2022-08-29 15:42:05
በአንድ ዘመን አጼ ቴዎድሮስ (የያንጊዜው ካሣ ኃይሉ) ሰራዊታቸው ሁሉ ኮስሶ ነበር። ግዛታቸው ቀንሶ ነበር። የድክመቱ መንስኤ አማቶቻቸው ራስ አሊ እና እቴጌ መነን የካሣ የመሳፍንትን የክፍፍል አገዛዝ አስወግዶ ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ ህልም ስለገባቸውና ሥልጣናቸውን እንዳያጡ በመስጋት ወዳጅ መስለው ስለጎዷቸው ነው።
በዚህ ወቅት በቋራ ግንባር ማለትም፥ በካሣ ኃይሉ ግዛት በኩል የውጭ ወራሪ መጣ። የኦቶማን ቱርኮች እገዛም ያለበት የግብፅ እና የሱዳን ወራሪ ሃይል ነበር። የወቅቱን ዘመናዊ የጦር መሳሪያ እስከ አፍንጫው ታጥቋል። ብዛቱ ለጉድ ነው። የካሣ ኃይሉ ጦር ትጥቁ በአብዛኛው ጎራዴ ሲሆን ቁጥሩም አነስተኛ ነበር። ጎንደር ላይ የተደላደለው የእነ እቴጌ መነን መንግሥት ብቻህን ተወጣው ብሎታል።
የካሣ ሰራዊት 'እንዝመት ወይስ አንዝመት' የሚል ግርታ ውስጥ ገባ። እሳቸው ግን ከቶ ግር አላላቸውም። የአማቶቻቸው ሴራ ሁሉ ቁልጭ ብሎ እየታያቸው፤ አባ ታጠቅ 'ሀገሬ ስትደፈር ቁጭ ብዬ አላይም። አጋዤ ከላይ ነው። ሲሆን ከፊቴ የሚቆም አይኖርም። ካልሆነም ለኢትዮጵያ ክብር እየተዋጋሁ እሰዋለሁ' አሉ። ፈረሳቸውን አስጭነው ዘመቱ። አፋፉን ሲወጡ የጠላት ጦር ከሩቅ ፈስሶ ይታያል። ብዛቱ አስፈሪ ቢመስልም ውጊያ እንደሚገጥም ሳይሆን ከመካከል አብሮ እንደሚሰለፍ ቀጥ ብለው በመሄድ ተጠጉት። በድፍረታቸው ግራ የተጋባው ጠላት መሳሪያዎቹን ወድሮ ባሰፈሰበት የቋራው ካሣ ድንገት ከፈረሳቸው ዘለው ጎራዴያቸውን ቀኝ እና ግራ እያገላበጡ ከመካከሉ ድንቡር አሉ። አንገት አንገቱን እየቀሉ ይጥሉት ጀመር። ከጎራዴ የተረፈ እጁ ከጠመንጃው ምላጭ ደርሶለት የተኮሰ ጠላት ቢኖር እንኳን፥ ከካሣ ሰራዊት ይልቅ ሳያውቀው እርስ በእርሱ ተከሻከሸ።
ድል የተገፋው ጀግና ሆነች። ካሣ ኢትዮጵያ በወቅቱ ፈፅሞ ያልነበራት ዘመናዊ የጦር መሳራያ ባለቤት ሆኑ። የእቴ መነን እና የራስ አሊ ሴራ ከሸፈ ብቻ ሳይሆን በተቃራኒው ሆነ። የካሣ ሰራዊት እየጨመረ፤ ግዛቱም እየሰፋ መጣ።
ዛሬ በፋኖ ላይ እየተፈጸመ ያለው ትናንት በአባ ታጠቅ ላይ ከተደረገው የተለየ አይደለም። ሰው የሚማረው ከኦና አይደለም፤ ከተሞክሮ ነው። የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮዎች ስንጠቅስ 'የፈረንጅ ምናምንቴ' የሚል አጣጣይ አይጠፋም። ሆኖም ትውልድ ከሌላ ሀገር ተሞክሮ ወይም ከታሪክ ይማር ዘንድ ግዴታው ነው።
የሀገርን ትርጉም እና የጨበጣ ውጊያን ከቴዎድሮስ ያልተማረ ከሌላ ለመማር የሚያዳግተው ይመስለኛል። ፋኖም ሆነ ከአገዛዙ ቅርጫት ውጭ ያሉ የጦር ሰዎች ከዚህ ሊማሩ ይገባል።
ድል ለፋኖ
join
https://t.me/sera_tarik_mirmir
2.1K viewsማኢጎ ጉቤ, edited 12:42