Get Mystery Box with random crypto!

ማዕተብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ bale_maeteb — ማዕተብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ bale_maeteb — ማዕተብ
የሰርጥ አድራሻ: @bale_maeteb
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.19K
የሰርጥ መግለጫ

እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ። ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው። |ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ 8፤5-6 |
ለ 10 ሰው ሼር እናድርግ....እኛን ከጠቀመ እነርሱም ይጠቀሙ ።

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-04 20:21:57
432 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 17:07:22 + ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ አለ +

“ከልቦቻችን በማይነቀሉ የፍቅሩ ችንካሮች ተቸነከርን:: ያዝነው አንለቀውም እርሱም አቀፈን አልተወንም:: ወደ እርሱ በሃይማኖት አቀረበን:: ከእርሱም ወደ ቀኝ ወደ ግራ አንሸሽም:: እንደ ቀለበት በልባችን እንደ ማኅተም በክንዳችን አኖርነው:: እንደ ዕንቁ በልባችን ሳጥን አስቀመጥነው:: እንደ ወርቅ በሕሊናችን መዝገብ አኖርነው::
እንደ ግምጃ ለበስነው:: እንደ ሐር ግምጃ ተጎናጸፍነው:: እንደ ወታደር ሰይፍ ታጠቅነው:: ለጦር ዕቃ እንደተዘጋጀ የድል ጋሻ ተደገፍነው:: ተከዜና ግዮን በኢሎል ወር እንደሚሞሉ ፍቅሩ በልባችን መልቶአል:: እንደ መከር ጊዜ የዮርዳኖስ ወንዝ እንደ ክረምት ጊዜም የጤግሮስ ወንዝ ስንዴ ሲያሹት እንደሚሆን እንደ ኤፍራጥስ ወንዝ ልባችንን በወንጌል ፈሳሽነት አረሰረሰው:: መርከባችንንም በሃይማኖት ወንዝ አስዋኘው"
መጽሐፈ ምሥጢር 24:20

"ከእኛ ወገን ክርስቲያን እየተባሉ በገዛ መንገዳቸው የሚኖሩ ብዙዎች ናቸው ... የእንስሳ ሥጋ ከመብላት የሚከለከሉ የሰውን ሥጋ ለመብላት ግን የሚተጉ እነዚህ ናቸው"

"ስምዖን ጴጥሮስ ከሐዋርያት ሁሉ አብልጦ ክርስቶስን ወደደው:: ክርስቶስ ግን ከሐዋርያት ሁሉ አልቆ ወንጌላዊው ዮሐንስን ይወድደው ነበር::
ስለወደደው ግን አለቃ መሆንን ለዮሐንስ አልሠጠም:: እርሱ ከወደደው በላይ እርሱን የሚወደውን አለቃ አደረገው እንጂ"

"ክርስቶስን መውደድ ከወንድሞቹ ይልቅ በጴጥሮስ ላይ በዛ:: ከወንድሞቹ ይልቅ ወደ ጌታ ኢየሱስ ለመድረስ ቸኩሏልና ከመርከቢቱ ዘልሎ ወደ ባሕር ተወረወረ እንጂ በመርከብ ለመጎተት አልቆየም::
ወደ ወደደው ለመድረስ ቀደማቸው:: ከመርከቢቱ ላይ ያዘለለችው ወደ ጥልቁም ባሕር የወረወረችው ፍቅር እርስዋ የክህደቱን መጽሐፍ ደመሰሰችለት::
ራሱን ወደ ጥልቁ የጥብርያዶስ ባሕር በወረወረ ጊዜ የዕዳው መጽሐፍ ሰጠመ:: እርሱ ግን በብዙ ጭንቅ በብዙም ፍለጋ በዋናተኞችም በብልጠታቸው ጥበብ እንደሚገኝ እንደሚያበራ ዕንቁ ሆኖ ከባሕር ውስጥ ወጣ"

ከመጽሐፈ ምሥጢር ውብ ገጾች

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሰኔ 27 2014 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
471 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 23:06:17 #ዕርገት
† መኳንንት ደጆቻችሁን ክፈቱ †

ጌታ ሆይ ዛሬ መላእክት የሰማይ ደጆቻቸውን ከፍተው በምስጋና በክብር ይቀበሉሃል ፤ ደመናን የምትሰውራት አንተ ፣ ደመና ሰውራ ተቀበለችው ተባለልህ ፤ ከሃዋርያት አይን መሰውርህን ለመናገር እንጂ ሰማይ ዙፋን የሆነልህ አንተን ደመና በምን አቅሟ መደበቅ ትችል ይሆን።

ጌታ ሆይ ወደተቀደሰው ዙፏንህ ዛሬ ዐረግህ ፤ በፈቃዴ ወዳረከስኩት ወደ እኔ ልብ’ስ መቼ ነው የምታርገው ? እኔ እንደመላእክቱ የምከፍተው ደገኛ በር የለኝም ፤ የልቤ በር ተቆልፎ ከቆየ ብዙ ዘመን አልፎታል ፣ መክፈቻ ቁልፉም ጠፍቶብኛል ፣ ላንተ የሚሆን ምስጋና የሚያዘጋጅ ንጹህ ህሊናም አልተረፈኝም ፣
" ለእኔ ምን አይነት ቤት ትሰሩልኛላችሁ ብለህ ነበር " አዎ ጌታ ሆይ የኔ ቤት የሚከረፋ በኃጢአት የቆሸሸ ቤት ነው ።

እንግዲህ ጌታ ሆይ ላንተ የሚሆን ምንም የቀረልኝ ነገር የለም ፤ ግን በጥበበኛ እጅህ ሠርተኸኛልና አድነኝ ፣ ወደ ልቤ ቤት ለመግባት አንተ ቁልፍ አያስፈልግህም ፣ በተዘጋ በር መግባት ታውቅበታለህ እና ና ግባ ፣ ያም ካልሆነ የመቶ አለቃውን ጸሎት ተውሼ እማጸንሃለሁ "ቃል ብቻ ተናገር ልቤ ይፈወሳል"



[_ዲያቆን ብንያም አለባቸው_]
700 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 17:47:30
594 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 12:10:42 የልዳው ጊዮርጊስ ሆይ፤ ለአንተ ሰላምታ ይገባል። ፈረሰኛው ጊዮርጊስ ሆይ፤ ሰላምታ ይገባሃል። - የተወደደው የልጅዋ የኢየሱስ ክርስቶስና የድንግል ማርያም ዕውነተኛ ምስክር ሆይ፤ ሰላምታ ይገባሃል። የጥበብ መገኛዋ አዳራሽ ሆይ፤ ሰላምታ ላንተ ይገባሃል።

ጊዮርጊስ ሆይ፤ ለውሳጣዊ ገንዘቦችህና ሃሳቦችህም ሁሉ ከቶ ችሎታ ሣይኖረኝ ደፍሬ ሰላም እላለሁ። ተአምር ሠሪው ሰማዕት ሆይ፤ አዲሱን የወይን ድርሰት በማከታተል አጠጣኝ የኖረ የወይን ጠጅ በኔ ዘንድ አለና እኔም እኮ አዲሱን የምስጋና ውይን ጠጅ አቀርብሃለሁ።

[_መልክዐ ጊዮርጊስ_]
590 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 20:48:41
608 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 16:30:28 https://www.facebook.com/106519081868281/posts/162003512986504/?flite=scwspnss
594 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 10:41:09 "ዑራኤል ሆይ ከፈጣሪህ ይቅርታን አስገኝተህ የኃጥአንን ነፍስ የምትጐበኝ ነህና በዚያች የቁርጥ ፍርድ ቀን የሲኦልን ደጃፍ እንዳናይ ስለእመቤታችን ድንግል ማርያምና ስለልጅዋ ኢየሱስ ክርስቶስ በቃል ኪዳንህ እንማፀናለን"

[_መልክአ ዑራኤል _]
565 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 08:48:39
ማንኛውም ሰው ለሚሰራው መንፈሳዊ አገልግሎት ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግን ምክንያቱም "ያ ሰው" ደካማነት የሚዋጋው ስጋን የለበሰ አንተ ልትተጋለት/ልትፀልይለት የሚገባው ኃጢአተኛና የእግዚአብሔርን ቸርነት ተስፋ የሚያደርግ ነው ማንም ሰው ቤተክርስቲያንን ለራሱ ክብር ብሎ አያገለግልም ትልቁ ህልም 'ከእግዚአብሔር ተለይቶ አለመኖር' ነው።


" መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።" // ማቴ 5:16 //

ዲያቆን አቤሴሎም ድንቅአለም
ሰኔ-2014 ዓ.ም HU
618 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , edited  05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 08:23:18
545 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ