2022-09-23 15:18:07
መዉሊድ የኢስላም መሰረት
መውሊድ ባልነበር :- አሏህ(ሱ.ወ) ፈጣሪያችን መሆኑን አናውቅም ነበር
መውሊድ ባልነበር :-ቁርዓንን ከጌታችን አሏህ ባልወረደልን ባልቀራነው ባልተመራንበት
መውሊድ ባልነበር :-አምስት ወቅት ሶላት ከአርሹ ጌታ ተለግሶን ባልሰገድን ባልተረጋጋንበት
መውሊድ ባልነበር :-ረመዷን መፆም አይደለም ወሬውም ባልነበር
መውሊድ ባልነበር :-ሀጅና ዑመራ ለማድረግ ወደ በይቱሏህ ባልተጓዝን
መውሊድ ባልነበር :- ሁለቱም ኢዶች ከቶ ባላወቅናቸው ባልተደሰትንባቸው ነበር
በአጠቃላይ መውሊድ ባልነበር ዲነል ኢስላም አይኖርም ነበር ለዚህም ነው መውሊድ የኢስላም መሠረት ነው የምንለው!
فاعتبروا يا أولي الأبصار
አስተውሉም የአእምሮ ባለቤቶች ሆይ
አሏህ (ሱ.ወ) ከኩፍር ጨለማ ወደ ዲነል ኢስላም ብርሃን እንድንገባ የመሆኑ ምክኒያት ምርጡ የአሏህ ባሪያ የሆኑትን ነቢያችን ሙሐመድ ሶለ ሏሁ አለይሂ ወሰለም በመወለዳቸው በመገኘታቸው እና ወደ እኛ ቀጥታ መንገድ እንድንመራ ዘንድ ነቢይ አድርጎ ጀሊሉ በመላኩ እንጂ በሌላ በምንም ምክኒያት አይደለም እና ለዚህ ለዋለልን ታላቁ የመውሊድ ፀጋ በመደሰት ምስጋና ለአሏህ እናቀርብ ዘንድ አሏህ አዞናል!
قل بفضل الله وبرحمته فبذلك فليفرحوا هو خير مما يجمعون
«በአላህ ችሮታና በእዝነቱ (ይደሰቱ)፡፡ በዚህም ምክንያት ይደሰቱ፡፡ እርሱ ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ነው» በላቸው። (ዩኑስ 58)
እናንተ የአእምሮ ባልተቤቶች ሆይ! በነቢያችን ሙሐመድ ﷺ በመወለድ ሰበብ ያገኘነው ፈድል(ችሮታ) እና በሳቸውም ሰበብ የኢስላምን ዲን ከመጎናፀፍ በላይ የበለጠ ምን ችሮታ አሏህ ችሮአችኋል?!
እናንተ የአእምሮ ባልተቤቶች ሆይ! በኩፍር ጨለማ ከመዋጣችንና መሪ አጥተን ቀጥተኛውን መንገድ ፍለጋ ከመባዘናችን በፊት ነቢያችንን ﷺ በመውሊዱ ማስገኘቱ አሏህ ማስገኘቱ ለእኛ ጀሊሉ ታላቅ እዝነቱን ፍቅሩ ያሳየበት የገለጠበት መንገድ የበለጠ ሌላ ምን ነገር ይኖራል?!
ስለዚህ አሏህ በሰጠኋችሁ ችሮታና በእዝነቴ ተደሰቱ ብሎ ካለን ለእኛ በነቢዩ ﷺ መውሊድ ሰበብ ነውና ኢስላምን የተጎናፀፍነው ደስታችንን ከምንም ነገር በላይ በመውሊዱ እያበላን እየመደህን ሶለዋት በነቢያችን ﷺ እያወረድን እየተደሰትን አሏህን እየሸከርን ከቤተሰቦቻችን ከወንድሞቻችን ከመሻኢሆቻችን ጋር በማሳለፍ አሏህ ፈጣሪያችንን የምናመሰግንበት መንገድ እንጂ ጥራዝነጠቆች እንደሚሉት የአሏህ ባሪያ የሆኑትን ሀቢቡሏህ ሰይደና ሙሐመድን ﷺ አምልኮ የምናደርግበት በኢስላም ዲን ላይ ተቀፅላ ፈጠራ የሆነ ቢድዓ የምንፈፅምበት መንገድ አይደለም እና ብዥ ያለበት ብዥታውን አጥርቶ የኢስላም ወንድማማችነት በነቢያችን ﷺ ዉዴታ ስም በመውሊዱ በመሰባሰብ አንድነታችንን እናጠናክር
ኻሊድ ሙርሰላ
1.3K views12:18