Get Mystery Box with random crypto!

Orthodox Tewahedo Mezmur

የቴሌግራም ቻናል አርማ firstorthodoxmezemurchannel — Orthodox Tewahedo Mezmur O
የቴሌግራም ቻናል አርማ firstorthodoxmezemurchannel — Orthodox Tewahedo Mezmur
የሰርጥ አድራሻ: @firstorthodoxmezemurchannel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.77K

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-22 00:05:32
1.8K views21:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 10:37:46

2.0K views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 22:29:25 መልክአ ሕማማት
በ pdf እንሆ ብለናል፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር
ለሌሎች ሼር ማድረግዎን አይርሱ
https://t.me/firstorthodoxmezemurchannel
7.3K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 22:29:25
1.7K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 22:29:25
1.5K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 22:29:25
1.3K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 22:29:24 #ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘሰሙነ_ሕማማት፡፡
በሰሙነ ሕማማት የሚባሉትን በአጭሩ ስንቃኛቸው፡፡
(#ለዐርቡ_ጸሎት_እንደ_ዘማች_ስለሚያገለግል) ዐርብ ከምንለቀው የዐርቡ ጸሎት ጋራ አብረን የምንጠቀምበት ስለሆነ በቃል ጭምር አጥኑት፡፡
/ይህን ጽሑድ በአድካሚ ሁኔታ እንደ ንብ ቀስመንና ሰብስበን አዘጋጅተንላችኋል፤ ላልደሰረሰው አዳርሱ፤ ማተሚያ ቤት ያላችሁ አትማችሁ ስጡ፡፡/
፠የሰሙነ ሕማማት ጸሎት የሚደረገው በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት መሠረትነት 7ት ጊዜ ነው፡፡ ለዚሁ አገልግሎት ታላቁ ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ7ቱ ጊዜያት ከፋፍሎ የደረሰው መልክአ ሕማማትም አብሮ በዜማ ይደርሳል፡፡ (መልክአ ሕማማትን ለብቻው አዘጋጅተን ለጥፈንላችኋል)
#የጸሎቱ_አደራረስ_ሥርዐትም ከዚህ እንደሚከተለው ነው፤
፠ደወልና ቃጭል ይመታል፤
፠ጸሎታት(ሙሉ ውዳሴ ማርያምና ዳዊት)ና (የኦሪትና የነቢያት) ምንባባት ይደርሳል፤
፠የተአምር መቅድምና ምንባብ ይነበባል፤ የተአምራት መርገፍ በዜማ ይባላል፡፡
፠የወንጌል አቡን በቅብብሎሽ ይደርሳል፤
፠ምስባክ ይሰበካል ፥ ወንጌል ይነበባል፡፡
#1ኛ_ስግደት፤ ‹‹ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ›› እያለ ቃጭል ሲያሰማ 22ት ጊዜ ‹‹እግዚኦ ተሣሃለነ›› እየተባለ ይሰገዳል፡፡
#2ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለከ ኀይል ክብር ወስብሐት›› የሚለውን በቅብብሎሽ 6ት ፥ 6ት ጊዜ (በድምሩ 12)፤ 7ኛውን በኅብረት እየተሰገደ ይባላል፡፡
#3ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለአምላክ ይደሉ›› የሚለውን 1ኛውን ዙር በቅብሎሽ፤ 2ኛውን ዙር እያስተዛዘሉ፤ ከስግደት ጋራ ይባላል፡፡
#4ኛ_ስግደት፤ ‹‹ክርስቶስ አምላክነ…›› የሚለውን በመሪና ‹‹ንሰብሖ ..›› ወናልዕል ስሞ የሚለውን በቅብብሎሽ ብለው በዚያው ቀጥለው፤ ‹‹ኪራያላይሶን፥ ኪራያላይሶን፥ ኪራያላይሶን›› የሚለውን በመሪ 21 ጊዜ፤ በተመሪ 20 ጊዜ (በድምሩ 41 ጊዜ) እየተሰገደ ይደርሳል፡፡
፠የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡
፠ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡
1.5K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-15 17:30:07 +እንዘ ሰለስቱ አሃዱ +

ግጥምና ዜማ :-ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
በዘማሪ:-ሊቀዲያቆን ወንደሰን በላይ

+እንዘ ሠለስቱ+

ዓለምን በጥበብ ለፈጠረ ጌታ
ዘወትር እናቅርብ የክብር ሰላምታ
መላእክት በፍርሃት ለሚያመሰግኑት
ለሥላሴ እናቅርብ አኮቴት ስብሐት

ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
እንዘ ሠለስቱ አሐዱ

በሃሳቡ ብቻ ዓለምን ለሠራ
በአምላካዊ ቃሉ ብርሃንን ላበራ
ሰውን በምሳሌው በአርኣያው ፈጥሮ
ከአፈር አበጀው ከሁሉ አክብሮ

ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
እንዘ ሠለስቱ አሐዱ

የሰው ልጅ ሲበድል አምላክ ልሁን ብሎ
የሰይጣንን ምክር አምኖ ተቀብሎ
አዳም አዳም ብሎ ፍለጋ ለወጣ
ለይቅር ባይ ጌታ ምስጋናን እናምጣ

ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
እንዘ ሠለስቱ አሐዱ

ወደ ዓለም ልኮ አብ አንድ ልጁን
ወልድም በፈቃዱ መጣ ሰው ሊሆን
በመንፈስ ቅዱስ ግብር ተጸንሶ ተወልዶ
አክሊል አቀዳጀን በመስቀል ተዋርዶ

ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
እንዘ ሠለስቱ አሐዱ

እንዴት ላመስግንህ የቅዱሳን አምላክ
በልቤ ጉልበትም ለአንተ ልንበርከክ
ዓይኔን ከእጄ ጋር ወደ ላይ አንሥቼ
እዘምርልሃለሁ እንደ አባቶቼ

ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
እንዘ ሠለስቱ አሐዱ

ዝማሬ : ሊቀ ዲያቆናት ወንድወሰን በላይ
ግጥምና ዜማ: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
3.5K viewsYordanos Gidey, 14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-06 12:31:17 +++ ይግባኝ! +++

አንድ ሰው ለብዙ ዘመናት አብሮት በፍቅር ይኖር የነበረ ወዳጁን በቅንዓት ተነሳስቶ ይገድለዋል፡፡ በዚህም የወንጀል ሥራው ተከስሶ የፍርድ ብይን ያገኝ ዘንድ ሰዎች ከችሎት ፊት አቆሙት፡፡ ዳኛውም ወንጀለኛው ለፈጸመው የጭካኔና ሰብአዊነት የጎደለው ክፉ ተግባር በሕጉ መሠረት የሚገባውን የዕድሜ ልክ እስራት ወሰኑበት፡፡ወንጀላኛውም በተሰጠው ፍርድ ፍትሐዊነት ላይ እንዳላመነበት እና ለፍርዱ ማቅለያ የሚሆን የይግባኝ ጥያቄን ማቅረብ እንደሚፈልግ በእጁ እየጠቀሰ ዳኛውን ተለማመነ፡፡

በዚህ ጊዜ ዳኛው ምን ዓይነት ይግባኝ እንደሚያቀርብ ለመስማት የጓጉ መሆናቸውን በሚያሳብቅ መልኩ ቸኩለው እድሉን ሰጡት፡፡

ወንጀለኛ፡-ክቡር ፍርድ ቤቱ እንዲመለከትልኝ የምፈልገው አንድ ነገር አለ፡፡በርግጥ ይህን ሰው መግደሌን አልካድኩም፣ ነገር ግን እርሱን ለመግደል የፈጀብኝ እኮ አፍታ ነች እንደው ቢበዛ ዐሥር ደቂቃ ቢሆን ነው፡፡ ታዲያ እንዴት በዚህች አጭር ጊዜ ላጠፋሁት ጥፋት ዕድሜ ልክ ይፈረድብኛል? በማለት ጥያቄውን አቀረበ፡፡

ዳኛው ምን ብለው የሚመልሱለት ይመስላችኋል? መቼም ወንጀሉን ለመፈጸም ከፈጀበት ጊዜ ጋር ተነጻጽሮ ፍርዱ ሊቀልለት ይችላል የሚል የየዋሕ ሰው ግምት እንደማይኖራችሁ አልጠራጠርም፡፡ በፍርዱ ሂደት የሚታየው ወንጀሉን ሲፈጽም የወሰደበት የጊዜ መጠን ሳይሆን በዚያች ሰዓት የፈጸማት የወንጀሏ ክብደት ናት፡፡

ውድ ምዕመናን! አሁን እኛ የፍርድ ቤት ዘገባ ምን ይጠቅመናል ትሉ ይሆናል? ከዚህ በኋላ ግን የምንነጋገረው ፍትሕ ስለማይገኝባት ስለዚህች ምድር ፍርድ አይደለም፤ ስለ ሰማያዊው ፍርድ ነው እንጂ። ስለ ሥጋዊው የዳኝነትም ሥርዓት አይደለም፤ ስለመንፈሳዊው ፍርድ ነው እንጂ፡፡ ብዙ ወንድሞቻችን እና እኅቶቻችን ስለ እግዚአብሔር ፍርድ ዘላለማዊነት (eternal punishment) ባሰቡ ቁጥር ‹የሰው ልጅ በዚህች ምድር የሚኖረው የዕድሜ ልክ ስልሳ እና ሰባ ቢበዛም ሰማንያ ነው፡፡ ታዲያ በዚህ የዕድሜ ወሰን ውስጥ ለተሠራ ኃጢአት እንዴት እግዚአብሔር ዘላለማዊ ፍርድን ይፈርዳል?› የሚል ጥያቄ በኅሊናቸው ይላወስባቸዋል፡፡

አንዳንዶቹም ለተገፉ ጠበቃ የሚሆን የእውነት ፈራጅ እግዚአብሔርን ፍርዱ ኢ-ፍትሐዊ (unfair judgment) ነው በማለት ይሞግታሉ፡፡ እነዚህ ወገኖች ምንም ስለ ‹ዘላለማዊ ሽልማቱ› (eternal reward) ‹ለምን ዘላለማዊ ሆነ?› የሚል ጥያቄን አለማቅረባቸው ትዝብት ውስጥ የሚጥላቸው ቢሆንም እነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ግን ከላይ ባለው አጭር ምሳሌ መልሳቸውን ያገኛሉ፡፡

አስተውሉ! ለወንጀለኛ መቼም ፍርድ እንደሚገባው ማንም የሚያምንበት ጉዳይ ነው፡፡ ወንጀለኛ ከወንጀል እስካልጸዳ ድረስ ፍርድ ከእርሱ ጋር እንደ ጥላ ትከተለዋለች፡፡ ቅጣትንም እንደ አክሊል በራሱ ላይ ደፍቶ ይመላለሳል፡፡ ለኃጢአተኛም እንዲሁ ነው፡፡ ራሱን በንስሓ መርምሮ ፣ወድቆ ተነሥቶ ፣በሥጋው በደሙ(ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል) አምላኩን እስካልታረቀ ድረስ ሁል ጊዜም ኃጢአተኛ ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ኀዘኑን እጥፍ የሚያደርገው ያ ኃጢአተኛ በዚህ አቋሙ እያለ በሞት ከተወሰደ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰው የሚድንበትን መንፈሳዊ ተግባር ማከናወን የሚችለው በምድር በሕይወተ ሥጋ እስካለ ድረስ ብቻ በመሆኑ ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ከራሷ ከክርስቶስ ከታነጸችበት የሐዋርያት ትምህርትም አላገኘችውምና ሰው ከሞተ በኋላ በሰማይ የሚሰግድበት ፣መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያደራጅበትና ኃጢአቱን የሚያስወግድበት ሥፍራ አለ ብላ አታምንም፡፡ ‹እም ድኅረ ሞቱ ለሰብእ አልቦቱ ንስሓ›/ ‹ለሰው ከሞቱ በኋላ ንስሓ የለውም› የሚለውን የአበው ቃል መመሪያዋ ታደርጋለች እንጂ፡፡

ስለዚህም በዚህ መልኩ የሞተ ሰው ኃጢአተኝነቱ ለዘላለም ነውና ፍርዱም ለዘላለም በማይጠፋ በዲንና በሚቃጠል የእሳት ባሕር ይሆናል፡፡ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው፡፡(ራእይ 21፤8) ከእንግዲህስ ከነኃጢአታችን ብንሞት የምንድንበት መሥዋዕት የለምና፣ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ አምላክ በዓይነ ምሕረቱ እንዲመለከተን የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደተባሉት ወደ ተሾሙ ካህናት እንገስግስ። ንስሓ እንግባ፣ ቀኖናችንንም እንፈጽም። መጠየቅን በሚወድ በእርሱ ፊት ለፍርድ በቆምን ጊዜ መልስ የሚሆነንን የጽድቅን ጥሪት እናከማች!

‹አቤቱ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ በደላችን አይሁንብን!›

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com

@dnabel
5.4K viewsYordanos Gidey, 09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-21 20:34:59
4.6K viewsYordanos Gidey, 17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ