2022-08-27 10:41:08
" Filter ያልነካቸው "
ኤልያስ ሽታኹን
(የልደት ዳር ጨዋታ)
~ ~ ~ ~ ~
እንደክርቶስ ሐሙሴ ይመጣል::
"ይቺ ነገር ትለፈኝ "የምልበት ::
ደመም ላብም ብቻዬን የማፈስበት::
የአትክልት ስፍራው ከኤርታሌ ብሶ የሚያቃጥለኝ ቀን አለኝ::
እስከዛው ትርካ ....
አምዳምነቴ ልክ አልነበረውም::
እንዚህ ቀናቶች ለሰው የገረጡ ለኔ ግን ያጌጡ ናቸው::
አራት ኪሎ
- የሰካራም ልጅ የተባልኩበት
- የድሀ ልጅነቴ ስታይ የማስታውቅ እኔ
- ጉልበተኛ ሀብታም ጎረቤት
- ዉኃ የሚነጠባጠበት ቤት
- የልጅነት ፀብ (አንዳንዶች አርጀተውም እኔን ለማሳፈር ይመዙልኛል)"እንዲህ ብለህ ነበር"ይላሉ
- ፅዋ ማህበር (አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ)
- ውድድር
- ትልቅ ህልም ትንሽ አቅም
- መጨረሻቸው ለሊት የሆኑ ወኮች
- የክበብ ሽኩቻዎች
- ጅንጅና ስልት ንድፎች
- ያወቁትን ቤት መጥቶ ማውራት (ጥሩ ቦታ ነው የሚውለው እንዲባል)
- ከእኩዮች ጋር አንድ አይነት ፋሽን መስራት....
ይሄ ሁሉ በህሊናና በልብ የቀሩ ማስታወሻዎች ናቸው::
ዛሬ ደሞ ለሰው ውብ ለራስ ግን ኮሽኳሻ ናቸው::
- ገላዬ ቆሽሾ በድንጋይ እህቴ ታላቅ እህቴ (ደርግ በሏት) ብረት ምጣድ ላይ እያጋጨች ፈተገችኝ::
"ማንን ለማሰድብ ነው" እያለች::
ጎረቤት አይሰማት ሰደበችኝ::
"ሰፈሩ እንደሆነ ቡዳ ነው"
"እኔ እኮ..."ላስረዳ ስሞክር ወኃውን ሳየው ጠቁሯል:: እድፌ ጭቃ ያህል ወፍራም:: ዝም ::
“ደሞ ባንተ እንሰድብ ወይ”
(“ድው” ከብረት ምጣድ ጋር ታላትመኛለች)
እልህ ዕንባ ነበራት:: አሁን ሳስባት ታሳዝነኛለች::
ምንበላው አልነበረንም ግን ስማችን አሳሰባት እና ጉልበቴ እስኪላጥ አሸችኝ::
ልክ እንደነዚህ ወዝም ደርዝም የሌለው የሚመስል እልፍ ቀን አለኝ
@ethiopia2123
@ethiopia2123
257 viewsHáŷmî, 07:41