Get Mystery Box with random crypto!

Asham TV

የቴሌግራም ቻናል አርማ asham_tv — Asham TV A
የቴሌግራም ቻናል አርማ asham_tv — Asham TV
የሰርጥ አድራሻ: @asham_tv
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.58K
የሰርጥ መግለጫ

Asham Tv is a privately owned media company, based in Addis Ababa, Ethiopia, that provides news, Analysis, information and other programs.

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-14 13:47:54
701 views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 12:09:19
667 views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 11:36:31
613 views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 11:16:44
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር < የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት "ጤናማ" ነው> አለ።

አሻም ዜና |ሐምሌ 7፣ 2014 ዓ.ም

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ዛሬ ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም በፅ/ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት "መልካም" መሆኑን የተናገሩት።

ቃል አቀባዩ ይህን ማብራሪያ የሰጡት "የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና ሶማሊያ የእርስ በእርስ ግንኙነት" አስመልክቶ ከአሻም ለተነሳላቸው ጥያቄ ነው።

እንደ ቃል አቀባዩ ከሆነ "ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር ያላት ግንኙነትም በተመሳሳይ "መልካም" መሆኑን" ጠቁመዋል።

በጋዜጣዊ መግለጫው "መንግስት በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ከዛሬ(ሐምሌ7) ጀምሮ፣ ከስምንት ሀገራት 12ሺህ ዜጎችን ወደሀገር ቤት የመመለስ ስራ እንደሚጀመር" ተገልፆል።

አምባሳደር መለስ ዓለም የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያና ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።

ዮሐንስ አሰፋ

[በምሽቱ የዜና ሰዓታችን መግለጫውን በዝርዝር እንድትከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።]
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asha
669 views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 17:33:43
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጋራ መኖሪያ ቤቶች የወጣውን ዕጣ ውድቅ ማድረጉን አስታወቀ ፡፡

አሻም ዜና |ሐምሌ 6፣ 2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ ባሳለፍነው ሐምሌ 1 ቀን 2014 የወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውድቅ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ዕጣው የተሰረዘውም የከተማ አስተዳደሩ ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓቱ በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ሲጀመር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነት መኖሩ በመረጋገጡ ነው ተብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 01 ቀን 2014 በወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር ድርጊት በመከሰቱ ሁኔታውን እያጣራ እንደሚገኝ እና በድርጊቱ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር እያዋለ መሆኑን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asha
966 views14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 14:25:47
የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ከ0.50 ሳንቲም እስከ 6 ብር ጭማሪ ማድረጉን ገለጸ።

አሻም ዜና |ሐምሌ 6፣ 2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ከነገ ጀመሮ ተግባራዊ የሚደረግ የታሪፍ ማሻሻያ መደረጉን አስታውቋል።

የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ለውጥን ብቻ መሰረት በማድረግ በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ የሚዲ-ባሶች እና የሚኒ-ባስ ታክሲዎች የአገልግሎት ታሪፍ ማስተካከያ ከነገ ሐምሌ 7/2014 ዓ.ም ጀምሮ ከ0.50 ሳንቲም እስከ 6 ብር ጭማሪ ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮው አስታውቋል።

በዚህም በሚዲ-ባስ 0.50 ሳንቲም እስከ 2.00 ብር የተጨመረ ሲሆን በሚኒ-ባስ 0.50 እስከ 6 ብር ተጨምሯል ተብሏል።
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asha
900 views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 11:36:43
1.0K views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 15:29:15
በጭጋጋማ የአየር ፀባይ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የአውሮፕላን በረራ በአብዛኛው መጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ፡፡

አሻም ዜና |ሐምሌ 4፣ 2014 ዓ.ም

በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በተከሰተው ጭጋጋማ የአየር ጸባይ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የአውሮፕላን በረራ በአብዛኛው መጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ ባለፉት ጥቂት ሰአታት በአዲስ አበባ የነበረው ጭጋጋማ የአየር ፀባይ መሻሻል ማሳየቱን ጠቁሟል።

ከዚህ ጋር ተያይዞም ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉና ከኢትዮጵያ የሚነሱ በረራዎች በአብዛኛው መጀመራቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው የበረራ መዘግየትና መስተጓጎል ይቅርታ የጠየቀና ለደንበኞቹ ስለሁኔታው ተጨማሪ መረጃዎች ማድረሱን እንደሚቀጥልም ገልጿል።
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asha
1.3K views12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 10:22:35
በጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት በአውሮፕላን በረራዎች ላይ መስተጓጎል መፈጠሩን አየር መንገዱ ገለፀ

አሻም ዜና |ሐምሌ 4፣ 2014 ዓ.ም

በአዲስ አበባ በተፈጠረው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት ከአዲስ አበባ በሚነሱና አዲስ አበባ በሚያርፉ በረራዎች ላይ መዘግየት መፈጠሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው የበረራ መዘግየትና መስተጓጎል ይቅርታ ጠይቋል፡፡

ደንበኞችም የተፈጠረውን ችግር ተገንዝበው አየር መንገዱ ስለሁኔታው የሚያቀርበውን መረጃ እንዲከታተሉ መጠየቁን የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል፡፡

አዲስ አበባ ዛሬ በዝናብና ጭጋጋማ አየር ተሸፍናለች።
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asha
1.2K views07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 11:20:59 ሦስት ፓርቲዎች " በመጪው ሰኞ መላው ኢትዮጵያዊያን ጥቁር ልብስ በመልበስ ለተጨፈጨፉ ዜጎች ሀዘናቸውን እንዲገልፁ ጥሪ አቀረቡ።"

አሻም ዜና |ሐምሌ 1፣ 2014 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ(ኢህአፓ)፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) እና እናት ፓርቲ ሐምሌ 1 ቀን 2014 ዓ.ም በጋራ በሰጡት መግለጫ ላይ ነው ጥሪውን ያቀረቡት።

"ጥቁር ከመልበስ በተጨማሪ፣ በዕለቱ ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም፣ ከቀኑ 6:30 የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት እንዲደረግ" ጥሪ አቅርበዋል።

ፓርቲዎቹ " መንግስት፣ የጭፍጨፋ መደላድሎችንና የማዘናጊያ መግለጫዎችን በማውጣት ለዘር ፍጅቱ የማይናቅ አስተዋፅዖ አድርጓል።" ሲሉ ወንጅለዋል።

የጋራ መግለጫውን በንባብ ያቀረቡት የእናት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ያየህ አስማረ" አሸባሪ እያሉ የጠሩት ኦነግ ሸኔ ወደሀገር ቤት አገባቡ ጀምሮ የተሠሩ መንግስታዊ ስህተቶች ጥርጥር ባይኖርም አንድ እግሩን አዲስ አበባ፣ አንድ እግሩን ምዕራብ ኦሮሚያ ጫካዎች ውስጥ ከተከለ በኋላም በከፍተኛ ሁኔታ መንግስታዊ መዋቅርና ማዘናጊያዎችን እንደሚጠቀም" ማሳያዎችን መጥቀስ ይችላል ብለዋል።

"ከሁሉም የሚያሳዝነው ሽብር ቡድኑ ላይ የማያዳግም እርምጃ ወስጃለሁ፤ በቡድኑ የተያዘ አንድም አካባቢ የለም" የሚሉትን "በሚዘወራቸው መገናኛ ብዙሃን በማስተጋባት የጭፍጨፋ መደላድሎችንና የማዘናጊያ መግለጫዎችን በማውጣት የዘር ፍጅቱ እንዳይወገዝ፣ ዓለምአቀፉ ማህበረሰቡ ትኩረት እንዳይደረግበት ለፍጅቱ የማይናቅ አስተዋፅዖ አድርጓል።" ሲሉ ከስሰዋል።

(በምሽቱ የዜና ሰዓታችን የፓርቲዎቹን መግለጫ በዝርዝር እንድትከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን)

ዮሐንስ አሰፋ
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asha
1.9K views08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ