2022-07-11 22:39:35
የግል ምልከታችን ነው
#በነገራችን_ላይ_ዛሬ_ልፅፍ_የወደድኩት_ስለ_ክለባችን_የበላይ_ነን_ስለሚሉ_አመራሮች_እና_ስለ_ክለባችን_ፋይናንስ_ነው
እውነት ግን ቡናን ትወዱታላቹ ወይስ ደሞዙን ላለማጣት ነው የምትቆዩት
እንዴት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንኳን #ለተሻለ_ሰው_ስልጣናቹን_አታስረክቡም በመጀመሪያ ግባቹ ምንድነው ወይም አላማቹ ምንድነው ግልፅ አርጉልን በመጀመሪያ ውድድር አመቱ እንዳለቀ መገማገም ሲኖርብን እናንተ ግን እንዳትገመገሙ የውይይት መድረክ አትከፍቱም። እንዲሁም ደጋፊውን ለማራቅ የሚሰሩ የሌላ ክለብ ፍቅር ያለባቸውን አማራሮች እየተመለከትን ነው
#እንደኛ_ክለብ_የህዝብ_ሀብት_ያለው_የለም_ግን_ምንም_እየተሰራበት_አይደለም_ምክንያቱም_አመራር_ላይ_ያሉት_ሰዎች_በልምድ_እንጅ_በእውቀት_ስለማይመሩ።
እስኪ ለተሻለና በእውቀት ተወዳድሮ ፕሮፓዛል አቅርቦ ለሚአሸንፍ እንሰጣለን በሉ ያኔ ሊወዳደር የሚመጣውን ሰው ብዛቱን ታዩታላቹ ምክንያቱም ያልተሰራበት ክለብ እንደሆነ ሁሉም ያውቃል
እባካቹ የክለቡ ደጋፊ እና ወዳጅ ከሆናቹ በመጅመሪያ #አቶ_ገዛሀኝ እባክህ ቡናን ልቀቅልን በመቀጠል #ለክለባችን_ጀግና_እና_እስከዛሬ_ላቆዩልን_ለመቶ_አለቃ_ፍቃደ_ማሞ_የክብር_ሽኝት_እና_የክለቡ_አምባሳደር_ይደረጉልን ከዛ የሚመጥኑ ሰዎች ይቀጠሩ
በመቀጠል መታወቂያ ለማውጣት ሂደን እንድንመናጨቅ አንፈልግም በትክክለኛ እና ክለቡን በሚአከብሩ ሰዎች መስተናገድ አለብን
ገቢአችን ፋይናንሳችን መስተካከል አለበት ከሀበሻ የሚበልጥ ስፖንሰር አለ ጨዋታችን በዲኤስ ቲቪ ስለሚተላለፍ #ከውጭ_ባንኮች_ጋር_ድርድር_አድርጎ ማድረግ ይቻላል ለምን እስክንቀደም ትጠብቃላቹ
በመጨረሻም ያለፈው አመራር ያስጀመረውን #የቤተሰብ_እሩጫም እንደቀልድ 2 አመት ሊሞላን ነው ከተውነው እንዴት ክለባችን በፋይናንስ እንደግፍ እየተባለ ይህን ያክል ገቢ ያለውን ሩጫ እንተወዋለን ወደ ቀድሞ ቦታው እንዲመለስ እንፈልጋለን
በቅርቡ የተወሰኑትን ውሳኔ እናከብራለን #ከካሳዬ ጋር ያለን ነገር በቀጣይ ቀናት እንመለስበት እና የተጫዋቾች መውጣት ላይ ግን ገና የሚቀሩ አሉ #ደሞዝ_እንጅ_ግልጋሎት_የሌላቸው በቀጣይ ከነ ስም ዝርዝራቸው እንገልፃለን ምክንያቱን አስደግፈን
#ከታፈሰና_ከዊሊያም ጋር ግን ስለተለያየን ትክክለኛ ውሳኔ ነው በተለይ #ከዲስፒሊን ጋር አይሆኑም ሁለቱም ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብለን እናምናለን #ከሀይሌ_ገብረ_ትንሳኤ ጋር ግን ቅር ቢለንም የክለቡ ውሳኔ ስለሆነ እናከብራለን
ለመወያይት ክፍት ነው ግሩፓችን ሀሳብ ይሰጥበት
@bunawustiawaki
@bunawustiawaki
93 views Fisho (የከቡየ ልጅ) , 19:39