Get Mystery Box with random crypto!

ማዕተብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ bale_maeteb — ማዕተብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ bale_maeteb — ማዕተብ
የሰርጥ አድራሻ: @bale_maeteb
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.19K
የሰርጥ መግለጫ

እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ። ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው። |ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ 8፤5-6 |
ለ 10 ሰው ሼር እናድርግ....እኛን ከጠቀመ እነርሱም ይጠቀሙ ።

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-29 19:06:01 The peace of Christ is more precious than all the riches, all the delights and joys of the earth. It consists in the undoubted knowledge of the Living God, our Father.

It is enough for us to have a little food, to be under the roof of the house, to have a body covered from cold and shame (1 Timothy 6:8). If only the mind – our spirit – would be free to plunge into contemplation of the Divine Being revealed to us by Christ.

Longing for the world above, a loving aspiration to it – is our joy, makes even a painful old age regally magnificent, full of expectation of the merciful "embrace of the Father" (Luke 15:20).
229 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 19:06:01 "... ይሰርቁኛል፤ ግን አላውቅም። ለአንተ እንዳልገዛም ያስደስቱኛል። ወደ አንተ መለመንን መማለድን ይከለክሉኛል። እነርሱ ወደ አንተ በዕንባ እንደምጮህ ያውቃሉና"

[_ውዳሴ አምላክ ዘረቡዕ_]
214 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:49:27 "ነፍሴ ሆይ! የምትድኝበትን እኔ እነግርሻለሁ
ከዚህ ሁሉ ይልቅ ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም ጩሂ፣እንዲህም_በይ የብርሃን እናት ሆይ! በልጅሽ_ፊት_በደልሁ_ኃጢአቴን_አስተስርይልኝ፡፡"

[_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_]
278 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:49:27 ቅዱስ ባስልዮስ እንዲህ ይላል "እግዚአብሔር ሰውን ከምድር አፈር አበጀው ከሚል ቃል ውስጥ የሰው ልጅ /ኢምንት/ መሆኑን ታላቅ መሆኑንም እንረዳለን የተፈጠረበትን አፈር ብቻ ካየህ የሰው ልጅ ኢምንት/ምንም/ ነው የተፈጠረበትን ክብር ካየህ ግን የሰው ልጅ ታላቅ ነው በእርግጥም እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ጨረቃና ከዋክብትን የፈጠረበትን መንገድ ሰውን ከፈጠረበት መንገድ ጋር ሲነጻጸር የሰው ልጅ ከሁሉም ክብር ነው።

አዳም በገነት ሳለ በደብረ ታቦር በሁለተኛው አዳም መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የተገለጸው ድንቅ ብርሃን አዳም በገነት እያለ ከነበረው ብርሃን ጋር አንድ ነበረ።

እንስሳት ብርሃን የለበሰውን አዳምን ሲመለከቱ እንደ ታቦር ደቀ መዝሙር በፍርሃት ከመውደቅ ምንም አማራጭ አልነበራቸውም።

እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ክቡርነት ሲያመለክት ጭቃ ይዞ ታየ
የሰው ልጅ ክቡር ሲሆን አላወቀም።

[_አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫ_]
2.0K viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 07:58:03 ነገር ግን አንድ ነገረ አስታውስ"ወርቅን ሊያጠራ የሚፈልግ ሰው እሳቱን አንድ ጊዜ የሚያነድ እንደገና መልሶ የሚያጠፋ ከሆነ ለስራው አይጠቅመውም። እንዲሁ ነፍስ አነድ ጊዜ ለእግዚአብሔር የምትገዛ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቸል የምትል ከሆነ አይጠቅማትም"[አበው]

"ዛሬን ለሰይጣን ነገን ደግሞ ለእግዚአብሔር አትስጡ!"[ታላቁ ቅዱስ ጎሮጎርዮስ]


[_ዲያቆን አቤሴሎም ድንቅአለም_]
HU ሰኔ 28-2014 ዓ.ም
1.4K viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 07:58:03 ኧ..ይገርምሀል! አለኝ"በእንባ የረጠቡ ጉንጮን በእጁ በያዘው ሶፍት እያደረቀ "በአንድ ወቅት በእግዚአብሔር ፊት ለጸሎት ለመቆም ወደ መቅደሱም ለመግባት የሌሊቱን ጨለማ መገፈፍ መታገስ የሚሳነኝ ነበርኩ! ...አሁን ግን¡ ...ስሜቱን መቋቋም ስላቃተው አንገቱን በእግሮቹ መሀል ደፍቶ ማልቀሱን ቀጠለ። .. ቀና ላደርገው እንባውንም ልጠርግለት አልፈለግሁኝም ምክንያቱም በእንባው እግዚአብሔርን ያገኘዋል።"[ይህ ጊዜ ይቆየን]

አቡነ ሺኖዳ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ላለን ሰዎች ከኃጢአተታችን የእግዚአብሔር ቸርነት እንደሚበልጥ አውቀን ተስፋ እንዳንቆርጥ ሲናገሩ እንዲህ አሉ"እግዚአብሔር ድካምህን እንደሚያውቅና እስካሁን ድረስም እንደሚወድህ እርግጠኛ ሁን ! በኃጢአት ውስጥ ብትሆንም እግዚአብሔር ሊያድንህ ወደ እርሱ ሊያቀርብህና ወደ ቀደመ ደረጃህ ሊመልስህ እንደሚሰራ እመን ። አዳም የዳነው ንሥሐ ለመግባት ባደረገው ሙከራ ሳይሆን አዳምን_በተመለከተው_የእግዚአብሔር_ቸርነት_ነው ።"

በነበርኩ አለኝ!

"እግዚአብሄርን የቀመሰች ነፍስ ኃጢኣት ምን ያክል እሳት ሆኖ እንደሚያቃጥላት ተመልከቱ። ወንድሜ ተነስ! አንተ አስቀድመው ታማኝ አገልጋይ እንደነበሩት ኋላ ግን ሰም አጠራራውቸ ከምድር እንደጠፋ የሚያልፈውን አለም ወደው የሚታየውን እንጂ የማይታየውን ባለማየት አንደጠፋ ዴማሳውያን አትሆንም። ይልቁንም
"የጦር መሪዎች--> ሰማዕታት"
"ቆነጃጅት --> ደናግላን"
"ነገስታት --> መናንያን"
"ገዳዎች-->ሟች"
"ተቃዋሚዎች --> ሐዋርያት"
"አሳዳጆች --> ወንጌላውያን" ለሆኑለት አለታችን ክርስቶስ በቁርጥ ህሊና በትህትና ሆነህ ታገለግለዋለህ!

ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ "ነበርኩ" ሊል ስለፈለገ 'የኋላ ታሪክ ያለው ጻድቅ' መሆኑን ሲገልጥልን የቅዱሳን ሐዋርያትን ስም ሲዘረዝር ራሱን"ቀራጩ ማቴዎስ" ብሎ ፃፈ። ቅዱስ ጳውሎስ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ኃይል እንደተሰጠው ታማኝ አገልጋይም ተደርጎ መሾሙን ከገለጠ በኋላ "ነበርኩ" በማለት አሳዳጅነተቱን'ተሳዳቢ አንገላችም ካለ በኋላ ከእግዚአብሔር ትዕግስትና ምህረት የሚበልጥ ኃጢአት የለም ሲል "ምንም"ስሆን በማለት "ምንም" ለሆንን ለእኛ ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ አለም እንደመጣ ይነግረናል። ቅዱስ አውግስጢኖስ 'ነበርኩ'በማለት የቀደመ የወንበዴነት ህይወቱን እና አሁን ያለበትን ህይወት የማይነፃፀር መሆኑን ሲገለፅ" አንተ በእኔ ውስጥ እያለህ እኔ አንተን በውጪ እፈልግህ ነበር"አለ። ተፈትነው ወድቀው የቀሩ ይሁዳንና ዲያቆኑ ኒቆላዎስን ደግሞ ተመልከቱ " ወግታ የጣለቻቸው ብዙ ናቸውና፤ እርስዋም የገደለቻቸው እጅግ ብዙ ናቸው። "(መጽሐፈ ምሳሌ 7:26)

እጅግ ልብን የሚመስጥ ህይወት የኖሩትን ከቀራጭነት ከዝሙት ተዳዳሪነት ከክህደት ከምንፍቅና ወደ ቅድስና የገቡትን በዙሪያችን የእግዚአብሔርን ምህረትና ፍቅር የምንመለከትባቸውን ብንመለከት መልካም ነው። እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ ................በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ ............የጸናውን አስቡ።[ዕብ 12:1-3]


ብዙ ጊዜ ብዙዎቻችን እግዚአብሔር ቅዱሳን ትዕዛዛቱን የሰጠን ሰው መሆናችንን ረስቶት ይመስል 'ሰው' መሆናችንን ለደካማነታችን ምክንያት አድርገን አናቀርባለን። አንድ አረጋዊ ለደካማነታችን ሰው መሆናችንን ምክንያት አድርገን ልናቀርብ እንደማይገባ ይልቁንም ሰው በመሆናችን እንደ መላዕክት ልንሆን እንደሚገባን ሲገልፁ እንዲህ አሉ"ሰው መሆንህን ለድካምህ እንደ ምክንያት አታቅርብ በትዕግስት መልዐክ መሆን ትችላለህና! ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚወዱትና ፈቃዱን ለሚፈፅሙት እንደ መላዕክት ይሆኑ ዘንድ አስደርጓቸዋልና።" እስኪ ስለዚህ ሰውነት እናውቅ ዘንድ አይኖቻችንን ቅዱስ ዳዊት ለልጁ ለሰለሞን ወደመከረው ምክር እናቅና"" በርታ ሰውም ሁን፤ የምታደርገውንና የምትሄድበትን ሁሉ ታከናውን ዘንድ............ በመንገዱም ትሄድ ዘንድ፥ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቅ።"[መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 2:3]

በምድር ላይ እንደ እንስሳ መኖር ስትመርጥ እና እንደ ሰው ለመኖር አቅም ስታጣ እንደ መላዕክት የኖሩ አበው መነኮሳተት በፀጋቸውና በተጋድሎአቸው በፍፁምም አፍቃሪነታቸው ከመላዕክት ይበልጣሉ የተባሉ[እነ ቅዱስ ጳውሎስ] ሰዎችን መኖራቸውን አስታውስ። ይህ ማለት ሰው በመሆናችን የሚመጣብን ፈተና የለም ማለት ሳይሆን ሰው በመሆናችን ኃጢአትን መቃወም እና በእግዚአብሔር ኃይል ድል መንሳት እንችላለን ማለት ነው። ቅዱሳን አባቶች ማለት የዲያቢሎስ ቀስት ያልተወረወረባቸው ማለት ሳይሆኑ እምነታቸው ጋሻ የሆናቸው ማለት ናቸው።[" በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤"(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6:16)

ስለዚህ እነርሱ "ገፋኸኝ፥ ለመውደቅም ተንገዳገድሁ፤ እግዚአብሔር ግን አገዘኝ።"" በማለት ሲዘምሩ። አንዳንዶቻችን ከግዴለሽነታችን እና የዲያቢሎስን ሴራ ካለማወቃችን የተነሳ"እኔ ግን ሳልጨነቅ ሳትሁ" የሚለው መዝሙር እንኳ ልባችንን አልነካንም። ወንድሜ አንዳንድ ጊዜ መንገዳገዳችን ወይንም በእግዚአብሔር ቤት ጸንተን አለመቆማችን ወደ መውደቅ እንጂ ወደ መቆም ሊመራን የማይችል እስኪመስለን ድረስ ተስፋ እንቆርጣለን። ነገር ግን አውነታው እንደዚያ አይደለም እግዚአብሔር ውድቀታችንን የመይሻ አምላክ መሆኑን በመፅሐፍ ብቻ የነገረን አይደለም 'አይተንማል'።

"እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።" ያለ አምላክ የሚተወን ይመስላችኋል? በፍጹም! አቡነ ሺኖዳ እግዚአብሔር በማንኛውም ጊዜ ከእኛ ጋር እንዳለ እና በእኛ የእምነት ማነስ እና የእውቀት ውስንነተት ምክንያት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ያልወጣ ለሚመስለን በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ እንድንበረታ እና እግዚአብሔር ተስፋ እንድናደርግ እንዲህ አሉ" ለመንጋው ሁሉ በጎ እንደሚመኝ እንደ መልካም እረኛ እግዚአብሔርም በፍጥረታቱ በሙሉ ያለምንም ጥርጥር በዝምታ ይሠራል። ይሁን እንጂ ሰዎች በመከራ ውስጥ ሆነው የእግዚአብሔር መልስ ከዘገየባቸው እንደማይሰራ አድርገው ያስባሉ። እነርሱ እግዚአብሔር አይሰራም በሚያስቡበት ሰዓት ሁሉ እርሱ ግን ለእነርሱ በጥልቅ እየሰራ ነው። ሰዎች ይህንን ስለማይገነዘቡ የእግዚአብሔርን ሥራና የስራውን ውጤት ፈጥነው ለማየት ይፈልጋሉ። እነዚህ ሰዎች ግን በእምነታቸው ያመኑትን በዓይነቻቸው እስኪመለከቱ ድረስ ሊቆዩ ይገባቸዋል።" እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ በርታ ልብህም ይጽና እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፡፡" መዝ 26 ፥ 14። " እግዚአብሔር ዘወትር በስራ ላይ ነው ወይ ጉዳያችንን እየሰራ ነው ወይንም እኛን እየሰራን ነው። ይህ ቃል ሊታመንና ሁላችን ልንቀበለው የሚገባ ነው።

እግዚአብሔር አየተንገዳገድንም እየተንፏቀቅንም ቢሆን ወደእርሱ ለመድረስ የምንተጋውን ይቅርና የወደቁትን ለማንሳት ሰው የሆነ ለደካማዎች ኃይል ይሆን ዘንድ በሰው ዘንድ ደካማ መስሎ የታየ እርሱን በመተማመን ለሚጠባበቁትም የማያሳፍር ተስፍ የሚሰጥ ነው።
1.4K viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 11:18:47 Don't say, "I can't." This word is not Christian. The Christian word: "I can do everything." But not by itself, but about the Lord strengthening us.
360 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 12:16:24 የሕይወትህን መንገድ ወደ እግዚአብሔር ብታደርግ ያን ጊዜ እውነተኛውን እረፍት ታገኛለህ።

[አባ ሙሴ ጸሊም]
442 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 09:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 12:10:03 [_ደስታ ማለት የልብ ንፅህና ነው_]


ከራሳቸው ውጪ ደስታን የሚፈልጉ እንደምን ምስኪን ናቸው ደስታን በባእድ ምድር በጉዞ የሚፈልጉ አሉ፤ በሀብትና በዝና መካከል የሚፈልጉ ወገኖች አሉ፤ በታላቅ ይዞታና በንብረት መካከል የሚፈልጉ አሉ፤ መራራ ፍፃሜ ባላቸው በውበትና በተቃራኒ ፆታ መካከል የሚፈልጉ አሉ።

በተመሳሳይ ሁኔታ ደስታን ከራሳችን ውጪ ለመገንባት መሞከር በተደጋጋሚ በመሬት ርእደት በሚናወጥ ሥፍራ ላይ እንደ መገንባት፤ ደስታ የሚገኘው በእኛው ውስጥ እንጂ ከእኛ ውጪ አይደለም፤ ምስጉን ማለት ይህን ሁኔታ የተገነዘበ ሰው ነው።

ደስታ ማለት የልብ ንፅህና ነው፤ እንዲህ አይነቱን ልብ እግዚአብሔር ማደሪያ ያደርገዋልና፤ ስለዚህ ንፁህ ልብ ያላቸው ወገኖች ክርስቶስ እንዲህ ይላቸዋል፤ በእነሱ እኖራለሁ፣ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ አምላካቸው እሆናለሁ እነሱም ሕዝቤ ይሆናሉ። 2ኛ ቆሮ 6፥16

[_አባ ሳራባሙን_]  
                           
461 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 20:56:41
458 viewsንፁህ ልብን ፍጠርልኝ , 17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ