Get Mystery Box with random crypto!

የቡና ጉዳይ ይመለከተኛል

የቴሌግራም ቻናል አርማ bunawustiawaki — የቡና ጉዳይ ይመለከተኛል
የቴሌግራም ቻናል አርማ bunawustiawaki — የቡና ጉዳይ ይመለከተኛል
የሰርጥ አድራሻ: @bunawustiawaki
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 207
የሰርጥ መግለጫ

ለክለቡ ቅርብ የሆነ መረጃ የምታገኙበት ምርጥ ቻናል
ስለ ክለቤ ምን አቃለው ብለው እራሶትንም ለመፈተሽ ምርጥ ቻናል ይሄ ነው ተቀላቀሉ
https://t.me/bunawustiawaki/561
ለአስተያየት
@yebunagudayyemelketghal_bot
ፌስ ቡክ አካውንታችን ይህ ነው
https://www.facebook.com/105274797474854/posts/143281497007517/?app=fbl

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-13 20:54:04 በዝውውር መስኮቱ 17 ተጨዋቾች ብቻ ዝውውራቸው ጸድቋል

#እስካሁን_ፌዴሬሽን_ያወቀው_ዝውውር_የአራት_ክለቦችን_ብቻ_ነው።

ሀምሌ 1 በይፋ በተከፈተው የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ባለፉት ስድስት ቀናት ብቻ ህጋዊ ዝውውር ያደረጉት ተጨዋቾች ከ20 እንደማይበልጡ ተነገረ።
ከክለቦቹ ታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ

#ኢትዮጵያ_ቡና ብሩክ በየነ፣ አብዱልከሪም ወርቁ፣ ጫላ ተሺታ፣ ሀይለሚካኤል አደፍረስ፣ አብዱል ሀፊዝ ቶፊቅና መስፍን ታፈሰን ሲያስፈርም የሮቤል ተ/ሚካኤል ውልን ማራዘሙ ታውቋል። በርካታ ዝውውር እያደረገ ነው የተባለው

#መከላከያ በረከት ደስ፤ ዳግም ተፈራ፣ ምንይሉ ወንድሙና ሳሙኤል ሳሊሶን ሲያስፈርም

#ፋሲል_ከነማ በበኩሉ የበዛብህ መለዮ፣ የሱራፌል ዳኛቸውና የሽመክት ጉግሳን ውል ሲያድስ

#ባህርዳር_ከተማ ፍጹም ጥላሁን፣ ያሬድ ባዬህና ዱሬሳ ሹቢሳን ማስፈረሙ ታውቋል።

ከ16ቱ ክለቦች እስካሁን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ማረጋገጫ ያገኙት #አራት_ክለቦች ብቻ መሆናቸው ታውቋል።

ምንጭ #ሀትሪክ_ስርአት

@bunawuatiawaki
@bunawustiawaki
73 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 22:39:35 የግል ምልከታችን ነው

#በነገራችን_ላይ_ዛሬ_ልፅፍ_የወደድኩት_ስለ_ክለባችን_የበላይ_ነን_ስለሚሉ_አመራሮች_እና_ስለ_ክለባችን_ፋይናንስ_ነው

እውነት ግን ቡናን ትወዱታላቹ ወይስ ደሞዙን ላለማጣት ነው የምትቆዩት
እንዴት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንኳን #ለተሻለ_ሰው_ስልጣናቹን_አታስረክቡም በመጀመሪያ ግባቹ ምንድነው ወይም አላማቹ ምንድነው ግልፅ አርጉልን በመጀመሪያ ውድድር አመቱ እንዳለቀ መገማገም ሲኖርብን እናንተ ግን እንዳትገመገሙ የውይይት መድረክ አትከፍቱም። እንዲሁም ደጋፊውን ለማራቅ የሚሰሩ የሌላ ክለብ ፍቅር ያለባቸውን አማራሮች እየተመለከትን ነው

#እንደኛ_ክለብ_የህዝብ_ሀብት_ያለው_የለም_ግን_ምንም_እየተሰራበት_አይደለም_ምክንያቱም_አመራር_ላይ_ያሉት_ሰዎች_በልምድ_እንጅ_በእውቀት_ስለማይመሩ።

እስኪ ለተሻለና በእውቀት ተወዳድሮ ፕሮፓዛል አቅርቦ ለሚአሸንፍ እንሰጣለን በሉ ያኔ ሊወዳደር የሚመጣውን ሰው ብዛቱን ታዩታላቹ ምክንያቱም ያልተሰራበት ክለብ እንደሆነ ሁሉም ያውቃል

እባካቹ የክለቡ ደጋፊ እና ወዳጅ ከሆናቹ በመጅመሪያ #አቶ_ገዛሀኝ እባክህ ቡናን ልቀቅልን በመቀጠል #ለክለባችን_ጀግና_እና_እስከዛሬ_ላቆዩልን_ለመቶ_አለቃ_ፍቃደ_ማሞ_የክብር_ሽኝት_እና_የክለቡ_አምባሳደር_ይደረጉልን ከዛ የሚመጥኑ ሰዎች ይቀጠሩ

በመቀጠል መታወቂያ ለማውጣት ሂደን እንድንመናጨቅ አንፈልግም በትክክለኛ እና ክለቡን በሚአከብሩ ሰዎች መስተናገድ አለብን

ገቢአችን ፋይናንሳችን መስተካከል አለበት ከሀበሻ የሚበልጥ ስፖንሰር አለ ጨዋታችን በዲኤስ ቲቪ ስለሚተላለፍ #ከውጭ_ባንኮች_ጋር_ድርድር_አድርጎ ማድረግ ይቻላል ለምን እስክንቀደም ትጠብቃላቹ

በመጨረሻም ያለፈው አመራር ያስጀመረውን #የቤተሰብ_እሩጫም እንደቀልድ 2 አመት ሊሞላን ነው ከተውነው እንዴት ክለባችን በፋይናንስ እንደግፍ እየተባለ ይህን ያክል ገቢ ያለውን ሩጫ እንተወዋለን ወደ ቀድሞ ቦታው እንዲመለስ እንፈልጋለን

በቅርቡ የተወሰኑትን ውሳኔ እናከብራለን #ከካሳዬ ጋር ያለን ነገር በቀጣይ ቀናት እንመለስበት እና የተጫዋቾች መውጣት ላይ ግን ገና የሚቀሩ አሉ #ደሞዝ_እንጅ_ግልጋሎት_የሌላቸው በቀጣይ ከነ ስም ዝርዝራቸው እንገልፃለን ምክንያቱን አስደግፈን

#ከታፈሰና_ከዊሊያም ጋር ግን ስለተለያየን ትክክለኛ ውሳኔ ነው በተለይ #ከዲስፒሊን ጋር አይሆኑም ሁለቱም ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብለን እናምናለን #ከሀይሌ_ገብረ_ትንሳኤ ጋር ግን ቅር ቢለንም የክለቡ ውሳኔ ስለሆነ እናከብራለን

ለመወያይት ክፍት ነው ግሩፓችን ሀሳብ ይሰጥበት

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
93 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 22:37:07
የግል ምልከታችን ነው
፩ የኢትዮጵያ ቡና አመራሮች በቃቹ
፪ የክለባችንን ፋይናንስ ለታሻለ ሰው አስረክቡ
፫ የተረሳው ሩጫ ይመልስልን
፬ ክለቡን ፋይናንስ የሚአቃውሱ ደሞዝተኛ ተጫዋቾች ይቀነሱ
፭ በዲሲፒሊን ምክንያት የተቀነሱትን ተጫዋቾች እኛም በመቀነሳቸው እንስማማለን

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
85 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 09:24:31 ለቀጣይ ዓመት የስከዛሬውን መበሻሸቅ መጨቃጨቅ አቆይተነው በሁሉም መስክ የተሻለ ስራ እንስራ
ክለቡ ሃላፊዎች ስራችሁን ግዴታችሁን ቦታችሁን ጠንቅቃችሁ መርምራችሁ እቅድ አውጡ የተግባር ስራዎች ስሩ እኛም ገምግመን ይሄ አልተሰራም ይሄ ተሰርቶል ለዚህ ስራ እናመሰግናለን ለዚህ ስራ እንወቅሳለን እንድል ሃሳባችሁ አሳውቁን እኛም በጨዋነት እንገመግማለን የተሰራ እናደንቃለን ካልተሰራ እንወቅሳለን
ደጋፊ ማህበሩ እንደ አዲስ ተመርጦል እቅዶች አውጥታችሁ ንገሩን እሱን ለመተግበር ስሩ እኛም እናግዛችሁ እንገምግማችሁ ይሄ ተሰርቶል ይሄ ይቀራል እንበል እቅድና የተግባር ስራውን ለሁሉም ደጋፊ እንዲደርስ አርጉ ስራዎች ይሰሩ ሁሉም በአንድ ጀምበር አይሰራም በሂደት ነው ግን ለዛ ነገር መጀመር ግድ ነው ብዙ ነገሮች በእቅድ ብቻ እንዳይቀሩ
የክለቡ የሚዲያ ተቋም ፌስቡክ ሬዲዬ የተዘጋው ቲቪ ፕሮግራም የክለቡን ስም ከፍ የሚያደርገው የክለቡን መረጃ ለሁሉም ተደራሽ የሚያደርገው የእናተ ትልቅ ስራ ነው እና እናተም እንዲሁ በእናተ ዘርፍ የተደራጀ ነገር እንጠብቃለን
ይቀጥላል
ምንጭ #ቡናውያን_የዘር_ሀረግ

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
108 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 21:11:51
አቡኪ ከዛሬው ጨዋታ ቡሀላ የተናገረው ንግግር !

አቡኪ ከተናገራቸው መሀል የተወሰኑትን

#የቡና_ደጋፊ_ማለት_ለኔ_የተለየ_ነው

#ዋንጫ_ሳልበላ_በመውጣቴ_በጣም_አዝኛለው
በቀጣይ እንድትበሉ እመኛለው የምትበሉም ይመስለኛል

አለ ግን እውነታውን እንመልከተውና በዚህ እስኳድ ሊአውም ዋናውን ጀግና አቢኪን አተን ምን ተስፋ አለን ግን እስኪ እንወያይበት በግሩፓችን

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
158 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 21:07:15 ሰኔ 19 ቀን
የኢትዮጵያ_ቡና_ቀን
የኢትዮጵያ ቡና 46ኛ አመታችን እና የአቡበከር ናስር የሽኝት ፕሮግራም ይካሄዳል ፡፡

ስለ አቡበከር ሽኝት እና ስለ ክለባችን ስፓንሰሮች በቂ እውቀት ከፈለጉ ሰኔ ፩፱ እንዳይቀሩ
#አቡኪ_ጀግናችንን_በምትሄድበት_ሁሉ_ይቅናህ_ለማለት_ያለችን_ቀን

እንዲሁም የቀድሞ አመራሮቻችን ቢአናድዱንም ቢአስደስቱንም በስራቸው በአደረጉልን መልካም ነገር እናመሰግናለን የምንለበት ቀን ሰኔ 19

የሀበሻ ምርት አየተጠቀምን የምንዝናናበት ቀን መግቢያ እንዳይረሳ #ቢጫው_ማልያ_እና_ቢጫው_ማልያ_ብቻ

በእለቱም በአነስተኛ ቅናሽ ቢጫው ማልያ ለገብያ ይቀርባል

ቦታው ፡- ጀሞ የክለባችን ስታዲየም መገንቢያ ቦታ

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
190 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 20:49:27 የምሽቱ ጨዋታ በቡና አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ አሰልጣኞች ሀሳባቸውን ለሶከር ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ – ኢትዮጵያ ቡና

#ስለ_ጨዋታው
“ጨዋታው ጥሩ ነበር። ያው እነሱ አብዛኛው ቁጥራቸውን ከኳስ ኋላ አድርገው በመከላከል በሚገኙ ክፍተቶች በሚነጠቁ ኳሶችየግብ ዕድል ለመፍጠር ነበር ያሰቡት። ስለዚህ እኛ የኳስ ባለቤትነታችንን አስጠብቀን ሰው ሜዳ ለመግባት ስናስብ ያንንም ታሳቢ እያደረግን ነው። አንድ ሁለት ከዕረፍት በፊት የተነጠቁ ኳሶች አሉ። እነዛን ማስወገድ አለብን ፤ እየተቆጣጠርን እነሱ ሜዳ በመጫወት ከዛ በእነሱ ሜዳ ደግሞ እንዴት ነው ክፍተት ማግኘት የሚቻለው ? ምክንያቱም ብዙ የቁጥር ክምችት ስላለ የእኛም የእነሱም ተጫዋቾች ፤ በቀላሉ ክፍትት ማግኘት አይቻልም። ያንን እንዴት ነው ማግኘት የምንችለው የሚለውን በዕረፍት ሰዓት ለማድረግ ሞክረናል።

#የአቡበከር_ቅያሪ_ልዩነት_ስለመፍጠሩ

“አቡበከር ሲገባ ብዙ የተጋጣሚ ቡድን ተጫዋቾች ራሳቸው ሜዳ ላይ ስላሉ ክፍተት እና ነፃነት እንደማያገኝ ግልፅ ነው ፤ ከሚጫወቱበት መንገድ አንፃር። ጠቀሜታው ተጋጣሚ እሱ ላይ የሚያደርገው ትኩረት አለ ፤ በሁለት ሦስት ተጫዋቾች። በዛ ሂደት ውስጥ ሌሎች የእኛ ተጫዋቾች ነፃነት ያገኛሉ። ከዛ አንፃር ጠቀሜታ ነበረው።

#ስለ_ውጤቱ_ጠቃሚነት

“ከሥነ ልቦና አንፃር ትልቅ ጠቀሜታ አለው። ተሸንፈህ ስትመጣ እና አሸንፈህ ስትመጣ ልዩነት አለው። የምታሳልፋቸው የልምምድ ጊዜያቶች ላይም የሚያመጣው ልየነት አለ። ግን እኛ ሁሌም ትኩረት ማደረግ አለብን ብዬ የማምነው ተሸነፍንም አሸነፍንም ምንድነው ማሳደግ ፣ ማረም ያለብን ? የሚለው ላይ ነው። ማድረግ ያልቻልናቸው ነገሮች ምንድን ናቸው? የሚለው ሁል ጊዜ ከዋናው ችግር እንዳንወጣ ያደርገናል። አንዳንድ ጊዜ ሽንፈቶች ሲመጡ ከዋናው ነገር ትወጣለህ። የእኛ ዋናው እና መሰረታዊው ነገር ሜዳው ላይ የምንሰራው ነገር ነው። ስለዚህ በቀጣዩ ጨዋታ ከዚህ ጨዋታ ተነስተን ምንድነው የምናሻሽለው የሚለውን እናያለን። ምክንያቱም ተጋጣሚም እኛን ያየናል ፤ እዛ ላይ ነው ትኩረት የምናደርገው።”

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
264 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-16 22:40:30
አራተኛው የኢቢሲ የ2013 አመታዊ ምርጥ የእግር ኳስ ተጫዋች ዘርፍ አሸናፊ በአሁን ሰዓት በሸራተን አዲስ ሆቴል ይፋ ተደርጓል

በወንድ የእግር ኳስ ዘርፍ #የኢትዮጵያ_ቡና እና #የዋልያዎቹ የፊት መስመር ተጫዋች #አቡበከር_ናስር አሸናፊ ሆኖ ተመርጧል ።

#EBC

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
197 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 22:30:39
ሰበር ዜና
#ኢትዮጵያ ቡና በደርቢው ጨዋታ የዲሲፕሊን ቅጣት ተላለፈበት በዚህም መሠረት በሸገር ደርቢ ጨዋታ ላይ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች የተጋጣሚ ቡድን አመራሮችን ስለመሳደባቸው እና ቁርጥራጭ ወንበሮችን ወደሜዳ ስለመወርወራቸው እንዲሁም 42 ወንበሮች የተቆረጡ፣ የተሰነጠቁ ወይም የተነቀሉ ስለመሆናቸው ሪፖርት በክለቡ ላይ መቅረቡን በመግለፅ የክለቡ ደጋፊዎች ለፈፀሙት ጥፋትና ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ ክለቡ መቀጣቱ እንዲሁም ደጋፊዎቹም ሊታረሙ አለመቻላቸውን ታሳቢ በማድረግ ክለቡ የሰባ አምስት ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል ተወስኗል።

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
237 viewsስታቁኝ ታፈቅሩኛላቹ ስለዚህ አትወቁኝ ወንዶች, 19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-28 23:10:02
RIDE እና ቡና ነገ ይጣመራሉ

አዲሱ የክለባችን ኢትዮጵያ ቡና ስፖንሰር RIDE
!

ቀን :- #ረቡዕ
ሰአት:- ረፋድ 03:30 ላይ
ቦታ #በሸራተን_አዲስ_ሆቴል

በተዘጋጀ መድረክ ላይ ክለባችን #ኢትዮጵያ_ቡና በግልፅ ላልታወቀ ረጅም ዓመታት የሚቆይ #ከRIDE ጋር #የማልያ_ላይ_ስፖንሰርሺፕ
ስምምነት በይፋ የሚፈፅም ይሆናል።

@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
241 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ