Get Mystery Box with random crypto!

Esat tv

የቴሌግራም ቻናል አርማ esat_television_official — Esat tv E
የቴሌግራም ቻናል አርማ esat_television_official — Esat tv
የሰርጥ አድራሻ: @esat_television_official
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 59
የሰርጥ መግለጫ

ኢሳት የኢትዮጵያ #አይን እና #ጆሮ
መሳይ መኮንን ✍️

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-05-11 14:38:35
595 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ዛሬ ንጋት ላይ ጅቡቲ ወደብ ደረሰ

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለ2014/15 የሰብል ዘመን ከሞሮኮው የአፈር ማዳበሪያ አምራች ኩባንያ ከገዛው 7 ሚሊዮን 875 ሺህ 523.4 ኩንታል NPS ፋሚሊ (የናይትሮጅን፣ ፎስፌት እና ሰልፈር ውህድ) ውስጥ እስከ ግንቦት ዛሬ ድረስ 7 ሚሊዮን 299 ሺህ 150.5 ኩንታል (92.7 በመቶ) ጅቡቲ ወደብ ደርሶ ወደ ሀገር ውስጥ እየተጓጓዘ መሆኑን አስታዉቋል።

ቀሪው 576 ሺህ 372.9 ኩንታል NPS እና NPSB ማዳበሪያ ግንቦት ቀን 2014 ዓ.ም. ጅቡቲ ወደብ እንደሚደርስ ይጠበቃል። በሌላ በኩል በቅርቡ በሁለት ዙር ጅቡቲ ወደብ የደረሰው 1 ሚሊዮን ኩንታል ዩሪያ ለአርሶ አደሩ እየቀረበ ይገኛል። በቅርብ ቀናትም ተጨማሪ ዩሪያ ማዳበሪያ ወደብ እንደሚደርስ ኮርፖሬሽኑ አስታዉቋል።

በአጠቃላይ ከጥር እስከ ግንቦት ዛሬ ድረስ 8 ሚሊዮን 299 ሺህ 150 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ ደርሷል። ከዚህ መጠን ውስጥ እስከ አሁን 6 ሚሊዮን 292 ሺህ 229 ኩንታል (76 በመቶ) የአፈር ማዳበሪያ በክልል ዩኒየኖች አማካኝነት ለአርሶ አደሩ እንደሚገኝ ከኮርፖሬሽኑ ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official
9.7K viewsedited  11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-11 13:23:24 ያልገባኝ ነገር…?

"…ትርፍ አምራች የሚባሉ ሃገራት፣ በኢንዱስትሪ የበለፀጉ የሚባሉቱ ሁሉ፣ ነዳጅና ስንዴ አቅራቢዎች ጭምር በየሪፖርታቸው ላይ ከ29 ዓመት በኋላ፣ ከ60 ዓመት በኋላ፣ ከ15 ዓመት በኋላ ወዘተ ታይቶ የማይታወቅ የኢኮኖሚ ድቀት ደረሰብን እያሉ በግልፅ ሲያለቃቅሱ እያየን ነው። በአንዳንድ የአውሮጳ ሃገራት እንዲያውም በነዳጅ እና በሸቀጣ ሸቀጥ አቅርቦት ላይ ጭማሪ በመታየቱ የተቃውሞ ሰልፎች ሁሉ መታየት ጀምረዋል።

"…ይህንና ይህን የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ ዜናዎችን ሰምቼ አበቃና ወደ ምስኪን ሃገሬ ፊቴንም ጆሮዬንም አቅንቼ ስመለከት የማየውና የምሰማው ሁሉ ግራም ቀኝም ያጋባኛል። ታይቶ የማይታወቅ እድገት ይልልሃል አፈ ቅቤው የዥጋቤል ሰው ዐቢይ አሕመድ አሊ። በደቡብ ኦሮሚያ በቦረና ከብቶች አልቀው። የሰው ልጅ በበሬ ምትክ እያረሰ። ሶማሌ ክልልም እንደዚያው። በወለጋ ሚልዮኖች ተፈናቅለው። በቤኒሻንጉል በደቡብም እንደዚያው። ምሥራቅና ሰሜን ዐማራ ሙሉ ለሙሉ ወድሞ። አፋርም እንደዚያው። ትግራይ በሚልየን የሚቆጠር ህዝብ በምን ሁኔታ ውስጥ እንዳለ ከእግዚአብሔር በቀር ህወሓትም፣ ብልፅግናም በማያውቁበት ሁኔታ እድገታችን ተብሎ የሚወራውን ነገር ስሰማ ቁጥር ላይ በፊትም ደደብ ነበርኩ አሁንማ የባሰ ደደብ ነው ያደረገኝ።

"…ጦርነት በባህሪው ከባድ ወጪ የሚያስወጣ ነው። ሃገሪቷ እስከአሁን በማያባራ ጦርነት ውስጥ ናት። ከሸኔ ጋር እየተዛጠዙ ነው። መንግሥትም እየተዋጋሁ ነው እያለ ነው። ህወሓት ለሁለተኛ ዙር ውጊያ እያሟሟቀች ነው። ይሄም ወጪ አለው። አምራች ፋብሪካዎች በኃይል አቅርቦትም፣ በውጭ ምንዛሪ እጥረትም ምክንያት እየተዘጉ ነው። የምግብ፣ የሸቀጣሸቀጥ፣ የትራንስፖርት፣ የቤት ኪራይ ዋጋ በእጥፍ ጨምሯል። ኑሮ እጅግ በጣም መወደዱ እየተነገረ ነው። አይመምህ እንጂ ከታመምክ ህክምናው የማይቀመስ፣ የማይቻልም መሆኑ ነው እየተነገረ ያለው። ከተሳሳትኩ እታረማለሁ።

"…እዚህ ላይ ነው ጥያቄዬን የማነሣው። እንዲህ ምስቅልቅሉ በወጣ ዓለም ላይ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ብቻውን በምን ተአምር ነው ተስፈንጥሮ አድጎ መንግሥት የሃገሪቱ እድገት በአስደናቂ ሁኔታ እየተመነደገ ነው የሚል ሪፖርት እንዲያወጣ ያስደረገው። ቆይ ሃገሪቱ የምትመራው በእነ ኢዩ ጩፋ እና በእነ ዳንሳ መንፈስ ነው እንዴ? እንዲያ ካልሆነ በቀር እንዴት ባለ ሁናቴ ውስጥ ቢኮን ነው እነ ጣሊያን፣ እነ ግሪክ ወገቤን በሚሉበት በዚህ ዘመን ከጣት የማይቆጠሩት ፋብሪካዎቿ የተዘጉባት ኢትዮጵያችን ተአምራዊ እድገት ላይ ነኝ እንድትል ያደረጋት? የገባችሁ አስረዱኝ።

"…ገበሬ አፈናቅላ፣ ምርት እና ክምር በእሳት አቃጥላ፣ የቀንድ ከብቶቿም በድርቅ ተፈጅተውባት፣ የለስላሳ ፋብሪካ እንኳ የውጭ ምንዛሪ አጥቶ ተዘግቶባት፣ ነዳጅ ጣራ…

https://t.me/esat_television_official
9.5K views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-11 13:23:05
8.5K views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ