Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮ መረጃ University

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_university — ኢትዮ መረጃ University
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_university — ኢትዮ መረጃ University
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja_university
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.02K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-20 13:06:07
#JimmaUniversity

ጅማ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የነባር እና አዲስ ገቢ #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 18 እና 19/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

በመሆኑም በተጠቀሱት ቀናት በአካል በመገኘት ምዝገባ እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
459 viewsedited  10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 16:46:59
327 viewsedited  13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:01:02
292 views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:01:02
291 views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 14:54:34
#DebreTaborUniversity

ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምሀርት መስኮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 238 ተማሪዎች ቅዳሜ ሐምሌ 09/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።

ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 163ቱ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ብርሀኑ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።
431 viewsedited  11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 18:20:57
#SalaleUniversity

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ነባር የክረምት ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜን አራዝሟል።

ዩኒቨርሲቲው ምዝገባው ሐምሌ 07 እና 08/2014 ዓ.ም ይከናወናል በማለት ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ ከትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠ አቅጣጫ የምዝገባ ጊዜው ወደ ሐምሌ 20 እና 21/2014 ዓ.ም መራዘሙን ገልጿል።
296 views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 10:23:10
በአማራ ክልል የ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ መሰጠት ጀምሯል።

ፈተናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2014 ዓ.ም ለሦሥት ቀናት ይሰጣል ተብሏል።

በክልሉ ከ359 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

ፈተናው በክልሉ በሚገኙ 5 ሺህ 395 ትምህርት ቤቶች የሚሰጥ ሲሆን ከ10 ሺህ በላይ መምህራን ፈተናውን በመስጠት ይሳተፋሉ።

የ8ኛ ክፍል ፈተና በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ፣ በአፋር እና በሐረሪ ክልሎች ትላንት መሰጠት ጀምሯል።

@ethio_mereja_university
@ethio_mereja_university
654 viewsedited  07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 18:09:17
#Dilla

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 320 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ዩኒቨርሲቲው በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በሦሥተኛ ዲግሪ 3 ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን 126 ተማሪዎች ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ አስመርቋል።

የሲቪል ምህንድና ትምህርት ክፍል ተመራቂ የሆነችው ሄርሜላ በኃይሉ 3.92 ውጤት በማምጣት እንዲሁም የኮምፒውተር ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተመራቂ ለሊሳ ዮሐንስ 3.92 ነጥብ በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል።

Congratulations !
969 viewsedited  15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 16:22:36
ራጂ አሸናፊ

በ60 ኮርሶች A+ ያመጣው ባለምጡቅ አእምሮ ባለቤቱ ራጂ አሸናፊ !

ተማሪ ራጂ አሸናፊ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) በ60 ኮርሶች A+ በማምጣት በከፍተኛ ነጥብ ዛሬ ተመርቋል።

ራጂ አሸናፊ የተወለደው በኦሮሚያ ክልል፣ ቄለም ወለጋ ጊዳሚ ሲሆን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናውን በከፍተኛ ውጤት ነው ያጠናቀቀው።

የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናንም (ከኦሮሚያ ቦርዲንግ ትምህርት ቤት) ከመላው ኢትዮጵያ ሁለተኛውን ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቦ ነው ያጠናቀቀው።

በኃላም ወደ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ገብቶበ Applied Physics Department ትምህርቱን የተከታተለ ሲሆን በወሰዳቸው 60 ኮርሶች A+ በማምጣት እጅግ አስደናቂ ውጤት ማስመዝገብ ችሏል።

ራጂ አሸናፊ ባለው ከፍተኛ የሆነ ብቃት በአሜሪካ ሀገር Massachusetts Institute of Technology (MIT) ለ5 ዓመት የPHD ትምህርቱን ለመከታተል እድል አግኝቷል።

ህልሙ በፅንሰ ሀሳባዊ የPhysics መስክ ትምህርቱን ጨርሶ ለሌሎች የሀገሩ ልጆች የተሻለ እድል መፍጠር ሲሆን ከPHD ጥናቱ በኃላ ወደ ASTU በመመለስ የCenter for High Energy Physics የPHD ፕሮግራም መክፈት ነው።

በሌላ በላኩል የሀራምቤ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ በከፍተኛ ማዕረግ ለተመረቀው ራጂ አሸናፊ 50 ሺህ ብር ሸልሟል ፤ የዛሬ አራት አመት የ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት ሲያመጣ ዩኒቨርሲቲው ሽልማት አበርክቶለት ነበር።
891 viewsedited  13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 10:05:02
እንኳን ደስ ያላቹ

የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪቻቸውን
በዛሬው እለት እያስመረቁ ነው!!

የወልቂጤ፣ የሀዋሳ፣ የዋቻሞ ፣ ጂማ፣ ጎንደር እና አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መርሀ ግብሮች ያስተማሯቸውን ተማሪች በዛሬው እለት እያስመረቁ ነው።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲም በዛሬው እለት ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎቹን ለ23ኛ ጊዜ እያስመረቀ ሲሆን አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ለ35ኛ ጊዜ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ2 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች እያስመረቀ ይገኛል።

ጅማ ዩኒቨርስቲም በተለያዩ የምህርት መስኮች ያስተማራችውን 2 ሺህ 509 ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል። በተያያዘ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት 334 የሕክምና ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለ67ኛ ጊዜ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺሕ 866 ተማሪዎች በዛሬው እለት እያስመረቀ ይገኛል።
847 viewsedited  07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ