Get Mystery Box with random crypto!

EthioipaNews

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioipanews — EthioipaNews E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioipanews — EthioipaNews
የሰርጥ አድራሻ: @ethioipanews
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.38K
የሰርጥ መግለጫ

⚠️ Warning: Many users report that this account impersonates a famous person or organisation.

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 62

2022-09-05 19:20:20
ኢትዮጵያ ለህዳሴው ግድብ የሩሲያን የቴክኒክ ድጋፍ ልትጠይቅ ትችላለች- አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ!

ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድብ የውሃ መጠን ማወቅ ጋር በተያያዘ ሩሲያን የቴክኒክ ድጋፍ(የውሃ መጠን አቅርበው የሚያሳዩ የሳተላይት ምስሎች) ልትጠይቅ እንደምትችል አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ ተናገሩ፡፡

አምባሳደሩ ከሩሲያው “ስፑትኒክ” ኤጀንሲ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ “በሩሲያ በኩል ሁልጊዜ የቴክኒክ ድጋፍን ለማድረግ ፍላጎት አለ፤ ኢትዮጵያም በደስታ ትቀበለዋለች። አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በጥያቄው ላይ ከሞስኮ ጋር የምንነጋገርበት ይሆናል ..በእነሱ በኩል ሀሳቡ እንዳለ አውቃለሁ፤ ጥሩ ይመስለኛል” ብለዋል፡፡

አምባሳደር አለማየሁ ቀደም ሲል ከዚሁ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የህዳሴው ግድብ ግንባታ 88 በመቶ መጠናቀቁን እና ስራው በሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ ላይ እንደሚጠናቀቅ መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡
“ይህንን ግድብ የምትመራው ኢትዮጵያ ብቻ ናት” ሲሉም ነበር ያሳሰቡት፡፡

የአባይ ውሃ ብቅረቡ ለሶስተኛ ጊዜ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አናት ላይ መፍሰስ መጀመሩ የሚታወቅ ነው፡፡ግንባታው ሲጠናቀቅ በአፍሪካ ግዙፉ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ እንደሚሆን የሚጠበቀው የህዳሴ ግድብ ከፍታው 145 ሜትር ሲሆን፤ ርዝመቱ ደግሞ 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ነው። ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ፈሶበት ከአምስት ሺህ በላይ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል የተባለው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአካባቢው ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።

Via @Addis_Mereja
@EthioipaNews
9.6K viewsedited  16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 00:46:24
ሰበር ዜና!!

የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ሰራዊት አዲአርቃይን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር አውሏል!!


የጥምር ጦር ሃይላችን አስገራሚ ብቃቱን ድል በድል ላይ እየደራረበ ማሳየቱን ቀጥሏል።

ጠላት የተማመነባቸው የኮንክሪት ምሽጎችን በመደርመስና በጠላት ላይ ከባድ ዱላ በማሳረፍ መኒ ወንበርጌን እና ለአንድ አመት ያህል በጠላት እጅ የነበረችው አዲአርቃይን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር አውሏል። የጠላት ሃይል ለቁጥር በሚታክት መልኩ የረገፈ ሲሆን ህይወቱን ለማትረፍ ሽሽት የያዘውንም የጥምር ጦር ኃይሉ እግር በእግር እየተከተለ እየለበለበው ይገኛል።

ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊታችን ከፊቱ የሚቆመውን ሁላ እየጠረገ ወደ ሽሬ እንደስላሴ ጉዞውን ቀጥሏል።

በአካባቢው የመሸገው የህወሓት ሀይል ሰራዊታችን ጠንካራ ምት ተመትቶ እየተደመሰሰ ሲሆን የቀረው ጥቂት ወራሪ ትጥቅና ስንቁን ጥሎ ባገኘው መንገድ መፈርጠጡን ቀጥሏል።

Via @Addis_Mereja
@EthioipaNews
11.9K viewsedited  21:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 21:53:47 ከደሴ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የተላለፈ ተጨማሪ ውሳኔ!!

የደሴ ከተማ አስተዳደር ነሀሴ 22/2014 ዓ.ም በከተማው ልዩ ልዩ ክልከላዎችን በማስቀመጥ የተቀመጡ ህጎችን እያስተገበረ ይገኛል።

እነዚህ ህጎች እንደተጠበቁ ሆነው በተጨማሪ ከነሀሴ 30/2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆኑ ተጨማሪ ክልከላዎችን ያስቀመጥን መሆኑ ታውቆ ህዝቡ ተባባሪ እንድሆን እንጠይቃለን።

1ኛ- የመከላከያ አባል ሳይሆን የመከላከያን የደንብ ልብስ መልበስ ፣ የአማራ ልዩ ኃይል አባል ሳይሆን የልዩ ኃይሉን የደንብ ልብስ ለብሶ በከተማው ውስጥ መንቀሳቀስ ፈፅሞ የተከለከለ ነው። የመከላከያም ሆነ የአማራ ልዩ ሀይል አባል ሳይሆን የደንብ ልብሱን ለብሶ ሲንቀሳቀስ የተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል ።

2ኛ- ከደሴ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ መዋቅር ውጭ ተፈናቃይ በመሆን የመጥታችሁ በከተማው በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ ነው ፡፡

3ኛ- ሀሰተኛ ወሬ በመልቀቅ የጥምር ጦሩን ስም ማጠልሸት ፈፅሞ የተከለከለ ሲሆን ይህን ተላልፎ የተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል ።

ለዚህም የከተማው ማህበረሰብ አሉባልታዎችን በተለያዩ ተቋማት በማሰራጨት ህዝቡን ለማደናገጥ ወይም ጥላቻ ለማሳደር የሚሰሩ ኃይሎችን ለፀጥታ ሀይሉ ጥቆማ እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡

4ኛ- ፀጉረ ልውጥ የሆነ ሰው በምናገኝበት ሰአት ማህበረሰባችን በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ አካል የመጠቆምና የማቅረብ ኃላፊነት ይኖርበታል።

5ኛ- በከተማችን የሚገኝ ማንኛውም የመንግስት እና የግል ታጣቂ በመንግስት አደረጃጀት ውስጥ በመካተት በየደረጃው ያለ የፀጥታ አካላት በሚሰጠው ስምሪት አካባቢውን የመጠበቅ ኃላፊነትና ግዴታ አለበት።

6ኛ- ማንኛውም አካል ከመንግስት አደረጃጀት ውጭ ለጦርነቱ በሚል ገንዘብ መሰብሰብ ፈፅሞ የተከለከለ ሲሆን ከመንግስት ዕውቅና ውጭ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ አካል ሊኖር አይገባም ። ሆኖም መንግስት ወጣቱንም ፣ ባለሀብቱን ፣ መንግስት ሰራተኞችና አመራሮችን ወዘተ በማሳተፍ የራሱን የመንግስት አደረጃጀት ተጠቅሞ ለጥምር ጦሩ የሎጅስቲክ ድጋፍ በዓይነትም ሆነ በገንዘብ በህጋዊ ደረሰኝ ከህዝቡ እየሰበሰበ ጥምር ጦሩ ውስጥ እየተሳተፈ ለሚገኝ ማንኛውም ኃይል ይጠቀምበት ዘንድ ያስረክባል።

7ኛ- በማንኛውም ሰዓት ታርጋ ቁጥር የሌለው ተሽከርካሪ ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀስ ከተገኘ በቁጥጥር ስር ውሎ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድበታል ።

የደሴ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት
Via
@Addis_Mereja
@EthioipaNews
11.6K viewsedited  18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ