Get Mystery Box with random crypto!

Ahmedin Jebel - አሕመዲን ጀበል

የሰርጥ አድራሻ: @ahmedin99
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 60.21K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ይፋዊ የአሕመዲን ጀበል የቴሌግራም ገፅ ነው!

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 38

2022-12-26 06:46:39
ነሲሐ ቲቪን እንደግፍ

"ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም" በሚል መሪ ቃል ለህዝበ ሙስሊሙ ኢስላማዊ ትምህርቶችን ሲያቀርብ የነበረው ነሲሐ ቲቪ ስርጭቱ ተቋርጧል::

የስርጭቱ መቋረጥ የዳዕዋ ክፍተት የሚፈጥር በመሆኑ ሁላችንም ድጋፍ በማድረግ ስርጭቱ ዳግም ተመልሶ ለህዝበ ሙስሊሙ ተደራሽ ይሆን ዘንድ የበኩላችንን ሃላፊነት እንወጣ::

ድጋፍ ለማድረግ ለምትፈልጉ ወንድም እና እህቶች በተከታዩ የባንክ አካውንት ድጋፍ በማድረግ ለነሲሓ ቲቪ ቀጣይነት አስተዋፅኦ ያበርክቱ
***
ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር

-ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 444
ወይም 1000145615929

– ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል 1445091300001

– አቢሲኒያ ባንክ 73169062

– ንብ ኢንተርናሽናል 7000025634638

– ዘምዘም ባንክ 7122

– አዋሽ ባንክ 01410844116300

ነሲሓ ቲቪ... ኢስላማዊ ዕውቀት ለሁሉም!
14.4K views03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 20:30:56 "ዉለታ እንደዋዛ" በሚል መሪ ቃል በሰሜኑ ግጭት የተጎዱ ሃሪማዎችን መልሶ ለማቋቋም እና ለማደራጀት ፕሮጀክት ተወጥኗል ።

ታህሳስ 14 - 2015 : በቢላሉል ሀበሽ ኢስላማዊ ማዕከል የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

ካስማ የበጎ አድራጎት ድርጅት የእስልምና እምነትን
መሰረታዊ አስተምህሮ ከትውልድ ወደ ትዉልድ በማስተላለፍ ሂደት ዉስጥ ዘመን የማይሽረውን መስዋእትነት ከፍለው ባቆዩ እና በሚያቆዩ ሃሪማዎች ፤ ዛውያዎች እንዲሁም መሰል ተቋማት ሊይ
ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራዉና በ አስራ አንድ (11) የቦርድ አባላት የሚመራ ደረጅት መሆኑን በመግለጫችን አንስተናል ።
ሲወርዱ ሲዋረዱ የመጡ ... በቃችሁ ሊባሉ ከሚገቡ ዋነኛ ከ ማዕከላቱ ክፍተቶችና የዚህ ፕሮጀክት አበርክቶዎች ከሚሆኑ መሰረታዊ ተግርባራት ዉስጥም የ ደረሶች ፤ የመሻኢኾችን የምግብ አቅርቦት
ችግር መቅረፍ ፤ የመብራት የዉሃና ሌሎች የመሰረት ልማት እጥረቶችን ማሟላት ፤ የኪታብ (የመጽሃፍት) አቅርቦቶችን በማሻሻል ማእከላቱን የሚመጥኑ ቤተ-መጽሃፍትን ማደራጀት ፤ የሰርአተ ትምህርት ክለሳ ማድረግ እና የ አቅም ማጎልበት ስራዎችን መስራት እንዲሁም በማዕከላቱ የሚገኙ የመረጃ አያያዝ ስርአቶችን ማዘመን በ ካስማ የበጎ አድራጎት ድርጅት የተያዙ ዋነኛ ተግባራት መሆናቸዉም በእለቱ ከተነሱ ነጥቦች መካከል ናቸዉ ።
በዚህም መሰረት 50 የተመረጡ ሃሪማዎች የሶላር ተጠቃሚ ይሆናሉ ፤ ላይብረሪዎች በተደራጀ መልኩ ይገነቡላቸዋል ፤ ምግብና አልባሳት ለማዕከላቱ እና በዙሪያቸው ላሉ የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽ
እንዲሆኑ ይደረጋል ተብሏል ። ተቋማቱን በ ቋሚነት የሚደግፉ ወቅፎች ( ስጦታዎች ) እና የገቢ ማስገኛ ስራዎች ይጀመራሉ ፤ 50 ለሚሆኑ ሼኾች የ ላፕቶፕና የ ሶፍት ኮፒ መጽሃፍት ድጋፍ ይደረጋል ።
እነዚህ ድጋፎች በመደረጋቸው ሳቢያም በተለያዩ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ከ ሃሪማና ዛውያዎች ወጥተው የነበሩ ተማሪዎች ቁጥር መሻሻል ከማሳየቱ ባሻገር ፤ የ ማዕከላቱ የትምህርት አሰጣጥ ጥራት መልካም መሆን ሃሪማና ዛውያዎች ተመራጭ የ ኢስላማዊ እውቀት ተቋማት እንዲሆኑ ያደርጋል ።
በመጨረሻም ካስማ የበጎ አድራጎት ድርጅት ይህን ሀሳብ ለሚደግፉ ሁሉ በሩ ክፍት መሆኑን በ ታላቅ ደስታ ይገልፃል ።

በሚከተሉት የድርጅቱ አካውንቶች ድጋፍ ስላደረጉ እናመሰግናለን።

ዘምዘም ባንክ
0015172010301
አጭር ኮድ
151720

ሂጅራ ባንክ
1000013130001
አጭር ኮድ
1313

ንግድ ባንክ
1000517781178
አጭር ኮድ
4224

#ውለታ_እንደዋዛ!

እናመሰግናለን !!
6.7K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 20:30:52
6.5K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 15:39:15
Warra Shaashamannee maraaf: Inshallah harra galgala salaata magribaa booda magaalaa SHAASHAMANNEE, ganada 01 masjida HAMZAATTI sagantaa daw'aa irratti wal argina.

ለሻሸመኔ ጀመዓዎች በሙሉ: ዛሬ ማታ ከመግሪብ ሰላት በኋላ አላህ ካለ በሻሸመኔ ከተማ፣01 ቀበሌ በሀምዛ መስጂድ በሚኖረን የዳዕዋ ዝግጅት ላይ እንገናኛለን።
3.2K views12:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-16 10:23:30 ሐባን ኢብኑ ሙንቂዝ [ረዐ] እንደዘገቡት:

«አንድ ሰውዬ እንዲህ አለ: ‐ «የአላህ መልክተኛ ሆይ! የዱዓዬን ሲሶ(አንድ አራተኛ) ለርሶ ሶለዋት ላድርገው?»

እርሳቸውም:‐ «ከፈለግክ አዎን!» አሉት።

«ሁለት ሶስተኛውን ላድርገው?» አላቸው።

«አዎን!» በማለት መለሱለት።

«ሁሉንም ለርሶ ሶለዋት ላድርገው?» ጠየቀ።

የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ አሉ:‐ «እንደዚያ ከሆነ ያሳሰበህን የዱንያም ሆነ የአኺራን ነገር አላህ ይገላግልሀል።»

ሹዐቡል‐ኢማን ላይ በይሀቂይ ዘግበውታል።
2.3K viewsedited  07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 13:17:37
ለአጋሮ ከተማና አከባቢው ሙስሊሞች
Muslimoota magaalaa Aggaaroo fi naannoo isheetiif

ዛሬ በአስር ሰላት በኋላ በአጋሮ ከተማ ቡኖ በር (ሂላል) መስጂድ በሚኖረን የዳዕዋ ዝግጅት ላይ እንገናኛለን።

Yoo Rabbin jedhe guyyaa harra salaata asriin booda magaalaa aggaarootti masjidaa bunno barritti (Hilaallitti) sagantaa da'waa jirutti wal argina.
8.5K views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 21:56:21
ኡስታዝ ስዑድ አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ይፈልጋል

በበርካታ ዳእዋዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምናውቀው እንዲሁም ቤተል መስጂድ ላይ በዳእዋው የምናቀው ኡስታዛችን ኡስታዝ ሱዑድ አብዱ በአይን ግፊት አይኖቹ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን አስቸኻይ ህክምና ካላደረገ የአይኖቹን ብሌኖቹን ሊያጣ እንደሚችል ጅዳ ሓይል ሓይፋ ዘጋፍ ሙስተሽፋል ዑዮን ሀኪሞች ነግረውታል ።

አዲስ አበባ ላይ አንድ ግዜ የቀዶ ጥገና ህክምና ያደረገ የነበረ ሲሆን ውጤት ባለማምጣቱ ወደ ሳውዲ ለህክምና ሄዶ የገንዘብ እጥረት እንደገጠመው ከቅርብ ጓደኞቹ ማወቅ ትችሏል። ለህክምናው ወደ 750ሺ የኢትዮጲያ ብር የተጠየቀ ሲሆን ኡስታዝ ስዑድ ይህንን ገንዘብ ከፍሎ መታከም እንዳልቻለ ከቅርብ ወንድሞች ሰምተናል። ስለዚህ የኡስታዝ ስዑድ ዓይኖችን ለመታደግ ገንዘቡ መሸፈን የምትችሉ አህለል ኸይሮች ኡስታዝ ስዑድን ከታች ባሉት አካውንቶች መርዳት ትችላላችሁ።

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000243569749
ሱዑድ አብዱ

በስልክ ለማግኘት

+966 53 505 4896
5.5K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 09:08:24 ያለ በቂ ምክንያት የጁምዓ ሰላትን ያለመስገድ ምን ያክል ወንጀል እንደሆነ ያውቃሉ?

ዝርዝሩን ያንብቡ:- https://t.me/ahmedin99/4723

የጁምዓ አንድ ረከዓና ሁለት ረከዓ ያገኘ ሰው እንዴት እንደሚሰግድ ያውቃሉ?

ዝርዝሩን ያንብቡ:- https://t.me/ahmedin99/4736


በጁምዓ ክልክል የሆኑ ተግባራትን ለማንበብ

https://t.me/ahmedin99/3596
10.1K viewsedited  06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 06:38:19
6.5K views03:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 06:37:32 ሀገር አቀፍ ሀላል ሲምፖዚየም በሸራተን አዲስ ይካሄዳል


የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሀላል ሲምፖዚየም ህዳር 24/2015 በሸራተን አዲስ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።


ምክር ቤቱ ለለፋት 25 ዓመታት የሐላል እርድ ቁጥጥር እና ሴርትፊኬሽን አገልግሎት ሲሰራ መቆየቱን አስታዉቆዋል። በአሁን ሰአት አገራችን ኢትዮጲያ በዋናነት ለተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ ለሳኡዲ አረቢያና ለኳታር ስጋና የስጋ ውጤቶች የምትልክ ሲሆን ለሌሎችም የመካከለኛው ምስራቅ አገራት የሃላል እርድ መስፈርቶችን ባሟሉ መልኩ እየተላከ ይገኛል።

በአሁኑ ወቅት 11 የሃላል እርድ መስፈርትን ካሟሉ ዘመናዊ ቄራዎች ስጋና የስጋ ውጤቶች  የሚላክ ሲሆን በቀጣይም ተጨማሪ ዘመናዊ ቄራዎች ኢንዱስትሪውን ይቀላቀላሉ።

ምክር ቤቱ ለሃላል ቁጥጥር እና ሴርቲፊኬሽን ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት በአለም አቀፍ መመሪያ መሰረት በፋይናንስና በመዋቅር ራሱን የቻለ ሃላል ሰርተፊኬሽን ክፍል በማወቀር በዘርፋ ከፍተኛ ልምድና አለም አቀፍ የሃላል እውቅና ሰርተፊኬት ባላቸው ባለሙያዎች የሚመራ ሲሆን ሃይማኖታዊ ስርአቱን ጠብቆ እንዲሄድ ከም/ቤቱ ስራ አስፈፃሚዎች የተወከሉ ዋናና ምክትል ተጠሪ አሉት።

በተጨማሪም ሃገራዊ ሃላል ኮሚቴ እና የዉስጥ ሐላል ቁጥጥር ኮሚቴ የተዋቀረና በየቄራዉ  የሃላል ስርዓቱን የሚቆጣጠሩ የእንስሳት ሃኪሞችን ምክር ቤቱ የመደበ ሲሆን ተጨማሪ የጤና ምርመራ የሚያደርጉ ሃኪሞችን የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ይመድባል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ በሁሉም ኤክስፓርት ቄራዎች የሃላል እርድ የሚያከናውኑ በለሙያዎችን በማሰልጠንና የብቃት ማረጋገጫ ወረቀት በመስጠት ያሰማራል።

ይህ ዘርፍ ለአገሪቱ ምጣኔ ሀብት እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ሲሆን በ 2013 እና በ 2014 ብቻ በድምሩ ከ200 ሚሊዮን ዶላር በላይ የዉጭ ምንዛሬ አስገኝቷል።

የኦሮሚያ መጅሊስ በቅርቡ ከኳተር በተሰጠው እውቅና መሰረት ኡጋንዳ ለኳታር አለም ዋንጫ ለምታቀርበዉ ስጋ የሃላል ቁጥጥር  እና ሰርተፊኬሽን አገልግሎ መሰረት ለአንድ ኤክስፖርት ቄራ እውቅና ሰጥቷል። የዩጋንዳ ቄራ ይህንን ሊያገኝ የቻለው አስፈላጊ መስፈርቶችን ለኦሮሚያ መጅሊስ በማቅረብና በማሟላት፣ ምክር ቤቱም ቄራውን በአካል ኦዲት አድርጎ ክፍተታቸውን እንዲያሟሉ በማድረግ ነው።

ይህንንም መሰረት በማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ መሰረታዊ ግንዛቤ ለመፍጠር፣  የሀላል ዘርፍን የበለጠ ለማዘመን፣ የኢትዮጵያን የሃላል ምርት ኤክስፖርት ለማሻሻል እና ተደራሽነትን ለማስፋት "ጠንካራ የሃላል ሰርተፊኬሽን ስርዓት ለተሻለ ጤና እና ኢኮኖሚያዊ ልማት" በሚል መሪ ቃል ህዳር 24 ቀን 2015 ከ2:30 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ በሸራተን አዲስ ሆቴል ሀገር አቀፍ የሐላል ሲምፖዚየም አዘጋጅቷል።
6.5K views03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ