Get Mystery Box with random crypto!

Campus Edu life

የቴሌግራም ቻናል አርማ campusstudent — Campus Edu life C
የቴሌግራም ቻናል አርማ campusstudent — Campus Edu life
የሰርጥ አድራሻ: @campusstudent
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.02K
የሰርጥ መግለጫ

👇👇👇👇👇👇
♨️♦️@CampusStudent ♨️
♨️♦️@CampusStudent ♨️ #SHARE

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-07 13:58:56 መረጃ

የ 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ መስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የሚሰጥ ሲሆን
ተማሪዎች ከክልላቸዉ ዉጭ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ይፈተናሉ።
ፈታኞች ከሌላ ክልል (ብሄር) ይሆናሉ።
ተማሪዎች ገና ከቤታቸዉ ሲወጡ ስልክ ያስቀምጣሉ። ዩኒቨርስቲ ከገቡ በኋላ ፈተናዉ እስኪጠናቀቅ ከስልክ ጋር ንክኪ ስለማይኖራቸዉ ፈተናዉ ቢሰረቅ እንኳ የሚያገኙበት ዕድል አይኖርም።
ይህን መሰረት አድርጎ ተማሪዎችን ማዘጋጀትና በስነ ልቦና መገንባት ያስፈልጋል።
======================

The 12th grade national exam will be given by government universities from September 30/2015(e.c).
Students are tested in universities outside their region.
Examiners will be from another region (ethnicity).
Students leave their phones when they leave their homes. After entering the university, they will not have contact with the phone until the exam is over, so even if the exam is stolen, there is no chance of finding it.
Based on this, it is necessary to prepare students and build them psychologically.
======================
for comment, suggestion or
For a question
@EtTemari_bot

ለአስተያየት ፣ ለጥቆማ አልያም
ለጥያቄ
@EtTemari_bot


╔═════════════╗
@HigherEduEt 
@HigherEduEt
╚═════════════╝ #SHARE
293 views10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 10:50:09
በአሜሪካ ኦሪጎን እየተካሄደ በሚገኘው አስራ ስምንተኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ ሜዳልያ ደረጃ ሰንጠረዡ ከአፍሪካ አንደኛ ከአለም ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

እስካሁን ኢትዮጲያ በውድድሩ አስር ሜዳሊያዎችን አግኝታለች። አራት ወርቅ፣ አራት ብር እና ሁለት የነሀስ ሜዳልያዎች እስካሁን በተደረጉ ውድድሮች ተገኝቷል።
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ እየመራች ትገኛለች ። ኬንያ በስምንት ሜዳልያዎች ከአፍሪካ የሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሀገር ስትሆን ዩጋንዳ በሁለት ሜዳልያ ሶስተኛ ሆናለች።

ዘጠኝ የወርቅ፣ ሰባት የብር እና አስር የነሀስ ሜዳልያዎችን ያገኘችው የውድድሩ አዘጋጇ ሀገር ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካን የአለም ሜዳልያ ሰንጠረዡን በበላይነት እየመራች ትገኛለች።

የነገውን የወንዶች የ5000 ሜትር እና የሴቶች 800 ሜትር የፍፃሜ ውድድሮችን ሳይጨምር ኢትዮጵያ እስካሁን ከተሳተፈችባቸው የአለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና መድረኮች ኦሪገን ብዙ ወርቅ (4 *) የተገኘበት ውድድር ሆኗል::
465 views07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 10:50:09
" ኢትዪጵያ ሁሌም በልጇቿ ትሳቅ " አትሌት ደራርቱ ቱሉ (ኮሎኔል)
356 views07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 08:43:46
ሰበር ዜና

የ ዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ተደርግዋል

የ 2013 12ኛ ክፍል ማለፊያ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ተደርግዋል

ዩኒቨርሲቲ ምደባው ለማየት
Telegram bot
@moestudentbot

Google link
https://result.ethernet.edu.et

ለአስተያየት ፣ ለጥቆማ አልያም
ለጥያቄ
@EtTemari_bot


╔═════════════╗
@HigherEduEt 
@HigherEduEt
╚═════════════╝ #SHARE
756 views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 07:35:46
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ አደረሰን!

@HigherEduEt
616 views04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 08:49:56 መጀመሪያ ግቢ ስንደርስ ማን ጋር ነው ምንገናኘው ?



ግቢ በር ላይ ከመኪና ኦር ከታክሲ እንደወረዳቹህ በመጀመሪያ የምታገኙት እንኳን ደህና መጣቹህ የሚል ፈገግ ያለ ፊት ነው ። ( like አስጌ ዴንዴሾ )

እዚህ ጋር መርሳት የሌለባቹህን ላገጠጠላቹህ በሙሉ ሻንጣ እንዳትሰጡ በተለይ መናሀሪያ የምትወርዱ ከሆነ በጣም ተጠንቀቁ አንገታቸው ላይ or ደረታቸው ላይ ባጅ ያጠለቁ እሱንም የዩንቨርሲቲው ማህተም ያለበት መሆኑን ቼክ አርጉ አንዳንድ ከተሞች ላይ በጣም የተደራጁና ረቀቅ ያሉ ሌቦች ስለሚኖሩ be take care.

የትኛውም ግቢ አዲስ ተማሪዎች በሚገቡበት ቀን በር ላይ የተለየ ዝግጅት በማድረግ ጥብቅ ፍተሻ ይደረጋል ።

ማንኛውም ተማሪ የያዘውን ሻንጣ ከፍቶ ሳያስፈትሽ እግሩ ወደ ግቢ አይገባም ።
ከፍተሻው በተጨማሪ ግን ሁሉም ተማሪ የዶርምና ብሎክ ቁጥር ማወቅ አለበት እሱም ከግቢ ውጭ ወይም ግቢ ውስጥ ይለጠፋል አንዳንዶች ግቢዎች ደግሞ ዌብሳይት ላይ አስቀድመው ይለቃሉ like AAU እንዳደረገዉ።
የብሎክና ዶርም ቁጥራችሁን ካወቃቹህ ጓዛችሁንም ካስፈተሻቹህ በኋላ ቀጥታ የምትሄዱት ወደ ዶርም ነው ።(ነባር ተማሪዎች ብሎክ ድረስ ይሸኟቹሃል)
ብሎካቹህ ጋር ስትደርሱ ground ላይ የብሎክ ሃላፊው(ፕሮክተር) ቢሮ በመስኮት በኩል ዶርም ቁጥራችሁን፣ ስም፣ phone number እና ፎቶ በመስጠት ፈርማቹህ የዶርም ቁልፍ ትቀበላላቹህ ።( ቁልፍ የሚሰጠው ቀድሞ ለመጣ አንድ የዶርም አባል ብቻ ነው ከተቀደማቹህ ቁልፍ የተሰጠውን ዶርሜት ስልክ ቁጥር ተቀብላቹህ መደወል ነው)


ዶርም ስትገቡ የመጀመሪያ ሰው ከሆናቹህ ያሻችሁን አልጋና ሎከር መርጣቹህ የመያዝ ሙሉ መብት አላቹህ ። ደስ ካላችሁም ትራስ ምናምን መቀያየር ችቡድ ሰባራ ከሆነ እሱንም መቀየር... ብቻ በዶርሙ ላይ የተመቻችሁን የግል ንብረት ማሽከርከር ትችላላቹህ coz ማንም በቦታው ላይ የለምና ።
ከተቀደማቹህ ግን ከቀደማቹህ ሰው ጋር ሳትጋፉ ያገኛችሁትን ....
አደራ ግን እንዳትጨቃጨቁ

ሌላው ዶርም ስትገቡ አንሶላና ትራስ ጨርቅ ምናምን ሳትጠቀሙ ጋደም ማለት ቢያምራቹህ እንኳ እንዳተኙ coz ፎከታም ትሆኑብኛላቹህ(biology ላይ የተማራችሁትን አትርሱ fungus+virus)

የዶርም ጣጣችሁን ከጨረሳችሁ ቀጥታ የምትሄዱት ወደ register ይሆናል (በስራ ሰዓት ብቻ)
አመሻሽ ላይ ግቢ ከደረሳቹህ ለምዝገባ ስለማትደርሱ የዶርማችሁን ጣጣ ለመጨረስ ሞክሩ ለምዝገባው አታስቡ በነገታው መመዝገብ ትችላላቹህ ።

ምዝገባ ቦታ ላይ ያለው process

መጀመሪያ ክላሰር ወረቀት ትገዙና የሚሰጣችሁን ፎርም ትሞላላቹህ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ኦሪጂናሉንና ኮፒውን ትጠየቁና ኦሪጂናሉ ይመለስላቹሃል ። ፎቶም ትጠየቃላቹህ
በሌላ መስኮት ደግሞ ID ምናምን ታወጣላቹ ከዛ ትንሽ ትንቀዋለሉና ትጨርሳላቹህ

Above ሁለት ሺህ ተማሪ ምናምን በአንድ መስኮት ስለሚስተናገድ በጣም መጨናነቅ ይኖራል ቻል ማድረግ ነው ።

ምዝገባ ከጨረሳቹህ መታወቂያ ከተቀበላቹ ዶርም ሂዳቹ ደስ ካላቹህ ተገልብጣቹህ ለጥ ማለት ትችላላቹህ ።



አንዳንድ ግቢዎች ላይ መጨናነቁ በከፊል ሊቀንስ ይችላል ።

አንዳንዶች ጋር ደግሞ ባስ ይላል



ተማሪዎችም በተመሳሳይ መልኩ ይሆናል register ላይ ግን እንደፍሬሽ አይንከራተቱም ID ማሳደስ ብቻ ሌላው ነገር በሙሉ ተመሳሳይ ነው ።

ለአስተያየት ፣ ለጥቆማ አልያም
ለጥያቄ
@EtTemari_bot


╔═════════════╗
@HigherEduEt 
@HigherEduEt
╚═════════════╝ #SHARE
1.1K views05:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-14 18:31:23
የ2013 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የማለፊያ ነጥብ

ለአስተያየት ፣ ለጥቆማ አልያም
ለጥያቄ
@EtTemari_bot


╔═════════════╗
@HigherEduEt 
@HigherEduEt
╚═════════════╝ #SHARE
1.1K views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-14 18:31:23 የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል

በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።

በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል።

በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል።

በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት

በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።

በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል።

በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል።

ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር

ለአስተያየት ፣ ለጥቆማ አልያም
ለጥያቄ
@EtTemari_bot


╔═════════════╗
@HigherEduEt 
@HigherEduEt
╚═════════════╝ #SHARE
844 views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-14 18:31:23
የከፍተኛ ትምህርት መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ይፋ አደረገ።

በዚህ መሰረት አንደኛ ዙር ተፈታኞችን በተመለከተ:-

የተፈጥሮ ሳይንስ በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለወንድ 363 እንዲሁም ለሴት 351

በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለወንድ እና ለሴት በተመሳሳይ 300
ለታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢዎች ለመደበኛ ተፈታኞች ወንድ 351 እና ለሴት 339

ለግል ለወንድና ለሴት በተመሳሳይ 300

መስማት ለተሳናቸው ለሁለቱም ጾታዎች 300

በግል ለሚማሩ 300

ተፈጥሮ ሳይንስ የግል (ድጋሚ ተፈታኞች) ሁለቱም ጾታ 380
በግል ከፍተኛ ትምህርት መከታታል ለሚፈልጉ 300

ማህበራዊ ሳይንስ ለመደበኛ ተፈታኞች ወንድ 264 እና ለሴት 254 እንዲሁም በግል ከፍተኛ ትምህርትን ለመከታተል 250

አይነ ስውራን መደበኛ ተፈታኞች ለሁለቱም ጾታ 200 እንዲሁም በግል ከፍተኛ ትምህርትን ለመከታተል 200

ለታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ለወንድ 254 እና ለሴት 250 እንዲሁም በግል ከፍተኛ ትምህርት ለመከታተል ለሚፈልጉ 250

መስማት ለተሳናቸው ለሁለቱም ጾታ 250 እንዲሁም በግል ከፍተኛ ትምህርትን ለሚከታተሉ ለሚፈልጉ 250

ማህበራዊ ሳይንስ የግል (ድጋሚ ተፈታኞች) ሁለቱም ጾታ 280 እንዲሁም በግል ከፍተኛ ትምህርትን ለሚከታተሉ 250 መቁረጫ ነጥብ ሆኗል።

ለአስተያየት ፣ ለጥቆማ አልያም
ለጥያቄ
@EtTemari_bot


╔═════════════╗
@HigherEduEt 
@HigherEduEt
╚═════════════╝ #SHARE
760 views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-04 09:55:53
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ዐረፉ
*********************

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ማረፋቸውን የቤተክርስትያኗ መገናኛ ብዙኃን ጠቅሶ የዘገበው ኢዜአ ነው።

ቅዱስነታቸው ሰሞኑን ባደረባቸው ህመም የህክምና እርዳታ ሲደረግላቸው መቆየቱ ይታወሳል።

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ በ1980 ዓ.ም ነሐሴ 29 ቀን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ፓትርያርክ ተብለው የተሾሙ ሲሆን ላለፉት 34 አመታት በፓትርያርክነት አገልግለዋል።

ብጹዕ ወቅ አቡነ መርቆሬዎስ የቤተክርስቲያኗ ትምህርት የሆኑትን አቋቋም፣ ድጓና ዝማሬ መዋስዕት በላቀ ሁኔታ የተማሩ መሆናቸውን ከሕይወት ታሪካቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
865 views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ