Get Mystery Box with random crypto!

ታደሰ ደምሴ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopia2123 — ታደሰ ደምሴ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopia2123 — ታደሰ ደምሴ
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopia2123
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

ሥነ_ግጥም
ግጥሞችን በዩቱብ ለመከታተል👇👇👇
https://youtube.com/@maryam2116

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 08:49:52 የእውር ጉዞ ፣
የጅል በለስ
"ውሃ ቅዳ ፣
ውሃ መልስ"


@ethiopia2123
150 viewsአበሜሌክ ዘጎጃም, 05:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 12:24:43 ያልታደለች ሀገር
(ታደሰ ደምሴ)
እንዲህ አልነበር ወይ...
ሀገር ህዝብ ይወልዳል፣
ህዝብ ሰው ይተካል፣
አብራክ ለወግ ሲውል አሳዳጊ ይከብራል...
በእንዲህ አይነቱ ጡብ አገር ይገነባል!
ሀገር ይታነጻል!

እቺ የኛ ሀገር...
ወጠጤ ወጠምሻ ጨበሬ ልጅ ወልዳ
ወልዶ በመክበር ትክ በልጅ አየች ፍዳ!

እዝጎ

#ሼር
@ethiopia2123
256 viewsአበሜሌክ ዘጎጃም, edited  09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 11:45:01 አሮጊቷ አገሬ...
(ታደሰ ደምሴ)

ድሮ...
ያልተማሩ ምሁር በእንዝርት እየዳጡ በጥበብ ሸመኑሽ
ልዕልናሽን ሽተው፣
ክብርሽን አግዝፈው፣
በጽኑ ክንዳቸው ማማ ላይ ሰቅለውሽ!
ቅጽርሽ ሳይደፈር እልፍ ዘመን ዋጀሽ!

ከዛማ በኋላ ...
ስምሽ ሲቀማጠል
ዘመን ሲቀባበል
የሆነ ወቅት ላይ ከጊንጥ ተዛመድሽ
ከጊንጥ ተጋባሽ
ከመልክሽ ያልመጣ ተኩላ ቢጤ ወለድሽ!

ከዛማ በኋላ...
አንቺም እንደሰው ፊት ወረት ወግሽ ሆነ!
የወለድሽው ድቃይ፣
ፈቃድሽን ተችሮ በምድርሽ ዘመነ!
ከእልፍኝሽ አዳራሽ በወግ ሰለጠነ!

ከዚያን ቀን ጀምሮ...
ጠቦቶቻቸውን የተቀሙ ሁሉ ለክስ ሲወጡ
በቀበሮ ችሎት፣
በእከከኝ_ልከክህ በጎችሽ ፍርድ አጡ!

ይሔው...
እልፎች ተሰውተው
ስጋ ደም ገብረው
በአጥንታቸው ካሳማ ማማ ላይ ቢሰቅሉሽ
ዘመን ያመጣቸው፣
ወረት የሾማቸው፣ ዲቃላ ልጆችሽ
ካስማሽን ነቅንቀው ዘጥብያ አወረዱሽ!

ይበልሽ...!
ይበልሽ...!
ከማ'ፀንሽ ወጥቶ ለሞትሽ የሚሞት አብራክ ሳይቸግርሽ
በአመንዝራ ቅሌት መርዛም ገላ ታቅፈሽ ማን ተጋደሚ አለሽ!

እይልኝ ጉድሽን...
"እረኛ ሁን" ያልሽው ከእሪያነት ያነሰ
ከበላተኞች ጋር መንጋውን ጨረሰ!

ይብላኝለት ለዛ...
ሙሴ ላጣው ህዝቤ ዘመን ላኮረፈው
በጅል የቅናት ፍሕም ለሚለበለበው!

ይብላኝነት ለዛ...
ህግ ባለባት ሀገር
"በህግ አምላክ" ብሎ ጮሆ ላልተሰማ
በስልጣን ጥማት ጦስ፣
ከቀየው ለሚጋዝ፣
በመከራ ገፈት ነፍሱን ለሚቀማ!

ይብላኝነት ለዛ....

#ሼር

@ethiopia2123
@ethiopia2123
@ethiopia2123
301 viewsአበሜሌክ ዘጎጃም, edited  08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 10:41:08 " Filter ያልነካቸው "
ኤልያስ ሽታኹን
(የልደት ዳር ጨዋታ)
~ ~ ~ ~ ~
እንደክርቶስ ሐሙሴ ይመጣል::
"ይቺ ነገር ትለፈኝ "የምልበት ::
ደመም ላብም ብቻዬን የማፈስበት::
የአትክልት ስፍራው ከኤርታሌ ብሶ የሚያቃጥለኝ ቀን አለኝ::

እስከዛው ትርካ ....

አምዳምነቴ ልክ አልነበረውም::

እንዚህ ቀናቶች ለሰው የገረጡ ለኔ ግን ያጌጡ ናቸው::
አራት ኪሎ
- የሰካራም ልጅ የተባልኩበት
- የድሀ ልጅነቴ ስታይ የማስታውቅ እኔ
- ጉልበተኛ ሀብታም ጎረቤት
- ዉኃ የሚነጠባጠበት ቤት
- የልጅነት ፀብ (አንዳንዶች አርጀተውም እኔን ለማሳፈር ይመዙልኛል)"እንዲህ ብለህ ነበር"ይላሉ
- ፅዋ ማህበር (አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ)
- ውድድር
- ትልቅ ህልም ትንሽ አቅም
- መጨረሻቸው ለሊት የሆኑ ወኮች
- የክበብ ሽኩቻዎች
- ጅንጅና ስልት ንድፎች
- ያወቁትን ቤት መጥቶ ማውራት (ጥሩ ቦታ ነው የሚውለው እንዲባል)
- ከእኩዮች ጋር አንድ አይነት ፋሽን መስራት....

ይሄ ሁሉ በህሊናና በልብ የቀሩ ማስታወሻዎች ናቸው::
ዛሬ ደሞ ለሰው ውብ ለራስ ግን ኮሽኳሻ ናቸው::

- ገላዬ ቆሽሾ በድንጋይ እህቴ ታላቅ እህቴ (ደርግ በሏት) ብረት ምጣድ ላይ እያጋጨች ፈተገችኝ::

"ማንን ለማሰድብ ነው" እያለች::
ጎረቤት አይሰማት ሰደበችኝ::
"ሰፈሩ እንደሆነ ቡዳ ነው"
"እኔ እኮ..."ላስረዳ ስሞክር ወኃውን ሳየው ጠቁሯል:: እድፌ ጭቃ ያህል ወፍራም:: ዝም ::

“ደሞ ባንተ እንሰድብ ወይ”
(“ድው” ከብረት ምጣድ ጋር ታላትመኛለች)
እልህ ዕንባ ነበራት:: አሁን ሳስባት ታሳዝነኛለች::

ምንበላው አልነበረንም ግን ስማችን አሳሰባት እና ጉልበቴ እስኪላጥ አሸችኝ::

ልክ እንደነዚህ ወዝም ደርዝም የሌለው የሚመስል እልፍ ቀን አለኝ

@ethiopia2123
@ethiopia2123
257 viewsHáŷmî, 07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 13:28:24 የባከኑ ህልሞች

መተኛት አልሻም ማለም እፈራለው
ይሄን ያንን ሳስብ ሳልተኛ ነቃለው
መናገር ያሰበው ለማይገባኝ ቅኔ
ማለምን አልሻም ያንች ወዳጅ እኔ
ከሁሉ ከሁሉ ፈራለው ምኝታ
ህልም ብሎ እያሳየ ስለነሳኝ ፋታ

ህልም ነው እያለ አንቺን ያሳይሻል
በቢጫ ቀሚስሽ ስትበሪ ይስልሻል
ፀጉርሽን ነስንሰሽ ስትስቂ ያመጣሻል
ግን ልነካሽ ሳስብ መልሶ ያጠፋሻል
እኔ አንችን ልነካ ሲቀረኝ በሳንቲ
ሚሰውርሽ ከቶ ምን ሊያገኝ ነው እስቲ

እናም ምኝታየን እፈራለው እኔ
ህልም ብሎ እያሳየኝ የማልፈታው ቅኔ
እሳቀቅ ጀመረ ቢያርቅሽ አቅርቦኝ
ፍራሽም መቃብር እንቅልፍም ሞት መስሎኝ
እናምልሽ ውዴ....
አሁን ላይ ሳስበው የፍራቴን ነገር
ለካ አንቺን ማግኘቱ ይበልጥብኝ ነበር

ሰሞኑን ስነሳ በሰላም ተኝቼ
ይናፍቁኝ ጀመር የባከኑ ህልሞቼ።

በአቤኒ የተጻፈ


@ethiopia2123
279 viewsHáŷmî, 10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 22:14:20 አንደኛው ሰው ላንዱ

በቀን ወይ በሌሊት
በጾም በቅበላ
የበላ ይኖራል፥ ይብላኝ ለተበላ
ጋጋሪው ቢራቀቅ፥ ቢሰወር ምጣዱ
የለት እንጀራ ነው፤ አንደኛው ሰው ላንዱ ::

              #በእውቀቱ_ስዩም

@ethiopia2123
282 viewsአበሜሌክ ዘጎጃም, 19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 22:11:30 "ሸራተንም አደርህ
ሼራ ቤት መንጋቱ አይቀርም"
273 viewsአበሜሌክ ዘጎጃም, 19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 20:54:02 እራሴን አፋልጉኝ
(ታደሰ ደምሴ)

የሐምሌ ወር ጉም ነኝ ...
ያለሁ የምመስል አሻግሮ ለሾፈኝ
ገመናየ ባዶ...!
ነፍስ የሌለው ነፋስ ባሻው እያጋዘ ባሻው የሚያተነኝ!
:
:
"ጋግረነዋል!" ያሉ፣
መብሰሌን ተስፋ አርገው እልፎች ሲጠብቁኝ
እንኳንስ ልጋገር፣
እንኳንስ ልበስል፣
ከ'ቧቃ ሳልደርስ ወፍ እብስ ያረገኝ
የወፍጮ አፍ የተፋው የቋት ስር ዱቄት ነኝ!

እራሴን አፋልጉኝ ...!

ይሔው ባለመኖር፣
መኖርን ከከጀልሁ ብዙ ዓመት ተቆጥሯል!
ብዙ ወርህ ነጉዷል!
አዕላፍ ሰዓት ከስሯል!
ታዲያ...
"አለህ!" አሉኝ እንጂ፣
ተስፋ ደስታን ችሮኝ "ኖርሁ!" የምለው የታል!?

እራሴን አፋልጉኝ...
ከመታገል ልውጣ ከመኖር ልወዳጅ
ባስለቃሾቸ ፊት፣
እምባየን ገፍትሬ ፈገግታን ልቀዳጅ!

ለምክንያት ተፈጥሮ፣
እድሜ ባጉል ሲወድም እጅጉን ይቆጫል
እራሴን አፋልጉኝ!፣
ነገንኳ ልኑር! "ትናንትናስ" ከስሯል!

በቀሪ እድሜየ ላይ
ከእርጅና ፊት ጋ ህልሜ በስሎ ይታይ!

በመንጋ እየታሸሁ፣
በመንጋ እየታወርሁ፣
በባዶ በርሜል ወግ ዘመን ማክሰር ይብቃኝ
ከእኔነት ጨው ይውጣ፣
መራራየ እረክሶ ኑረት ይጣፍጥልኝ!
:
:
.... እራሴን አፋልጉኝ !

#ሼር

@ethiopia2123
340 viewsአበሜሌክ ዘጎጃም, 17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 16:44:27 #ቀን_ገንቢ
ምዕራፍ ፩ : ክፍል ፪


ሁለት ዘሮች
--------------


ሁለት ዘሮች ናቸው፡፡ በአካባቢው የተፈጠረ ንፋስ ከቅርፊታቸው ነጥሎ እያንሳፈፈ አጓጉዞ በላመ፣ በለሰለሰ አፈር ላይ ጎን ለጎን ቀላቀላቸው፡፡ ዘሮቹም ከለሰለሰ አፈር ላይ ማረፋቸውን በተረዱ ጊዜ በጉርብትና መንፈስ ውይይት ጀመሩ፡፡

አንደኛው ዘር፡ “በዚህ በእንደዚ ለመብቀን በተዘጋጀ ማሳ ላይ ሳርፍማ መብቀን እፈልጋለሁ፡፡ ሥሮቼንም ወደ ጥልቁ አፈር  በመላክ፤ ቅርንጫፎቼን ከምድር በላይ ከፍ አድርጌ እንደ ባነር በመዘርጋት የበልግ ወራት መድረሱን፤ ልምላሜ መምጣቱን ማወጅ ይገባኛል፡፡ የጠዋቷን ፀሐይም የተፈጥሮ ስጦጣየን መመገብ ይገባኛል እፈልጋለሁም፡፡” ሲል ሀሳብን ለባልጀራው ሰነዘረለት፡፡ እናም በቅሎ ማደግ ጀመረ፡፡

ሁለተኛው ዘርም በፈንታው እንዲህ አለ፡ መጀመሪያ ሀሳቡን ህምምም.. ሲል በመደመም ጀመረ፡፡ “ስሬን ወደ ጥልቁ አፈር ብለቀው በዛ ጨለማ ውስጥ ምን እንደሚገጥመኝ ከየት አውቅና ነው! ጉንቁሎቼን ባጎነቁልስ የቀንድ አውጣ ምግብ መሆኔ አይደለምን! እንዲሁም ደግሞ አበቦቼን ባፈነድቃቸው ህፃናቶች ቆርጠው ምድር ላይ በመጣል መጫዎቻ ያደርጉኛል፡፡ ስለሆነም ከዚህ ሁሉ የምጠበቅበት ምቹ ሁኔታ እስኪፈጠር መጠበቁ የተሻለ ሳይሆን አይቀርም” ሲል የመብቀል የሕይወት ተልዕኮውን ገታው፡፡

ይህን ሀሳባቸውን ከተነጋገሩ ከሰዓታት በኋላ በአካባቢው ምግቧን ፍለጋ  ምድርን ስትጭር የነበረች ዶሮ ለመብቀል ምቹ ሁኔታን ሲጠብቅ የነበረውን ዘር አገኘችና ተመገበችው፡፡ ሥራን ለመስራት የማይመጣን ምቹ ሁኔታን መተበቅ ስራ እንዳንሰራ ከማድረግ ውጪ የሚፈጥረው ፋይዳ የለውም፡፡ እንቅፋትም እስከመጨረሻው ስለማየውቅ በዓለማችን እስካሁን ተሰሩ ወሳይኝ የሚባሉ ስራዎች በሙሉ በችግር ውስጥ እንጅ በተደላደለ ሁኔታ እንደልሆነ አብዛኛው መረጃ ይናገራል፡፡ There is no ideal condition for everything we can do what we have to do even in adverse condition. 

/ምስጋናው ግሸን/

#ሼር
@ethiopia2123
348 viewsአበሜሌክ ዘጎጃም, 13:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 22:37:35 #ቀን_ገንቢ
ምዕራፍ ፩: ክፍል ፩


የራስ ዋጋ(አንብቤ ከወደድሁት የጋበዝኋችሁ)
------------

በአንድ ሰሚናር ውስጥ ሁለት መቶና በላይ ሰዎች በታደሙበት ታዋቂው ንግግር አድራጊ ተጋብዞ በቦታው ተገኝቷል፡፡ ተናጋሪው ለለቱ ማስተላለፍ የፈለገውን መልዕክት ለማጠናከር ያግዘው ዘንድ ንግግሩን የጀመረው የሃምሣ ብር ኖት በእጁ ይዞ በማሳየት “ከመካከላችሁ ይህን የሃምሣ ብር ኖት የሚፈልግ ማን ነው!?” ሲል ጠየቃቸው፡፡ ታዳሚውም በተከታታይ ሁሉም እጁን አንድ ባንድ አወጣ፡፡ ተናገሪው ቀጠለ “ከመካከላችሁ ለአንዳችሁ መስጠት እፈልጋለሁ ነገር ግን ከዛ በፊት” አለና የሃምሳ ብር ኖቱን በእጁ በማፋተግ እንዲጨማተር ካደረገ በኋላ “አሁንስ የሚፈልገው ይኖራል!?” ሲል በድጋሜ ጥያቄ አቀረበ፡፡
አሁንም የታዳሚዎች እጅ እፈልጋለሁ በሚል ስሜት ተዘረጋ፡፡ በጣም ጥሩ አለ ተናጋሪው እንደዚህ ባደርግስ ብሎ የሃምሣ ብር ኖቱን እግሩ ሥር ጥሎ በጫማው ምድሩ ጋር ካፋተገ በኋላ አሁን “እደምትመለከቱት በጣም ቆሽሿል:: ተጨማትሯልም:: አሁንስ ትፈልጉታላችሁ!? አሁንም የፈላጊዎች እጅ በአንድነት ተነሳ፡፡ “ወገኖች አሁን በጣም ወሳኝና መሰረታዊ ትምህርት እንደቀሰማችሁ አምናለሁ፡፡ ምንም እንኳን ብሩ ላይ ማናቸውንም ነገር ባደርግበት፣ ባቆሽሸውም፣ ባጨማትረውም፤ ብሩን የራሳችሁ የማድረግ ፍላጎታችሁ እንዳለ ነው፡፡ አልቀነሰም፡፡ ምክንያቱም የብሩ ኖቱ ቢጎሳቆልም ቢጎዳም እንደ ብርነቱ የሚሰጠውን ዋጋ ወይም ጠቀሜታ አልቀነሰበትምና፡፡ እስካሁንም ዋጋው ያው ሃመሳ ብር ነው፡፡” አላቸው፡፡

ብዙውን ጊዜ በሕይዎት ውጣውረድ በምናሳልፋቸው ውሳኔዎች ፣ በሚፈጠሩት ክስተቶች መውደቅ መነሳቱ፤ መደቆሱ ያለና የሚኖር ነው፡፡ በተፈጠሩት የህይዎት ፈታኝ ክስተቶች ዋጋ ያጣን ያህል ሊሰማን ይችላል፡፡ ነገር ግን ምንም ይሁን ምን፣ ያለፍንበት የሕይዎት ጎዳና ምንም ያህል አባጣ ጎርባጣም ቢሆን እኛ ማለት እኛ ነንና የእኛነታችንን፣ የራሳችንን ዋጋ አናጣምም ማጣትም የለብንም ፡፡


#ሼር

@ethiopia2123
382 viewsአ.ቡ.ጊ.ዳ.., 19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ