ ቦታ ደርሼ ልምጣ?» አይመልስልኝም። ቀና ብዬ አየሁት! «አታደርገውም አዲስዬ!!» ራስጌውጋ ያለውን መጠቀም ያቆመውን ያኔ ከባድ ህመም ሲሰማው ይወስድ የነበረውን ከባድ ፔንኪለር እቃ አየሁት!! «አታደርገውም! አዲስ አታደርገውም!» እቃው ባዶ ነው! ተነስቼ ይሰማኝ ይመስል ደረቱን እየደበደብኩ ማልቀስ ጀመርኩ።
መጠርጠር አልነበረብኝም ሲሸነፍልኝ? ያቺን ከዲያቢሎስ ጋር ሲማከር የሚያመጣትን ፈገግታ ፈገግ ካለ በኋላ ድንገት ቅይር ስል መጠርጠር አልነበረብኝም? አውቀው አልነበር ክፉ ሲያስብ? ከምንም ተነስቶ እንደዛ ቅይር እንደማይል እንዴት ጠፋኝ? ይሄን አስቦት ነው ማታ የሆነውን ሁሉ የሆነው! መጠርጠር አልነበረብኝም ፍቅሩን ሲያምንልኝ? መጠርጠር አልነበረብኝም በደሉን ሲያምንልኝ?? እስከሞት ራሴን የምወደው ራሴን ነው ሲለኝ መጠርጠር አልነበረብኝም? ሁሌም አፍቃሪ ሰውነቱ በተገለጠ ማግስት መዘዝ ተከትሎት እንደሚመጣ እንዴት ዘነጋሁት? ከመሸነፍ ሞትን እንደሚመርጥ አውቀው አልነበር? ድምፅ የወጣው ለቅሶ ማልቀስ አቃተኝ። እንባዬ ጉንጬ ላይ እየተንዠቀዠቀ አገላብጬ ሳምኩት። እያለቀስኩ ወደሳሎን ሄጄ ፀሃይን ጎረቤታችንን እንድትጠራ ስነግራት
«ምነው እናቴ? ምን ሆንሽ?» ስትለኝ
«አዲስ አዲስ » ብዬ መጨረስ አቃተኝ።

«በጠዋት ስትነሳ ስጫት ብሎ ይሄን ወረቀት ሰጥቶኝ ነበር ትናንት! ምነው አመመው እንዴ?» አለችኝ ወረቀቱን እያቀበለችኝ።
210 viewsBetslot markos, 15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 18:34:28 ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ………. እኔ የቀጠልኩት

(የመጨረሻው ክፍል)

ሜሪ ፈለቀ

«ዶክተር ራሴን ሀኪም ቤት ካገኘሁት አልድንም ይብስብኛል እመነኝ! ትንሽ ቀን አይተኸኝ ከባሰብኝ ቃል እገባልሃለሁ ራሴው ሄዳለሁ» አልኩት። ከህክምና ጣቢያ ህክምናዬን መከታተል እንዳለብኝ ሲነግረኝ
እቤቱ ይዞኝ ሄደ። በዚህ ጊዜ እንዳለፈው ለማላውቀው ጊዜ ያህል ጨለማና ፍርሃቴ ውስጥ አልነከርም!! አስፈሪው ደቂቃ ትንሽ ነው። ያቃተኝ እንቅልፍ ሲወስደኝ የምቃዠውን ቅዠት ነው። የእናቴ ሬሳ ሆኖ ይጀምራል። በእጄ እንደታቀፍኳት ማዕረግ ትሆንብኛለች። ወይም ሚስቴን! በሌላኛው ቀን ደግሞ ልክ የአባቷን ሞት ስትሰማ እጄ ላይ እንደወደቀችው ስትወድቅ እጀምራለሁ። እንደታቀፍኳት ወይ ማዕረግን ወይ እናቴን ትሆንብኛለች። ለቀናት መተኛት ፈራሁ። ዶክተር መድሃኒት አዘዘልኝ። ለሳምንታት እሱጋ ቆየሁ። አሁንም ግን እሱ የሚለውን ፋይል ለመክፈት ዝግጁ አልነበርኩም! እቤቴ ለመመለስ ዝግጁ ስሆን ተመለስኩ። ከተመለስኩ በኃላ የአባቷን ለቅሶ አብሬያት ስላልነበርኩ ታኮርፈለች ብዬ ስጠብቅ ጭራሽ የእኔ ደህንነት አሳስቧት ደህና መሆኔን ትጠይቀኛለች። ትታኝ እንድትሄድ እፈልጋለሁ። ግን ደግሞ ራሷ ጠልታኝ እንድትሄድ እንጂ በእኔ ምክንያት ከሆነችው መሆን ሲደመር ከአባቷ ሀዘን ጋር ሌላ የከባድ ሀዘኗ ሰበብ መሆን አልፈልግም! ያን የማላደርገው ራሴን ላለመጉዳት ይሁን እሷን አላውቅም። ምናልባትም እናቴ እንዳስታቀፈችኝ አይነት ፀፀት ድጋሚ ላለመሸከም ፈርቼም ይሆናል።
ተናግሬ በማላውቃት ለቤተሰቦቿ በምትልከው ገንዘብ ተናገርኳት። የማትደራደርበት ዋልታዋ ስለሆነ ከጠላችኝ በላይ የምትጠላበት ምክንያት ያቀበልኳት ነበር የመሰለኝ። ትጥላኝ ትውደደኝ አላውቅም ግን ትታኝ አልሄደችም። ከሆነ ጊዜ በኋላ ማታ ላይ እራት ልበላ ተቀምጬ ምስቅል እንዳለች ወደሳሎን ገባች። የእናቷን ቤት መወረስ ስትነግረኝ ደነገጥኩ። አላወቅኩም ነበር! ስለእውነት ትኩረት ሰጥቼም ብሩ መከፈል ማቆም አለማቆሙን አላስተዋልኩም! ከእኔ ቃል እና ከእናቷ የእኔን ቃል እንደምታከብር ልገምት አልችልም ነበር። እያለቀሰች ትታኝ ስትገባ ተከትያት መሄድ ፈለግኩ። ለቀናት ሸሸኋት። ይሄ የመጨረሻዋ ይሆናል ብዬ ጥላኝ እንድትሄድ ስጠብቃት የሆነ ቀን ጠዋት ትታኝ እንደማትሄድ ቁርጥ አድርጋ ነገረችኝ። ዓመቱን ጠብቃ ብሯን ተካፍላ እንደምትሄድ ነገረችኝ። ንግግሩም ሀሳቡም የእሷን ስለማይመስል ግራ ገባኝ። ከፈለግክ አንተ ፍታኝ ብላኛለችኮ እንድትሄድ እፈልግ የለ? ለምንድነው በቃ እንፋታ ማለት ያቃተኝ? ለራሴኮ ደጋግሜ እነግረዋለሁ። እሷን አጊንተህ ራስህን ከምታጣ እና እሷን አጥተህ ራስህን ከምታተርፍ የቱ ይበልጥብሃል? ሁለቱንም በራሴ መወሰን አቃተኝ እሷንም ማጣት ፈራሁ ራሴንም ማጣት ፈራሁ። እሷ እንድትወስንልኝ ፈለግኩ። ራሷን ይዛልኝ እንድትሄድ!! ያገባኋትን ቀን ረገምኩ! አብረን ያሳለፍናቸውን ዓመታት ረገምኩ። የሆነ ቀን ያለወትሮዬ እሷን ሳላገባ በፊት አልፎ አልፎ የምሄድበት ባር ሄጄ ስጠጣ ድሮ እንጎዳጎድ የነበረች ኤክስ ተንጎዳጓጄን አገኘኋት። ድንገት የመጣልኝ ሀሳብ ከሷ ጋር ወደቤት መሄድ! ሊፈጠር የሚችለውን አሰላሁ። እንዴት ሴት ይዘህብኝ መጣህ ብላ በተደፈርኩ ትቀውጠዋለች ፣ ምንም ሳይመስላት ታልፋለች ፣ ትቀናለች ፣ ትከሰኛለች ……….. ምንም ሳትል ተነስታ ጥላኝ ትሄዳለች። አንዱ ይሆናል ወይም የቱም አይሆንም ብዬ ሄድኩ። ብቅም አላለችም!! ምንም ዓይነት ከሴት ጋር የመነካካት ፍላጎቱ ስላልነበረኝ ትንሽ እንደተጫወትን ተኛን። በነገታው ከሰዓት ማታ የተፈጠረውን እንዳወቀች የእርሷ ባልሆነ ስርዓት የለሽ ንግግር ነገረችኝ።
እዚህጋ ጥላቻዋ በደንብ ይታይ ነበር። የመከፋት ሳይሆን ከእኔ ከዚህ የተለየ እንደማትጠብቅ ዓይነት ንቀት ያለበት ነበር አነጋገሯ። እንድትጠላኝ አይደል ስፈልግ የነበረው? ደስታ ግን አልተሰማኝም! የዛን ቀን የእረፍቱ ቀን ቢሆንም ዶክተርጋ ደወልኩ። በምልልሳችን መሃል።
«አዲስ! የጥንካሬዬ መሰረት ናቸው የምትላቸውን መርሆችህን ማጣት መጀመርህን እያስተዋልክ ነው? እሷ ከህይወትህ እንድትወጣልህ መፈለግህ አንድ ነገር ነው። ከእርሷ እና ከራሴ ራሴን መረጥኩ አልክ እንጂ እሷንም ራስህንም እያጣህ ነው። ስሜትህን ለመካድ ወይም ለመሸሽ ስትል በጤነኛ ጭንቅላትህ የማታደርጋቸውን ነገሮች እያደረግክ ነው። አልመረጥክም አዲስ!» አለኝ።
ስለእርሷ መሄድ ወይም መቅረት እዚህና እዛ የሚረግጠውን ውል የለሽ ሀሳብ እና ስሜቴን ለማደብዘዝ ስራ እና መፅሃፎቼ ውስጥ አብዝቼ ጠለቅኩ። አብራኝ አትበላም። ላይብረሪም አትመጣም። ከክፍሏ አትወጣም!! አንድ እሁድ ልጆቼ ጋር በሄድኩበት እዛው መጣች። ልጆቼ እሷን ሲያዩ እየተንደረደሩ እናታችን መጣች ብለው ተጠመጠሙባት። በእነርሱ ፊት የተኳረፈ መምሰል ስላልፈለግኩ ጉንጯን ሳምኳት። የሳምኳትን ቦታ በእጇ ዳብሳ ፍዝዝ ብላ ቆመች። ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሳምኳት ነገር። ከልጆቹጋ እየተጫወትኩ ትኩረቴን ከሷ ላይ ማንሳት አቃተኝ። ፍዝዝ ብላ እያየችኝ አይኗ እንባ አቀረረ። ደረስ መለስ የሚለው ፍርሃቴ ተመለሰ። ልጆቹን ማጫወት ትቼ እሷን ማባበል አማረኝ። አሁንም ድረስ አልጠላችኝም። ይሄን ሁሉ አድርጌያትም አልጠላችኝም! የዛን ቀን ተጨማሪ በደል ላልበድላት ለራሴ ቃል ገባሁ! መቆየት እስከፈለገች ጊዜ ትቆይ መሄድ በፈለገች ቀን ትሂድ! አልኩ። ራሴን ረገምኩላትኮ! ከአሁን በኋላ ላልከፋባት ራሴን አስጠነቀቅኩላት!! ማታ ላይ ሻይ ልትወስድ ከክፍሏ ስትወጣ ያለቀሱ አይኖቿ አባብጠው ደፈራርሰዋል። ሳሎን መኖሬን ስታይ እንዳላያት ፊቷን ደበቀችብኝ ግን አይቻታለሁ።»
እያነበብኩ አንገቴ ላይ የሚርመሰመስ እጁን አንድ እጄን ልኬ ያዝኩት። የመከልከል ሳይሆን የመደረብ። የሰርጉ ቀን አጋጣሚ ላይ ስደርስ መጮህ ቃጣኝ።
«የረሳሁትን ሳቋን ተፍለቀለቀች። አውርቶ ሳይጨርስ ይግባባሉ። መቼ ነበር እንዲህ ደስተኛ የነበረችው? እሩቅ!! የማላስታውሰው ቀን ላይ ነበር እንዲህ ስትፍለቀለቅ ያየኋት ! ይሄን ሳቋን ቀምቻታለሁ። በአንድ በኩል ራሴን ረግማለሁ። በሌላ በኩል ደግሞ እንዲህ የተፍለቀለቀችለት ሰው እኔ ብሆን ብዬ አስባለሁ። ሰው እንዴት ሁለት ጠርዝ ላይ ያለ ስሜት እኩል ይሰማዋል? በጣም ስቀርባትም የምትፈጀኝ ስርቃትም የምትፈጀኝ ዓይነት ነገር ናት። መሃል ስሆን ደግሞ እሷን የምጎዳት!! ቀስ ብዬ ወጥቼ ወደቤት ሄድኩ። እቤት ሸኝቷት በሩ ላይ ከመኪናው ስትወርድ አቅፎ ሲሰናበታት አየኋቸው። ፍልቅልቅ ፊቷ አልተለያትም። »
«አንተኮ ቆንጆ ሆነሻል ስላልከኝ ነው እንደዛ ደስ ብሎኝ የነበረው! ለማዕረግ ያልካትን ታስታውሳለህ? ለእኔም የወንድ መለኪያዬ ነበርክኮ አድስዬ! ያንተን ሚዛን ተለካክቶ አይኔን የሚሞላ ማንም አልነበረም! (ለምን ዝም ብለሽ አታነቢም? ዓይነት አየኝ) እሺ ከአሁን በኋላ ዝም ብዬ አነባለሁ!» ብዬው ማንበቤን ቀጠልኩ።

«ውስጤ ያለው ብዙ ስሜት ቢሆንም ጎልቶ የሚሰማኝ ንዴቴ ነው። ማን ላይ እንደተናደድኩ አላውቅም! በትክክል በየትኛው ምክንያት እንደተናደድኩም አላውቅም!! ተነስቼ ወጣሁ። ድብልቅ ያለ አወዛጋቢ ስሜት ናጠኝ። ከሷጋ ለመጨረሻ ጊዜ ከሁለት ዓመት ከምናምን በፊት ለመጨረሻ ጊዜ ካደረግነው ጉድጉድ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነች ሴት ጋር መሆን ፈለግኩ። በትክክል ምን ፈልጌ እቤት እንዲሆን እንደፈለግኩ አላውቅም! አብራኝ ያለችው ሴት የሆነ ነገር ያደረገችኝ ይመስል እንግልት የበዛበት ነገር እያደረግኳት እንደሆነ ገብቶኛል ግን አላቆምም
207 viewsBetslot markos, 15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 20:34:38 «ፊቴን አዙሬብህ አልነበረም! (የዛኔው ህመሜ ከማንበቤ ጋር መጣ) ባለቅስም እንደማታዝንልኝ አስቤ ሳታየኝ በትራሱ ተሸፍኜ እያለቀስኩ ነበርኮ!» አልኩት በቀዘቀዘ ድምፅ። እጁን ሰዶ የኋላ ቤቢ ሄሮቼን መነካካት ጀመረ።

«የትኛው ምን አይነት ስሜት እንደሰጠኝ አላውቅም። ብትጠላኝ እና አልፈልግህም በቃ ብላ ጥላኝ ብትሄድ ደስ ይለኛል። ግን ሙሉ በሙሉ ደስ ይለኛል? በእኔ ምክንያት እንዲህ መሆኗ ደግሞ የሚያስጠላ ስሜት ሰጠኝ። ለተከታታይ ቀናት እኔ ያለሁበት ላለመሆን ወሰነች። ፀሃይን ደህና እንደሆነች ስጠይቃት

«ዛሬ ምንም አትል! ቅድም አየር ልትቀበል ብቅ ብላ ነበር» አለችኝ። ልታየኝ አለመፈለጓን አከበርኩላት!!! ከቀናት በኋላ ግን አባቷ ሞተው በለሊት ደውለው መርዶውን ሊነግሯት ሽማግሌዎች እንደሚመጡ ነገሩኝ! ሳሎን ቁጭ ብዬ ስጠብቃቸው ሊነጋጋ ገደማ መጡ! ገና እሷ መርዶውን ሳትሰማ በፊት እጄ እና እግሬ ሲንቀጠቀጥ ይታወቀኛል። ሳሎን ብቅ ከማለቷ ሰዎቹን ስታያቸው የተፈጠረውን አውቃለች መሰለኝ በቁሟ ተገነደሰች። የሚርበተበት ሰውነቴ እንዴት እንደታዘዘልኝ አላውቅም። መሬቱ ላይ ከመውደቋ በፊት እጄ ደረሰ።

እስከዛሬ የሆንኩትን ሁሉንም በአንዴ ሆንኩት። እናቴ ሬሳ ላይ ስደርስ ከአፌ ቃል አልወጣ ብሎኝ ያማጥኩትን ከነሬሳ ሽታው፣ ማዕረግ ወንድሜ ክፍል ስትሳለቅብኝ ያደረግኩትን ፓኒክ ፣ ማዕረግ ወንድሜን እንዳገባች የእንጀራ እናቴ ከነገረችኝ በኃላ የከደነኝ ጨለማ ……. የለም ብዬ ያመንንኩትን እግዜር ለመንኩላት። <እሷ የምታምንህ አምላክ ካለህ ምንም አታድርጋት! ለእኔ ብለህ ሳይሆን ለእርሷ ብለህ ስማኝ ምንም አትሁን!> አልኩት። ሆስፒታል ተሰናብቻት እንደወጣሁ ታክሲ ጠርቼ ዶክተርጋ ሄድኩ።

. አልጨረስም

t.me/ethiopia2123
t..me/ethiopia2123
t.mec/ethiopia2123
246 viewsBetslot markos, 17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 20:26:32 ከደስታቸው የሚያርቅ መዓት አድርገው ይጠምዱታል። ድህነት ውስጥ ደስታ ያለ ሀብት ደግሞ እንቅልፍ አልባ ለሊቶችን ያቀፈ አድርገው ስለነገሩን ሁሌም ገንዘብ ያለው ሰው ለገንዘቡ ሲል በደልን የፈፀመ እንቅልፍ አልባ ምስኪን ይመስለናል። ያለኝን ህይወት እወደዋለሁ። ማድረግ የምፈልገውን ነገር ማድረግ በፈለግኩ ሰዓት ማድረግ መቻሌን እወደዋለሁ። ከማንም ምንም ፈልጌ አላጎበድድም። ከማንም ምንም ስለማልፈልግ ድንበሬ ይከበርልኛል። ሰውኮ እንዲህ ነው …….. በተለይ በኢኮኖሚ እንደተደገፍከው እና የእሱ መኖር እንደሚያስፈልግህ ሲያውቅ ከሱ በምታገኘው ጥቅም ክብርህን ሊገዛህ ይዳዳዋል። በማጣትህ ሽንፈት ይጠቀምበታል። ገንዘብ ይሄን ነፃት ይሰጥሃል። በማንም በምንም ተሸናፊ ያለመሆንን። ከዚያ በተጨማሪ ገንዘብ ስላለኝ ነው ከእስርት ዓመታት በላይ የጭንቅላቴን ውጥረት ማርገብ በፈለግኩ ሰዓት የምሄድበት ዶክተር ያለኝ። ብዙ በተለያዩ ትራውማ እና የአዕምሮ ህመም እየተሰቃዩ አቅሙ ስለሌላቸው መታከም ያልቻሉ ሰዎች አሉና)

ግንኙነታችን ያሰመርኩትን መስመር መች እንዳለፈ አላውቅም። ከአራት ዓመታት በኋላ የሆነ ቀን እንደተለመዱት ምሽቶቻችን ልንተኛ ስንል የከንፈር ብቻ ያልሆነ መሳም ሳመችኝ። ስትስመኝ ወፍራም ከንፈሯን እወደዋለሁ። የዛን ቀን ከተለመደው ስሜት ውጪ ለእኔ መልዕክት ያደረሰ መሳም ሳመችኝ። አስቁሚያት መሳሟ ለውጥ እንዳለው ስነግራት ለውጡ እንዳልተሰማት ነገረችኝ። የዛን ቀን ለመግለፅ የሚከብድ ቅር የሚል ስሜት ተሰማኝ። የሆነ ያልተለመደ ወይም የረሳሁት ቅሬታ!! ከዚህ ስሜት በኋላ ብዙም ባልራቀ ቀን አልጋችን ላይ ጨዋታና ፍቅር ደርበን እየፈተልን

«እኔ ከዚህ በላይ ማስመሰል አልችልም! ከአቅሜ በላይ ነው የምወድህ!» አለችኝ እንደገረፉት የሁለት ዓመት ህፃን ልጅ ህቅ ህቅ እያለች። የሆነ መኪናዬን እየነዳው ተጋጭቶ ኤርባጉ ተነፍቶ ፊቴን ሲጠልዘው ያለው ዓይነት ስሜት ነው የተሰማኝ። ያ ስሜት እንደነበራት ባትነግረኝም አውቀው ነበርኮ የማላውቀው ከአፏ ሲወጣ እኔጋ ሊፈጥር የሚችለውን ስሜት ነበር። እንጂማ ብዙ የማውቃቸው ሴቶች ብለውኛል። የማናቸውም እኔጋ የፈጠረው ስሜት አልነበረም። የተሰማኝ ፍቅር አይደለም። ፍርሃት ነበር።»

(ይሄን ሳነበው ልቤ ዝቅ ሲልብኝ ተሰማኝ!!)

«ማብራራት የሚከብደኝ የማጣት ዓይነት ፍርሃት ፤ ላላስታውሰው ረስቼዋለሁ ያልኩት ድሮዬ ላይ የማውቀው የመለየት ፍርሃት ፤ የዛሬውን አዲስ ከአንድ ጠጠር እና አሻዋ ጀምሬ ከመገንባቴ በፊት ሰውነቴን የወረረኝ መሸነፍ!! የምትፈልገውን እንድታደርግ እና በፈለገችው ቁልምጫ እንድትጠራኝ ፈቅጄላት የመጨረሻዬ እንደሆነ የወሰንኩትን ፍቅር ሰራን። ደረቴ ላይ ሆና የፈገገ ፊቷን ሳትመልሰው እንቅልፍ ወስዷት ምን እንደማደርግ ሳስብ አደርኩ። ከራሴ በላይ እንዳላጣው የምሳቀቅለት ነገር እንዲኖረኝ አልፈልግም!! ከማዕረግ በኋላ ያለው አዲስ ስሜቱንም ውሳኔውንም ለማንም ለመናገር አይደለም ሊፈራ ሁለቴ አያስብም ነበር። አዲስ ፍርሃትን ከላዩ ከገፈፈ ዓመታት ተቆጥረዋል። የተሰማኝን ልነግራት መጨነቄ ይበልጥ ያለሁበትን ሁኔታ እንድጠላው አደረገኝ።

የኑሮ ዋና መርሄን ተፈታተነችው! በስሜቴ ከእኔ ውጪ ማንም አያዝበትም የሚለውን!! አዲሱ አዲስ ስሜቱ ራሱ የሚያዘው ፤ ማንም የማይሰለጥንበት ነው። አልነገርኳትም! በነገታው የእርሷን በቅርቤ መኖር ጠላሁት! ራሴን እንዳላዘው እየሆንኩ እንደሆነ ገባኝ። ትቻት ሌላ ክፍል ተኛሁ። እንቅልፍ ግን አልወሰደኝም። በመሃል በሩን ከፍታ መኖሬን አረጋግጣ ስትመለስ እሰማታለሁ። ሲነጋላት መጥታ

«……… ላፍቅርህ ብዬ ነው ወይ ያፈቀርኩህ? ለምን ትቀጣኛለህ?» ስትለኝ ውስጤ ሲረበሽላት ሰማሁት። ከማዕረግ ውጪ ለማንም ያልሆንኩት መሆን ስሆነው ታወቀኝ። ያ ስሜት ደግሞ ከደስታው በላይ ስቃይ እና ሰቀቀኑ ነው ትዝ የሚለኝ። «እንፋታ» ስላት ራሴን ሰማሁት። ከዛ በኋላ ለሳምንታት ከልቧ ልታወጣኝ እየታገለች መሰለች። አብራኝ መዓድ ብትቀመጥም ብዙ አታወራም!! ያሰብኩት ወይም የተመኘሁት ልክ እንዳልሆነ ፀዲ ስትደውልልኝ ገባኝ! ፀዲ የደወለችልኝ ቀን እራት ላይ ፀዲጋ እንደሄደች ስትነግረኝ የማውቀው ነገር በመሆኑ አልተገረምኩም። የተገረምኩት አድርጋ የማታውቀውን ሜካፕ እና ሊፒስቲክ ፊቷ ላይ ማየቴ ነበር። እቤት ውስጥ በቱታ ወይ በቁምጣ አልያም በኔ ቲሸርቶች እንጂ የማውቃት ቀሚስ ለብሳ አላስታውስም! የእኔን ትኩረት ለመሳብ መሆኑን ሳስብ አሳዘነችኝ። ያንን ግን እሷ እንድታውቀው ማድረግ አልፈለግኩም። በነጋታው ሀኪሜጋ ሄጄ የተፈጠረውን ነገርኩት።

«ወደሃታል! በፍቅር መሸነፍን እንደድክመት የምታይበት የራስህ በቂ ምክንያት አለህ ያን እረዳልሃለሁ! ግን ይህችኛዋ የተለየች ብትሆንስ? ከመስበር ይልቅ የምታጎብዝህ ብትሆንስ? ከእውነቷ የምታፈቅርህ ብትሆንስ? » አለኝ

«ዶክተር ባትሆንስ? ብትሆንስ በሚል ግማሽ እምነት ባትሆን የማጣውን መቋቋም አልችልም።»

«በባትሆን ፍርሃትህ በፍቅር ውስጥ ያለውን ደስ የሚል ህይወት ራስህን እያሳጣኸው ነውኮ! ራስህን እየቀጣኸው ነው!»

«am fine ፍቅር በሚሉት ግማሽ ደስታ ግማሽ ሰቀቀን ያለበት እሳት መጫወት ለጊዜው ምርጫዬ አይደለም። ደስታው ይቅርብኝ እና ሰቀቀኑንም ይዞልኝ ይሂድ!» አልኩት ተነስቼ ቢሮው ውስጥ እየተንጎራደድኩ።

«አዲስ! እንዳንተ በጥንካሬ የማይታለፈውን ያለፈ ሰው አላውቅም። የምትኖራቸው ህጎች እና መርሆች ስለፈወሱህ I appreciate that! ከነዚህ ዓመታት በኋላ እንኳን ይሄን ሁሉ በራስ መተማመንህን እና የገነባኸውን እውቀት የሚከድን ፍርሃት ካነቀህ አሁንም ከትናንት ህመምህ አልዳንክም! ስለሸሸኸው ደግሞ አታመልጠውም! እባክህ አስብበት! ደጋግሜ ከዚህ በፊት እንዳልኩህ እሱን ፋይል ገልጠህ ለማውራት ራስህን አዘጋጅ!» አለኝ

ያን ህመም ቀስቅሼ ላወራ መቼም አልዘጋጅም!! የሬሳ ሽታ፣ የጨለማ ጣር ፣ የሚያደነዝዝ ድምፅ……… ያለበትን ፋይል ከፍቼ መተንፈስ አቅቶኝ መንፈራገጥ የቅርብ ዓመታት እቅዴ ውስጥ አልነበረም!! ወደቤቴ ተመልሼ ላለፉት ሳምንታት እንደተለመደው ዓይነት መግባት መውጣቴን ቀጠልኩ። የሆነ ቀን እራት ላይ ሳትመጣ ቀረች። ፀሃይን እንድትጠራት ስጠይቃት።

«አሟታልኮ ተኝታ ነው የዋለችው! አላስተዋልካትም እንጂ ምንም ደህና አይደለችምኮ! እንደው በማያገባኝ መግባት አይሁንብኝና እንደው በመሃከላችሁ ምን ክፉ ዘልቆ ነው?»

«ገባሽ ፀሃይ! በማያገባሽ ገባሽ!» ብያት ወደመኝታ ቤት ላያት ሄድኩ። ስታለቅስ እንደዋለች ታስታውቃለች። እንፋታ ካልኳት ቀን በኋላ በትኩረት ያየኋት የዚህን ቀን ነው። ከሰውነቷ መክሳት የፊቷ መገርጣት አስደነገጠኝ። አጠገቧ ሄጄ ስነካት ታተኩስ ነበር። እጠይቃታለሁ። አትመልስልኝም! ክፍሏ በታመቀ አየር ተሞልቷል። መስኮቱን እየከፋፈትኩ ሀኪም ቤት እንድወስዳት ደጋግሜ ጠየቅኳት። ቃል አልመለሰችልኝም። ፊቷን አዙራ በትራሷ ተሸፈነች። እራሴን ከመውደዴና ከፍርሃቴ ያየለ ስሜቴ አቅፌ ምን ሆንሽብኝ? ሁላ ልላት እያመነታብኝ ተንጎራደድኩ። ኮቴዬን እየሰማች እስክወጣላት እንደምትጠብቅ ነገር በትራሷ እንደተከለለች ዝም አለች። ይሄኛው አዲስ ስሜቱን መለየት ተቸግሮ አያውቅም ነበር። ዝብርቅርቅ ያለ ስሜት ተሰማኝ። ጠልታኛለች ልታየኝም ልታናግረኝም የማትፈልግበት ደረጃ ደርሳለች። ግን ደግሞ ብትጠላኝ እንዲህ ትጎሳቆል ነበር
186 viewsBetslot markos, 17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 20:21:56 ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል ሀያ አንድ…………….. meri feleke)

ፅፎ እስኪጨርስ እረፍት አጣሁ። አስሬ ላይብረሪ እመላለሳለሁ። ጣቶቹ አሁንም 100% ስላልሆኑ ቀስ ብሎ ነው የሚፅፈው።
«እሺ የፃፍከውን ላንብበውና ትቀጥላለህ?» እለዋለሁ።
«አይሆንም ህፃን አትሁኚ!» ይለኛል።
«ጮክ ብለሽ አታንብቢልኝ! የምትጠይቂኝ ነገር ከሌለ በቀር! ለራስሽ አንብቢው» ብሎኝ ሶፋው ላይ አጠገቡ እንድቀመጥ በእጁ እየመታ አሳየኝ። መስገብገቤ የሆነ እርቦት ውሎ ምግብ እንደሰጡት ርሃብተኛ ነው።

«ከድምፅ ጋር የተለየ ፍቅር አለኝ። ሰውን ሳላየው በድምፁ ብቻ መልክ እስላለሁ። ከድምፁ ቃና ፐርሰናሊቲውን መገመት ደግሞ የበለጠ ደስ ይለኛል። ሬስቶራንት ውስጥ ከጀርባዬ ድምፅዋን ስሰማው ጠይም ጎራዳ ፣ ጥርት ያለቆዳ ያላት ፣ ጥርሷ የሚያምር ፣ ከንፈሯ ስስ ……… ገመትኩ። ድምፅዋ ውስጥ የዋህነት ደግሞ ለዛ ሙሉነት ነበር በመጀመሪያ የሰማሁት። ዞሬ ሳላያት ከውጪ ከመጡ ተለቅ ያሉ ሴት ጋር ስታወራ ድንገት ድምፅዋ ወደ ቁጣ ሲቀየር ግን ቃላቶቿን ደምሬ ስሰማት የሆነች መብረር ፈልጋ ክንፎችዋን የፊጥኝ የተያዘች ነፍስ ያላት ሴት …… እድሉን ብታገኝ እልም ብላ የምትበር ዓይነት። ሲትየዋ ጥለዋት ሲሄዱ ዞሬ አየኋት እና ወንበር ቀይሬ አጠገቧ መጣሁ። መልኳን ከከንፈሯ እና ከቀለሟ ውጪ ብዙ አልሳትኩም። ቀይ ናት የጎራዳ ውብ፣ ቆዳዋ ከመጥራቱ የተነሳ ውሃ ስትጠጣ በረዥሙ አንገቷ ወደሆዷ ሲንቆረቆር ውሃው ኩልል ብሎ የሚታይ የሚመስል። ከንፈሯ ብዙ ስጋ የፈጀ አበባ የመሰለ ፣ ጥርሷ በድዷ ጥቁረት ደምቆ የሚያጥበረብር ፣ ሴት ልጅ ከኋላ የፀጉሯ ማብቂያጋ የተደፉ ሉጫ ፀጉሮች ሲኖሯት ባላውቃት እንኳን እጄን ሰድጄ መንካት ይቃጣኛል። እሷ ደግሞ ወደላይ ባስያዘችው ጥቁር ፁጉሯ ጆሮዋ ስር ድረስ ለጥ ብለው ንካኝ ንካኝ የሚሉ ሉጫ ፀጉሮች ነው ያላት። የዓይኖቿን ውበት ውስጡ በጉልህ የሚነበበው ሀዘን አደብዝዞታል።

ስለስብዕናዋ ግን ሁሉንም ልክ ነበርኩ። ለመነበብ የማትከብድ ያልተወሳሰበች፣ የዋህ፣ ለዛ ሙሉ፣ ልዝብ ያለች ፣ ስርዓት ያላት ግን ደግሞ ግልፅ ነገር፣ ባህልን ባታምንበትም ለቤተሰብ እና ለማህበረሰብ ግምት ብላ የምትኖርበት፣ ሀይማኖትን ግን አምናበት የምትከተል (ብዙ የማውቃቸው ሰዎች ሀይማኖት ያላቸው ሲኦል እና ገነት አለ ስለተባሉ ነው። ከክፋት የሚቆጠቡት ሲኦልን ፍራቻ እንጂ መልካም መሆን ምንም ሽልማት የለውም ክፉ መሆንም ምንም ቅጣት የለውም ቢባሉ ለክፋት የሚግደረደሩ ናቸው። በሰውነት ሰው ስለመሆን ሳይሆን እግዚአብሔር ወይም አላህ ወይም ሌላኛው አምላክ በክፋታቸው ይቀጣናል ፤ በመልካም ስራቸው ይሸልመናል ብለው ስለሚያምኑ ነው ሚዛን የሚሰሩት። እስኪ እውነት እናውራ ከተባለ የብዙ ሀይማኖቶች መደምደሚያ ከሞት በኋላ ያለ ሽልማት ወይ ቅጣት ባይሆን ምን ያህል ሰው ሀይማኖት ይኖረው ነበር? ምን ያህል ሰው ቅዱስ የሚለውን ስራ ለመስራት ይጋጋጣል? ምን ያህሉስ ሰው ወደሀይማኖት ተቋማቱ እየሄደ አቴንዳንስ ያስመዘግብ ነበር?) የሷን ሀይማኖተኝነት የምወድላት ቅጣትን ከመፍራት እና ሽልማትን ከመሻት ባለፈ አምላኳን በየቀን ህይወቷ ታምንበታለች።

እያወራን ሳለ የምትኖርበት ትርጉም ያጣች ጣዕም አልባ ነፍሷን ሰማኋት። ማምለጥ እየፈለገ የታነቀ ስብዕናዋን አየሁት። ሙሉ አደርጋታለሁ ብዬ አስቤ አይደለም። በህይወቴ ውስጥ ከዚህ በፊት የነበሩት ሴቶች ከሰጡኝ የተለየ የምትጨምርልኝም ነገር አለ ብዬ አስቤ አይደለም። እሷ ቤተሰቦቿን የምታስደስትበት ባል ትፈልጋለች። እኔ ደግሞ አጉል ባልከረረ ትስስር ቀኔን የምታጅብልኝ ሴት እፈልግ ነበር። የዛኑ ቀን እንጋባ አልኳት። በዛ ላይ በየቀኑ የምነካው የኋላ ቤቢ ሄር አላት። እያወቅኳት ስመጣ ባወቅኳት በደቂቃዎች ውስጥ እንድታገባኝ መጠየቄ ልክ መሆኑን አወቅኩ። ምንም ነገር ላይ የተሰማትን እና ያመነችበትን አስተያየት ከመስጠት ወደኋላ አትልም። የማታውቀውን ነገር አላውቅም ለማለት አታፍርም! እንደአዋቂ ለመታየት እና እኔን ለማስደመም ቅንጣት አትሄድም። ጠያቂነቷን እወድላታለሁ። ትጠይቃለች። መልሴ ካላሳመናት ለምን አዳር አይሆንም ትጨቃጨቀኛለች። ጭንቅላቴን ስለምትፈትነኝ ከሷ ጋር የማሳልፈውን ጊዜ እወደው ነበር። ገና ሳንጋባ አንድ የኑሮ ህጌን አስፈረሰችኝ። ሰውን እርዳታ መጠየቅ! ልታገባኝ ስትስማማ ሰርግ እፈልጋለሁ አለችኝ። ምክንያቷ ለራሷ ከእገሊት የተሻለ ሰርግ ነበረኝ ለማለት ወይም ሰርግ በራሱ ትርጉም የሚሰጣት ነገር ስለነበረ አልነበረም። በቤተሰቦቿ አይን ለመሙላት ፣ አጎደልኩባቸው ብላ ያሰበችውን ለመካስ ፤ ውርደታቸው ሆንኩ ብላ ያሰበችውን ክብር ልትደርብላቸው፣ በሷ ሰርግ እነርሱን ለማድመቅ ነበር እና እውነት ለማውራት አሳዘነችኝ። ሰው በ34 ዓመቱ የራሳቸውን ህይወት ኖረው ላገባደዱ ቤተሰቦቹ ይኖራል? ማስደሰት አንድ ነገር ነው። እሷኮ የህይወት ግቧም ፣ ስኬቷም ፣ ደስታ ሀዘኗም፣ ህልሟም፣ ትርጉሟም እነርሱ ናቸው። ዘመኗን ሙሉ በፈጠሩባት የትንሽነት እና የከንቱነት ስሜት ለእነርሱ ኖራ ራሷን ፕሩቭ ካላደረገች (የማለፊያ አረንጓዴ መብራት ካላሳይዋት) የራሷን ኖሮ መኖር እንደማይገባት ለራሷ አሳምናለች። እንኳን የራሴን ሰርግ ልደግስ የሰው ሰርግ የማልታደም ሰው ሰርግ ልደግስላት ተስማማሁ። ችግሩ ከእኔ ወገን የሆነ ሰርጌን የሚያጅበኝ ዘመድም ሆነ ጓደኛ አልነበረኝም። ወይም ማንንም በዛ ልክ ማቅረብ አልፈልግም።

የእኔ ሚዜ አልባ መሆን ወይም ዘመድና ጓደኛ አለመኖር ለሰርጉ የነበራትን ደስታ ወደጭንቀት ቀየረባት። ይሄም ለራሷ አልነበረም!! ዘመድ አልባ ባል አገባች ብለው ቤተሰቦቿ እንዳያዝኑባት እንጂ! 34 ዓመት አልጨበጥ ብሏት ስታሳድደው የኖረችውን ህልሟን በሳምንታት ላስቀይራት አልችልም ነበር። በህይወቴ ውስጥ ከምጠላቸው ዋና ዋና ነገሮች ውስጥ አንዱን አደረግኩ። ስራ ቦታ አብረውኝ ብዙ የሰሩ የስራ አጋሮቼን ሚዜ እንዲሆኑኝ ጠየቅኩ። በእርግጥ ከስራ ውጪ ማርስ ላይ ልደር ወይ ጎዳና፣ ሚስት ይኑረኝ ቅምጥ ምንም መረጃ ለሌላቸው ለብልጫዎቹ የስራ ባልደረቦቼ የቅርበት ምልክት አድርገው ስለወሰዱት በደስታ ነበር የተቀበሉኝ። የስራ ህይወቴን እና የግል ህይወቴን ማዳቀል የፈጠረብኝን መወላገድ ድጋሚ ልደግመው ስለማልፈልግ የግል ህይወቴን በአድራሻም በወሬም አርቄ ነው ያኖርኩት የነበረው። ተጋባን!!

መጀመሪያ ላይ ድንበሩን የጠበቀ፤ ያልከረረም ያልላላም፣ ያልሳቀም ያልተኮሳተረም፣ የማያቃጥልም የማይበርድም ዓይነት ትርጉም የነበራቸው ዓመታት ነበረን። እንደአብዛኛዋ ሴት ስም ያለው ቦርሳ መሸመት ፤ አዲስ የወጣ ፋሽን ልብስ እና ጫማ አሳዶ ማጌጥ ፣ አዲስ በተከፈቱ ሬስቶራንቶች መታየት ፣ ፊቷን ሜክአፕ ለመሰራት ጊዜ መፍጀት …….

አታውቅበትም። የመኪና መንጃ ፈቃድ እንኳን ያወጣችው እኔ ጨቅጭቄያት ነው እንጂ ራሴው ነበርኩ የማመላልሳት። ከመሰረታዊ ነገሮች ውጪ ገንዘብ ካወጣች ባትነግረኝም አውቃለሁ። ለቤተሰቦቿ ነው!! ገንዘብ አንዱ የነፃነት በር መሆኑን ባውቅም ከሚያስፈልገኝ ውጪ ባለ ትርፍ ገንዘብ የሚያሳምነኝ ምክንያት ይሁን እንጂ አልሳሳም። ለፍቼ ያመጣሁት ገንዘብ ነውና ሚዛን በማይደፋ ምክንያትም እንዲበተን አልፈቅድም። (ገንዘብ የነፃነት በር ነው ያልኩት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለነፍሳችን አስተዋዕፆ ስላለው ነው። እንደአለመታደል ሆኖ ሀይማኖቶቻችንም ሆኑ ባህሎቻችንን ድህነትን የሚያሞካሹ እና ገንዘብን ልክ ከአምላካቸው ወይ ከስርዓታቸው ወይም
159 viewsBetslot markos, 17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ