Get Mystery Box with random crypto!

ሴራ ታሪክ እና ምርምር

የቴሌግራም ቻናል አርማ sera_tarik_mirmir — ሴራ ታሪክ እና ምርምር
የቴሌግራም ቻናል አርማ sera_tarik_mirmir — ሴራ ታሪክ እና ምርምር
የሰርጥ አድራሻ: @sera_tarik_mirmir
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.46K
የሰርጥ መግለጫ

የጥንት ኢትዮጵያ መንፈሳዊና አለማዊ ስራወች፥ ኢትዮጵያን ለማፈራረስ እና የአውሬውን መንፈስ በኢትዮጵያ ላይ ለማንፀባረቅ የሚሸረቡ ሴራወች እንዲሁም የኢትዮጵያና ሌሎች ታሪኮች አስተማሪና ጠቃሚ ምክሮችና መረጃወች ይቀርቡበታል
የዩቲዩብ ቻናላችንን subscribe አድርጉልን
https://youtube.com/channel/UCBtYnl_gnPkD_bpk3qwmRHA አስተያየት ለማድረስ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 19:34:05
subscribe YouTube chanal
170 viewsማኢጎ ጉቤ, 16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:51:39 https://youtube.com/channel/UCBtYnl_gnPkD_bpk3qwmRHA
283 viewsማኢጎ ጉቤ, 12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:29:07 ታንክና ኦራል ይዞ ሄዶ በቅጽበት አስረክቦ በከተማ ውስጥ የሚከራዩ የህጻናት ሳይክሎችን እየቀማ በሳይክል መፈርጠጥ ምን ይሉት ሚሊቴሪ ጌም ነው?
እንዲህ ያለ ነገር በዘራችሁ አይድረስ!
ቆይ ግን ስልጠናው ስለ ሽሽት አይነቶች ፈጥኖ ስለመፈርጠጥ ትጥቅን አስረክቦ ስለመመለስ ስለምናምን ነው እንዴ? በውነት ግራ ያጋባል!
ነገር ግን አብይ አህመድን እና ጋሻጃግሬዎቹን ለፍርድ ሊያቀርብ የሚመጣ ሃይል የተባረከ ብቻ ሳይሆን የተቀደሰም ጭምር ነው!
ሌላው በራስ ጦርነት ወይም በራስ ስምምነት ነገ ከነገወዲያ ይፈታል!
ለማንኛውም በፒኮክ ወፍ እና በአንበሳ መካከል የተካሄደና የሚካሄድ ጦርነት ብለን የገለጽነው ስንቀልድ አይደለም!እውነታው ያ ስለሆነ ብቻ ነው!

Join the telegram chanal

https://t.me/sera_tarik_mirmir
1.3K viewsማኢጎ ጉቤ, edited  12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 22:36:58 የሀገረ መከላከያ ሰራዊት በኦህዴድ እየተመራ፣ የአማራ ልዮ ኃይል ደግሞ በብአዴን እየተመራ አማራና ኢትዮጵያ ያሸንፋሉ ብሎ ማሰብ ከንቱነት ነው።

"በተለይም ፋኖ እና የአማራ ልዮ ኃይል በብአዴን ኦህዴድ መንፈስ አየተመራ እንኳንስ በመቶ ሺዎች የተመራ ጦርነት ቀርቶ የቡድን ፀብን ማሸነፍ አይታሰብም"።"
394 viewsኢትዮጵያ ትቅደም, edited  19:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 16:47:13 "አብይ አህመድ መቀሌ አይገባም። ደብረፂዮንም አዲስ አበባ አይሄድም። የሁለቱም እቅድ አማራን ማድቀቅ ነው። የአማራን አንገት በማስደፋት ኢትዮጵያን ለሁለት መቀራመት ነው።"

- ፓስተር ደረጀ ከበደ
join telegram

https://t.me/sera_tarik_mirmir
446 viewsማኢጎ ጉቤ, 13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 15:42:05 በአንድ ዘመን አጼ ቴዎድሮስ (የያንጊዜው ካሣ ኃይሉ) ሰራዊታቸው ሁሉ ኮስሶ ነበር። ግዛታቸው ቀንሶ ነበር። የድክመቱ መንስኤ አማቶቻቸው ራስ አሊ እና እቴጌ መነን የካሣ የመሳፍንትን የክፍፍል አገዛዝ አስወግዶ ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ ህልም ስለገባቸውና ሥልጣናቸውን እንዳያጡ በመስጋት ወዳጅ መስለው ስለጎዷቸው ነው።

በዚህ ወቅት በቋራ ግንባር ማለትም፥ በካሣ ኃይሉ ግዛት በኩል የውጭ ወራሪ መጣ። የኦቶማን ቱርኮች እገዛም ያለበት የግብፅ እና የሱዳን ወራሪ ሃይል ነበር። የወቅቱን ዘመናዊ የጦር መሳሪያ እስከ አፍንጫው ታጥቋል። ብዛቱ ለጉድ ነው። የካሣ ኃይሉ ጦር ትጥቁ በአብዛኛው ጎራዴ ሲሆን ቁጥሩም አነስተኛ ነበር። ጎንደር ላይ የተደላደለው የእነ እቴጌ መነን መንግሥት ብቻህን ተወጣው ብሎታል።

የካሣ ሰራዊት 'እንዝመት ወይስ አንዝመት' የሚል ግርታ ውስጥ ገባ። እሳቸው ግን ከቶ ግር አላላቸውም። የአማቶቻቸው ሴራ ሁሉ ቁልጭ ብሎ እየታያቸው፤ አባ ታጠቅ 'ሀገሬ ስትደፈር ቁጭ ብዬ አላይም። አጋዤ ከላይ ነው። ሲሆን ከፊቴ የሚቆም አይኖርም። ካልሆነም ለኢትዮጵያ ክብር እየተዋጋሁ እሰዋለሁ' አሉ። ፈረሳቸውን አስጭነው ዘመቱ። አፋፉን ሲወጡ የጠላት ጦር ከሩቅ ፈስሶ ይታያል። ብዛቱ አስፈሪ ቢመስልም ውጊያ እንደሚገጥም ሳይሆን ከመካከል አብሮ እንደሚሰለፍ ቀጥ ብለው በመሄድ ተጠጉት። በድፍረታቸው ግራ የተጋባው ጠላት መሳሪያዎቹን ወድሮ ባሰፈሰበት የቋራው ካሣ ድንገት ከፈረሳቸው ዘለው ጎራዴያቸውን ቀኝ እና ግራ እያገላበጡ ከመካከሉ ድንቡር አሉ። አንገት አንገቱን እየቀሉ ይጥሉት ጀመር። ከጎራዴ የተረፈ እጁ ከጠመንጃው ምላጭ ደርሶለት የተኮሰ ጠላት ቢኖር እንኳን፥ ከካሣ ሰራዊት ይልቅ ሳያውቀው እርስ በእርሱ ተከሻከሸ።

ድል የተገፋው ጀግና ሆነች። ካሣ ኢትዮጵያ በወቅቱ ፈፅሞ ያልነበራት ዘመናዊ የጦር መሳራያ ባለቤት ሆኑ። የእቴ መነን እና የራስ አሊ ሴራ ከሸፈ ብቻ ሳይሆን በተቃራኒው ሆነ። የካሣ ሰራዊት እየጨመረ፤ ግዛቱም እየሰፋ መጣ።

ዛሬ በፋኖ ላይ እየተፈጸመ ያለው ትናንት በአባ ታጠቅ ላይ ከተደረገው የተለየ አይደለም። ሰው የሚማረው ከኦና አይደለም፤ ከተሞክሮ ነው። የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮዎች ስንጠቅስ 'የፈረንጅ ምናምንቴ' የሚል አጣጣይ አይጠፋም። ሆኖም ትውልድ ከሌላ ሀገር ተሞክሮ ወይም ከታሪክ ይማር ዘንድ ግዴታው ነው።

የሀገርን ትርጉም እና የጨበጣ ውጊያን ከቴዎድሮስ ያልተማረ ከሌላ ለመማር የሚያዳግተው ይመስለኛል። ፋኖም ሆነ ከአገዛዙ ቅርጫት ውጭ ያሉ የጦር ሰዎች ከዚህ ሊማሩ ይገባል።

ድል ለፋኖ
join
https://t.me/sera_tarik_mirmir
2.1K viewsማኢጎ ጉቤ, edited  12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 14:22:52 ስለቆቦ ከተማ!

“እኔ ባለኝ መረጃ መሠረት የቆቦ ከተማና አካባቢው እስከ አሁኗ ስአት ድረስ በጠላት ቁጥጥር ስር ነው የሚገኘው። አንዳንድ ወገኖችና የማህበራዊ ሚዲያ ሰዎች የወገን ጦር ቆቦ ገብቷል በማለት የሚሰጡት መረጃ ትክክል አይደለም። ይህም ሆኖ የወገን ጦር በቆቦና አካባቢው እየወሰደው ባለው የተቀናጀ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ አማካኝነት ቆቦ ከተማ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ነጻ ሊወጣ እንደሚችል ይታመናል።”

- ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ እንደገለፀው!

“በቆቦ ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው ንፁኃን በሕወሓት ታጣቂዎች መገደላቸው ተሰማ!

በቆቦ ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው ንፁኃን በሕወሓት ታጣቂዎች መገደላቸውን በስፍራው የሚገኙ ምንጮች ገልፀዋል። እስካሁን የሟቾቹን አስከሬን ማንሳት እንዳልተቻለም የአይን እማኞቻችን አረጋግጠዋል።ቆቦ ከተማ እስካሁን በሕወሓት ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ስትሆን ነዋሪዎቿ መንቀሳቀስ እንዳልቻሉ ለአማራ ድምፅ አረጋግጠዋል። ታጣቂዎች ቤት ለቤት እየዞሩ በርካታ ንጹኃንን ፋኖ እና ሚሊሻ ናችሁ በሚል ጎዳና ላይ አውጥተው እንደረሸኗቸው የአይን እማኞቹ አረጋግጠዋል።”

- ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ እንደገለፀው

401 viewsማኢጎ ጉቤ, 11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:18:03 ያሳዝናል!
መንግስት ቆቦ ከተማን አስረክቦ መውጣቱን አምኗል!!

መንግስት ቆቦን ለመልቀቅ ያስቻለውን ምክንያት ሲገልጽ "የህዝብን ከፍተኛ እልቂት ለማስወገድ ሲባል የመከላከያ ኃይል ቆቦ ከተማን በመልቀቅ እና ወደ ኋላ መጥቶ ለመከላከል የሚያስችለውን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለመያዝ ... " የሚል ነው::

ይኸው እንግዲህ "ስልታዊ ማፈግፈግ" ስሟን ቀይራ መጥታልች!!
298 viewsማኢጎ ጉቤ, 17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:17:50
#ለምን_ይሆን_ካለፈ__ስህተታችን_መማር_ያቃተን

ቆቦ የሚገኘው ከ60 ሺህ በላይ የትግራይ ተፈናቃይ ቀድሞ ከተማዋን በከፊል ወረራ ፈፅሞባታል።ከካምፕ ወጥቶ በባዶ እጅ ተልዕኮውን እየፈፀመ ነው።

#ስትሄድ_ያናቀፈህ_ድንጋይ_ስትመለስ_ከደገመህ...
https://youtube.com/channel/UCBtYnl_gnPkD_bpk3qwmRHA
799 viewsማኢጎ ጉቤ, edited  17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:10:42 ሰበር!
የቴሌግራም ቻናሉን አሁኑኑ ሰብስክራይብ አድርጉት
https://t.me/sera_tarik_mirmir

ጀኔራል ተፈራ ማሞ ለሶስተኛ ጊዜ የአማራ ልዩ ኃይልን እንዲያማክሩ በአማራ ክልል ባለስልጣኖች ተደውሎ ቢጠየቁም ጀኔራሉ እረፍት ላይ ነኝ ብሏል። ጀኔራል ተፈራ ማሞ ጦርነት በመጣ ቁጥር እየተጠሩ ለህዝቡ ደጀን በመሆን ይታወቃሉ። በቆረጣ ውጊያ ሸማቂው ኮማንዶ ተፈራ ማሞ ጀግንነታቸው የታወቀ ነው።

ጀኔራል ተፈራ ግን አሁን እግሬ ላይ ህመም ስላለብኝ አሁን እረፍት ያስፈልገኛል ብሏል። ጀኔራል ተፈራ እና ኮሌኔል ቢሰጥ ጌታሁን በህልውና ዘመቻው ውለታቸው ተዘንግቶ ታስረው በቅርቡ ነበር የተፈቱት።ጀኔራል ተፈራ ማሞ በህመም ሲሰቃዩ ሊያሳክማቸው የሞከረ ህዝብም ሆነ መንግስት አነበረም። የወደቁበትንም የጠየቀ ማንም አነበረም።

ታጋዮቻችንን መጠበቅ፤ሲታመሙ ማሳከም፤ሲቸገሩ መርዳት ካልቻልን ተተኪ ታጋዮችን ማፍራት አንችልም!
ዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ አድርጉልን
https://youtube.com/channel/UCBtYnl_gnPkD_bpk3qwmRHA
1.2K viewsማኢጎ ጉቤ, edited  04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ