Get Mystery Box with random crypto!

Ahmedin Jebel - አሕመዲን ጀበል

የሰርጥ አድራሻ: @ahmedin99
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 60.21K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ይፋዊ የአሕመዲን ጀበል የቴሌግራም ገፅ ነው!

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 39

2022-11-24 20:31:58 "የአላህን ፀጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም።" ቁርዓን

ከእነዚህ የአላህ ፀጋዎች መካከል አምስቱ የስሜት ህዋሳቶቻችን ናቸው።በእነዚህ የስሜት ህዋሳቶቻችን ብዙ ነገሮችን ማድረግ እንችላለን።የአላህን ተዕምራቶችን ማስተንተን፣ለዱንያና ለአኼራችን የሚጠቅሙንን ነገሮች መስራት ከብዙ ጥቂት ጥቅሞቹ ናቸው።እነዚህ የስሜት ህዋሳቶች ያለምንም ችግር መጠቀም የቻለ በእርግጥም አላህ በእርሱ ላይ ትልቅ ኒዕማ እንደዋለለት ሊገነዘብ ይገባል።

አንድ ሰው ወደ አንድ አሊም መጣና፦" እኔ በጣም ድሀ ነኝ።የአላህ ኒዕማ(ሀብት) ርቆኛል።እናም ይህ በመሆኑ ብስጩ ሆኛለሁ።ምን ይሻለኛል?" ብሎ ጠየቃቸው።

አሊሙም፦" አላህ ሁለቱን ዓይኖችህን ወስዶ አንድ መቶ ሺህ ዲናር ቢሰጥህ ፈቃደኛ ነህን? እረ አይደለሁም።እሺ! ሁለቱ መስሚያ ጆሮዎችን ወስዶ ሌላ አንድ መቶ ሺህ ዲናር ቢሰጥህ ፈቃደኛ ነህን? እረ በፍፁም።እሺ! ሁለቱን እጆችህንስ ወስዶ አንድ መቶ ሺህ ዲናር ቢሰጥህስ? እረ በፍፁም።እንግዲው በትንሹ አሁን እንኳን ለአንተ ከሶስት መቶ ሺህ ዲናር በላይ ዋጋ ያላቸውን ኒዕማዎች አላህ ሰጥቶሃልና አመስግነው።" አሉት።

ከዚህ በመነሳት የማየት ወይም የመስማት ችግር ያለባቸውን ወንድምና እህቶቻችንን ስናይ አላህ በእኛ ላይ የዋለውን ውለታ በማስታወስ ሹክር ልናደርግ ይገባል።ሹክር ደግሞ በቃል እንደሚገለፀው ሁሉ በተግባርም ይገለፃል። ስለዚህ መስማት የተሳናቸውን ወንድምና እህቶቻችንን ለመርዳት፣ቁርአን ለማስቀራት የተቋቋመ ኢማን የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ልማት ድርጅት የተባለ አገር በቀል ድርጅት በየካቲት 18/2014 ዓል የተቋቋመ ሲሆን ይህን ድርጅት አቅም በፈቀደ መጠን ከጎኑ መቆም የሁላችንም ሃላፊነት ነው።ስለሆነም በገንዘብ ለመርዳት የሚፈልግ ከታች ባሉት አካውንቶች በመጠቀም ድጋፍ እንድታደርጉ አንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት
1000461347936
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

ሒጅራ ባንክ
1002450020001
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

ዘምዘም ባንክ
0009389910301
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGAN
2.6K views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-21 18:05:48
የሂጅራ ባንክ ከፍተኛ አመራሮች በአቡ ዳቢ ከተማ

የሂጅራ ባንክ የቦርድ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የሸሪዓ አማካሪ ቦርድና የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በአቡ ዳቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ጋር ውይይት አካሂደናል::

ቀጣይ ህዳር 13 በዱባይ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት ከቀኑ 4:00PM በዱባይ እና አካባቢዋ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት ይኖረናል:: ሁላችሁም ተጋብዛቹኃል
2.4K views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-20 20:44:06
የዛሬው የኳታር አለም ዋንጫ መክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ የተነበበው የቁርዓን አንቀፅ ትርጉም ይህ ነበር..

«እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ከእናንተ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡»
(ቁርኣን 49÷13)

ከዚህ በተጨማሪ ኳታር ጨዋታውን ለመመልከትና ለመጫወት ለመጡ እንግዶቿ ...

በየሆቴሉ ክፍሎቹ ላይ የእስልምናን አስተምህሮ የሚያስተምሩና የሙስሊሞችን እምነት በቀላሉ የሚያብራሩ ሓዲሶች፣ መፃፅፎችና ቁርአናዊ መልእክቶችን ያቀፈ ባርኮድ ተያይዟል።

የአለም ዋንጫ ጨዋታው የሚካሄድባቸው 8 ስታዲየሞች መጠጥ ይዞ መግባት ተከልክሏል።

የመስጅድ ሙኣዚኖች ድምጸ መርዋ በሆኑ አዳዲስ ሙአዚኖች ተተክተዋል።በየስታዲየሞቹ አዛን እንዲሰማ የድምፅ ማጉያዎች ተተክለዋል።

የኳታር የእንግዳ ተቀባይ ሴንተሮች 10 ተንቀሳቃሽ መኪናዎችንና 10 ልዩ ድንኳኖችን በመትከል ወደ እስልምና የሚጣሩ ከ 2000 በላይ አስተማሪዎችን መድበዋል።

የኳታር የአውቃፍ ሚኒስተር በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ ኢስላማዊ አውደ ርዕዮችን ለጎብኝዎች አዘጋጅቷል።

በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በስቴዲየም ውስጥ የሶላት መስገጃ ቦታዎች ተሰናድተዋል።

የእስልምናን ውበት የሚያስተዋውቁ የነብዩ (ሰዐወ) ሀዲሶች በየቦታው ተለጥፈዋል።
7.1K viewsedited  17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 23:05:36
11.3K views20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 22:23:44
ኡስታዝ አቡሀይደር(ሳዲቅ መሀመድ) መኪናውን ተረክቧል።

ለድርጅቱ ማቋቋሚያ የተሰበሰበው ገንዘብም 12 ሚሊዮን 800ሺህ ብር ደርሷል።

Ustaaz Abu Haydar(Saadiiq Mohammed) konkolaataan harka isaa galeera. Qarshiin dhabbata daw'aa isaatiif walitti qabamees miliyoona 12 fi kumma 800 gaheera.
11.9K views19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 14:49:30
የትብብር ጥያቄ

270,000 ብር ብቻ

''እኛ መስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ዙርያ የምንሰራ ኢማን የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ልማት ድርጅት እንባላለን። ከማህበራት ማደራጃ ፍቃድ ያለን ህጋዊ ተቋም ነን።

ህዳር 19 ላይ አለም አቀፍ የመስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ኮንፈረንስ ጋምቢያ ላይ እንድንሳተፍ የጥሪ ደብዳቤ ተልኮልናለን። ስብሰባው ለመላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም መስማት የተሳናው ይጠቅማል ብለንም እናምናለን። ግን አሁን እኛ የደርሶ መልስ የአየር ጉዞ ቲኬት ለመክፈል አቅሙ የለንም። የምንሄደው 3 ሰዎች ነን።

ለያንዳንዳችን ከ80 እስከ 90ሺህ ብር ወይም ለ3ታችን 270ሺህ ብር ገደማ ይጠበቅብናል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የትብብር ደብዳቤ ፅፎልናል። እባካችሁ በኮንፈረንሱ ላይ እንድንሳተፍ ለአላህ ብላቹ ተባበሩን ይላሉ'' መልዕክታቸው።

ሁላችንም ብንተባበራቸው ቀላል ገንዘብ ናት። መስማት የተሳናቸውን፣ አይነ ስውራንን የመሳሰሉ ወገኖቻችንን በእምነታቸው እንዲጠነክሩ ማገዝ የሁላችንም ግዴታ ነው።

ከታች ባሉ አካውንቶች ድጋፍ በማድረግ እናግዛቸው።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት
1000461347936
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

ሒጅራ ባንክ
1002450020001
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

ዘምዘም ባንክ
0009389910301
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGAN
13.5K views11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 21:02:30
11 ሚሊየን 740ሺህ ብር

ለኡስታዝ አቡ ሀይደር ተቋም ምስረታ የተጀመረው የገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ ላይ በርካቶች የአቅማቸውን ድጋፍ በማድረግ አሻራቸውን ማኖር የቻሉ ሲሆን እስካሁን ለመኪና ግዢ ከተሰበሰበው ገንዘብ በተጨማሪ ለተቋም ምስረታው ብቻ 11,740,000 (አስራ አንድ ሚሊየን ሰባት መቶ አርባ ሺህ) ብር መሰብሰብ ተችሏል። አላሁ አክበር!

በዚህ መልካም ስራ ላይ የተሳተፋችሁና አሻራችሁን ያኖራችሁ በሙሉ አላህ መልካም ስራችሁን ይቀበላችሁ።



አካውንት ስም = Maqaan akkaawuunti:
SADIK MOHAMMED AHMED

1) የሂጅራ ባንክ አካውንት ቁጥር: Kan baanki hijraa: - 1001162290001

2) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ/Baanki daldala Itiyoopiyaa(COMMERCIAL BANK OF ETHIOPIA): - 1000329226712

3) አቢሲኒያ ባንክ(Baanki Abisiyaa)
83047178

4) አዋሽ ባንክ (Baanki Awaash):
01425212425200

5) ዘምዘም ባንክ 0014688820101

6 ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ
1011300008645

7 OROMIA INTERNATIONAL BANK
1330004700001
7.0K views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 13:22:39
ተቋሙ እውን እንዲሆን ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖቻችንም አሻራቸውን እያኖሩ ነው

የኡስታዝ አቡ ሀይደር ተቋም እውን እንዲሆን ሔለን ደመቀ የተባለች ሙስሊም ያልሆነች እህታችንና አብዮት በላቸው የተሰኘ ሙስሊም ያልሆነ ወንድማችን የ1000 ብር ድጋፍ በተናጠል በማድረግ አሻራቸውን አኑረዋል።



አካውንት ስም = Maqaan akkaawuunti:
SADIK MOHAMMED AHMED

1) የሂጅራ ባንክ አካውንት ቁጥር: Kan baanki hijraa: - 1001162290001

2) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ/Baanki daldala Itiyoopiyaa(COMMERCIAL BANK OF ETHIOPIA): - 1000329226712

3) አቢሲኒያ ባንክ(Baanki Abisiyaa)
83047178

4) አዋሽ ባንክ (Baanki Awaash):
01425212425200

5) ዘምዘም ባንክ 0014688820101

6 ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ
1011300008645

7 OROMIA INTERNATIONAL BANK
1330004700001
3.2K views10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-10 21:15:35
እንግሊዝ

በእንግሊዝ ሀገር የሚኖሩ ሙስሊሞች "ሒጅራ ወደ አላህ" በሚል ዋትስአፕ ግሩፕ አማካኝነት ለኡስታዝ አቡ ሀይደር ተቋም ምስረታ የሰበሰቡትን 136,500 ብር ድጋፍ አድርገዋል። እናንተስ?



አካውንት ስም = Maqaan akkaawuunti:
SADIK MOHAMMED AHMED

1) የሂጅራ ባንክ አካውንት ቁጥር: Kan baanki hijraa: - 1001162290001

2) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ/Baanki daldala Itiyoopiyaa(COMMERCIAL BANK OF ETHIOPIA): - 1000329226712

3) አቢሲኒያ ባንክ(Baanki Abisiyaa)
83047178

4) አዋሽ ባንክ (Baanki Awaash):
01425212425200

5) ዘምዘም ባንክ 0014688820101

6 ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ
1011300008645

7 OROMIA INTERNATIONAL BANK
1330004700001
8.8K views18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-10 20:47:57 የኢ/ እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት መተዳደሪያ ደንብ በሙሉ ድምፅ ፀደቀ

ለረጅም ጊዜ በእውቅ ህግ ባለሞያዎች ተዘጋጅቶ ሰፊ ውይይት እና ምክክር ሲደረግበት የቆየው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መተዳደሪያ ደንብ(ህገ-መጅሊስ) የመጨረሻው ረቂቅ ለጠቅላላ ጉባኤው ቀርቦ ሰፊ ውይይት እና ምክክር ሲደረግበት ውሏል::

በቀረበው ረቂቅ መተዳደሪያ ደንቡ ላይ በጉባኤው አባላት በርካታ ሃሳቦች ከተሰጡበት ቡኃላ ማሻሻያ ተደርጎበት በሙሉ ድምፅ በጉባኤው አባላት ፀድቋል::

ይህ የፀደቀው መተዳደሪያ ደንብ ጠቅላይ ምክር ቤቱ በቀጣይ የሚመራበት ህገ ደንብ ይሆናል::

ከህገ ደንቡ በተጨማሪ በፕሬዝደንቱ የቀረቡትን የግልግል ሸንጎ አባላት እና የኦዲት እና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ አባላትን በሙሉ ድምፅ ጉባኤው ተቀብሎ አፅድቆታል::

በጉባኤው የጠዋቱ ክፍለጊዜ የ100ቀናት የስራ ክንውን ሪፖርት እና የቀጣይ የ 2015 ረቂቅ በጀት እና እቅድን ተመልክቶ በሙሉ ድምፅ አፅድቆ ነበር::

በግራንድ ኢሊያና ሄቴል ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ልዩ አንደኛ ጠቅላላ ጉባኤ በመጨረሻም በጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት በሸይኽ አብዱል ከሪም ሸይኽ በድረዲን ዱዓ ተዘግቷል።

መረጃው የፌደራል መጅሊስ ነው

ህዳር 1/2015 ዐል
8.8K views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ