2022-06-05 01:54:33
የመጅሊስ ሒደት ላይ አጭር ማብራሪያ
✦•✦•✦
ክፍል አንድ
---
[1]. ከተለያዩ ወገኖች የተውጣጡ 9 አባላት ያሉት "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ" ኮሚቴ በጠ/ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ ተቋቋመ። ይህ ኮሚቴ 3ት አባላቱ የአህሉ ሱንናውን መስመር ወክለው ሲሆን 3ቱ ደግሞ ከወሃቢያ/ሰለፊ መስመር ነበሩ። የተቀሩት 3 አባላት ደግሞ "ገለልተኛ" ምሁራን ነበሩ።
---
[2]. መጀመሪያ ላይ የኮሚቴው ሚና መጅሊሱን በአዲስ መልክ ለማደራጀት የሚያስፈልጉ ሰነዶችን ማዘጋጀት የነበረ ቢሆንም በሂደት ግን ነባሩን መጅሊስ አመራር ስልጣን አንዲያስረክብ የማግባባት ስራና ጊዜያዊ መጅሊስ አመራር የማዋቀር ስራን ሰርቷል።
---
[3]. ኮሚቴው "የኢትዮጵያ ዐሊሞች የአንድነት እና የትብብር ሠነድ" እና "የመጅሊስ መተዳደሪያ ደንብ" የሚባሉ ሁለት ረቂቅ ሰነዶችን አዘጋጀ። መተዳደሪያ ደንቡን በተመለከተ 9ኙም ኮሚቴ አባላት (ሙፍቲን ጨምሮ) መስማማታቸውን በፊርማቸው ያረጋገጡት ቢሆንም በአማርኛ እና አረብኛ የተዘጋጀው 31 አንቀጾች ያሉት "የዑለሞች የአንድነት እና የትብብር ሠነድ" የሚባለውን ግን ከ9ኙ ኮሚቴ ውስጥ ሙፍቲን ጨምሮ ሶስት ግለሰቦች ብቻ ተስማምተው የፈረሙበት ሲሆን በተቃራኒው አንድም የወሃቢያ/ሰለፊ ተወካይ ሠነዱ ላይ አልፈረሙም። በመሆኑም በሸራተን ጉባዔ የተነበበው ይህ አዘጋጆቹ እንኳን ያልተስማሙበት ሠነድ ነው።
---
[4]. በዑለሞች መካከል በዐቂዳ መስመሮች፤ በመውሊድ እና ተሰውፍ ዙሪያ ዑለማ ሰነዱ ላይ እንዴት መግባት እንዳለባቸው በተፈጠረ አለመግባባት ከሚከተሉት አማራጮች ይበልጥ ገላጭ የሆኑትን ማስቀመጥ ይቻል ዘንድ መነሻ እንዲሆን በሚል ሶስት አማራጭ አንቀፆችን ያቀረበ ሲሆን የዘርፉ ዑለሞች አንዲወስኑበት የተተወ ነበር።
---
[5]. "አንድነት" በሚል ሲንቀሳቀስ የነበረው ወሃቢያ/ሰለፊ ቡድን ይህንኑ ፍላጎቱን በዑለሞች መግባቢያ ሠነድ ላይ እንዲያረጋግጥ ሲጠየቅ፤ የሚያለያዩን ጉዳዮች ተራ እና ጥቃቅን ጉዳዮች በመሆናቸው በዑለማ ሰነዱ መጠቀስ የለባቸውም እያለ ሲያጣጣል ሌላኛው ወገን ደግሞ ለኔ ወሳኝ ናቸው ሰነዱ በኡለሞች መካከል የሚፈረም እስከሆነ ድረስ በዚህ ጉዳይ ሳንስማማ እና ሳንፈራረም "አንድ ነን" ብለን መንቀሳቀስ የውሸት ነው፤ ጉዳዮቹ ላንተ ተራ ከሆኑ ተቀበልና በፊርማህ አረጋግጥ የሚል ጥያቄ አንስቷል።
---
[6]. በሌላ በኩል 9ኙ ኮሚቴ ያዘጋጀው መተዳደሪያ ደንብም ቢሆን የአህሉ ሰንናው ወገን ያሉ በርከት ያሉ ምሁራን እና ዑለሞች ትችት እና ተቋውሞ ያጋጠመው በመሆኑ፤ መጅሊሱን በአዲስ እና ሁሉንም ያሳተፈ እንዲሆን የተወጠነው ሀሳብ እንቅፋት ገጠመው።
---
[7]. የመተዳደሪያ ደንቡ ዋነኛ ችግሮች ተብለው በወቅቱ የተጠቀሱት፤
---
➥ መጅሊሱን ከእምነቱ በተጸጻሪነት እና የቀደምት ስርዓትን ፈለግ በመከተል በብሄር ለማዋቀር መሞከሩ፤
---
➥ የእምነት ተቋም ሆኖ እያለ የኃይማኖቱን መሪዎች ተራው ህዝብ እንዲመርጥ የሚፈቅድ በመሆኑ፤ የእምነት ተቋሙ የበላይ መሪ ዑለማ ብቻ መሆን ሲገባው ዑለማን እና ምሁራን መካከል ያለውን የስልጣን ኃላፊነት ስህተት መሆኑ ግልጽ አለማድረጉ ወይም አሰራር መዘርጋቱ፤
---
➥ ተቋሙ ዋና ግቡ በዋነኛነት የምእመኑን መንፈሳዊ ሕይወት ማጠናከር እና ማሳደግ ሆኖ ሳለ፤ ለዚህ ግብ መሳክት አስፈላጊ የሆኑ ተጓዳኝ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግልጋሎቶቹን በሚወጣበት መልኩ ማደራጀት አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ ቢሆንም፤ የተዘጋጀው ሰነድ ግን መንፈሳዊ ሚናውን የሚያኮስስ እና ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግልጋሎት ላይ አላስፈላጊ ትኩረት የሚሰጥ በመሆኑ፤
---
➥ የመንግስት አስፈጻሚ መስሪያ ቤት የሚመስል መዋቅር መከተሉ፤
---
➥ ላለፉት 1400 አመታት የዘለቀውን የሀገራችንን ሙስሊሞች እና እስልምና ትውፊቶች እና ባህል የሚያኮስስ እና ከነጭራሹም አውቅና የሚነፍግ አደረጃጀት መሆኑ፤
---
[8]. በሌላ በኩል ከመጀመሪያውኑ የአንድነት ውጥኑ የይስሙላ ነው፤ እውነተኛ አንድነት እንዲመጣ ከተፈለገ በአንድ ተቋም መሰባሰብ ብቻ አንድነት አያመጣም፤ ከዚህ ይልቅ አሉ የሚባሉት ልዩነቶች ከኃይማኖቱ የመነጩ ሳይሆን በጊዜ ሂደት ከእውቀት እና ግንዛቤ ማነስ፤ እና ሌሎችም ውጫዊ ምክንያቶች የተፈጠሩ በመሆናቸው፤ የአትዮጵያ ሙስሊም ይሁን የዓለም ሙስሊም ላለፉት 1400 አመታት በአንድ ዓይነት ኃይማኖታዊ አስተሳሰብ የመጣ በመሆኑ፤ አሉ በሚባሉ ልዩነቶችን ዙሪያ በቅድሚያ የሀይማኖቱ ምሁራን ተሰባስበው ውይይት እና ምክክር እንናድርግበትና ይህንኑ ይቀመጥ የሚል መጠይቅም ነበር።
---
[9]. ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ መጀመሪያ ላይ ከሁለቱም ወገኖች የተውጣጡ 4 ለ 4 የዐሊሞች ውይይት ተጀምሮ የነበረ ቢሆንም አንደኛው ወገን ውይይቱ ከፍ ባለ ታዳሚያን እና በዛ ያሉ ምሁራንን አካቶ እንዲደረግ ቢጠይቅም ሌላኛው የወሃቢያ ወገን በውይይቱ ለመቀጠል ፍቃደኛ ባለመሆኑ ሂደቱ በአጭር ተቋጨ።
---
[10]. በወቅቱ የተፈጠረውን የፖለቲካ አለመረጋጋት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም አንደኛው ቡድን ህዝብ ወደ ማነሳሳት እንቅስቃሴ በመጀመሩ መንግስት ጣልቃ በመግባት ሚያዝያ 23 ቀን 2011 የሸራተን ጉባዔ አንዲዘጋጅ ተደረገ።
---
[11]. በዚሁ መሰረት በወቅቱ የነበሩት ነባሩ መጅሊስ አመራር አባላት ስልጣናቸውን በፍቃደኝነት እንዲለቁ መንግስት በማግባባቱ እና ጫና በማድረጉ የቀድሞው አመራር አባላት ስልጣናቸውን በ9ኙ ኮሚቴ ለተመረጡ 26 ዑለሞች እና 7 የስራ አመራር ቦርድ አባላት አስረከቡ።
---
[12]. 26 አባላት ዑለማ ም/ቤት እና መጅሊሱ የሚመራው 11 አባላት ባሉት ዑለማ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሲሆን የስራ አመራር ቦርዱ ደግሞ በ7 አባላት የተወከለ ነበር።
---
[13]. ሸራተን ጉባዔ በአጠቃላይ ፖለቲካዊ የነበረ ሲሆን የጉባዔውም አጀንዳ ሠነድ ማጽደቅ ሳይሆን የአንድነት ጉዞ ጅማሪውን ማብሰሪያ እና ጊዜያዊ መጅሊስ ስራ አስፈጻሚ ማስተዋወቂያ ነበር። ነገር ግን፤ ሸራተኑ ስብሰባ ላይ 9ኙ ያልተስማማበት ረቂቅ ኡለማ ሠነዱ በግርድፉ ተነቧል።
---
[14]. በሸራተኑ ጉባዔ ላይ የመጅሊሱ አመራር የተቀየረ ቢሆንም ስለ ነባሩ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባዔው እጣ ፈንታ ምንም የተባለ ነገር አልነበረም። የዚህ ነባሩ መጅሊስ ጠቅላላ ጉባዔው እጣ ፈንታ በህግ አግባብ እንዴት ነው የሚለው ወደፊት የሚታይ ጉዳይ ነው።
---
[15]. አዲሱ አመራር ዋነኛ ተግባሩ ሁለቱን ሠነዶች (ማለትም የዑለማ መግባቢያ ሠነዱን እና የመተዳደሪያ ደንቡን) በባለድርሻ አካላት ውይይት ማዳበርና (በሌላ አካል) ማስጸደቅ ሆኖ በተጓዳኝም የመጅሊሱን የዕለት ተዕለት ተግባር እና ሌሎች ስራዎችን በጊዜያዊነት አንዲያከናውን ነበር። በመሆኑም በሸራተን የተቋቋመው ኮሚቴ ወይም ጉባዔ 26 አባላት ያሉት የዑለማ ም/ቤት እና ተጠሪነቱ ለዚሁ ም/ቤት የሆነ 7 አባላት ያሉት ስራ አመራር ቦርድ ነበር እንጂ 33 አባላት ያሉት ጉባዔ አልነበረም።
---
[16]. የ26ቱ ኡለማ አባላት 13ቱ ራሱን ወሃቢያ/ሰለፊ ብሎ ከሚጠራው ቡድን የተወከለ ሲሆን 13ቱ ደግሞ ዋና ሰብሳቢውን የመጅሊሱን ፕሬዝዳንት ሙፍቲን ጨምሮ ከነባሩ ሱኒ እስልምና የተወከሉ ነበሩ፡፡ ነባሩ/ሱኒ እስልምና ማለት የዛሬ 1400 በፊት ወደ ኢትዮጵያ የመጣውንና ከጥንት አመታት ጀምሮ በሀገራችንም ይሁን በአለም ላይ ሲተገበር የነበረውና በኃይማኖታዊ ቴክኒክ ቋንቋ አህሉ-ሱንናህ ወልጀመዓ መስመር የሚባለው እስልምና ሲሆን ራሱን ሰለፊያ ብሎ የሚጠራው ወሀቢያ ቡድን ደግሞ አለም ላይ
417 views22:54