Get Mystery Box with random crypto!

አድስ ዜና

የቴሌግራም ቻናል አርማ adszena — አድስ ዜና
የቴሌግራም ቻናል አርማ adszena — አድስ ዜና
የሰርጥ አድራሻ: @adszena
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.34K
የሰርጥ መግለጫ

ወቅታዊ፣ ጠቃሚ እና እንገብጋቢ መረጃወችን ከስር ከስር ለመከታተል የዚህ ቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ሆኑ!
ይጫኑ @adszena
Welcome to addis zena latest Ethiopian news channel you will get trust, usfull and latest news in and around the globe! STAY TUNED WITH ADDIS ZENA👍
@adszena

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-24 21:13:45 አንቶኒዮ ጉተሬዝ ግጭት እንዲቆም ተማፀኑ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ፤ በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን በመስማታቸው ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን ገልፀዋል።

ይህን የገለፁት ፤ ዛሬ ከሚካሄድ የፀጥታው ም/ ቤት ስብሰባ አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ነው።

በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ በጣም ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን የገለፁት ጉተሬዥ በአስቸኳይ ግጭት እንዲቆም ተማፅነዋል።

" ኢትዮጵያውያን ትግራዋዮች፣ አማራዎች፣ ኦሮሞዎች ፣ አፋሮች ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል " ሲሉ ገልፀዋል።

" አጠንክሬ የምጠይቀው በአስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግና የመንግስትና የህወሓት የሰላም ድርድር እንዲቀጥል ነው " ብለዋል።

ጉተሬዥ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ሙሉ ዋስትና እንዲሰጠው ፤ በተጨማሪ የህዝብ አግልግሎቶች ተመልሰው እንዲቋቋሙ ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል ፤ የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ በኢትዮጵያ እንደገና ወታደራዊ ግጭት መፈጠሩን የሚገልፁ ሪፖርቶች መስማታቸው እጅግ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል፤ ሁኔታውን እየተከታተሉ መሆኑንም አመልክተዋል።

ሊቀመንበሩ በአስቸኳይ ግጭት እንዲቆም ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት ንግግሩ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የአፍሪካ ህብረት የሀገሪቱን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ የጋራ ስምምነት ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሂደትን ለመደገፍ ከሁሉም ወገን ጋር አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ ነው ሲሉ አረጋግጠዋል።

ለዚህም ሁሉም ወገኖች ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ ከሆኑት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚደንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ጋር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
705 viewsMAK story, 18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 20:58:04 አጫጭር መረጃዎች

1፤ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በሱዳን አልፎ ለሕወሃት የጦር መሳሪያ በመጫን የኢትዮጵያ አየር ክልልን ጥሶ የገባ አንድ አውሮፕላን መትቶ መጣሉን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የዘመቻዎች ዋና መምሪያ ሃላፊ ሜ/ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ ተናግረዋል። አውሮፕላኑ ተመትቶ የወደቀው፣ ትናንት ምሽት አራት ሰዓት ገደማ በሑመራ ሰሜናዊ ክፍል በኩል ወደ ትግራይ ሲያልፍ እንደሆነ ሜ/ጀኔራል ተስፋዬ ገልጸዋል። ሜ/ጀኔራል ተስፋዬ አውሮፕላኑ "የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ንብረት እንደሆነ ይታመናል" ብለዋል። ሕወሃት በቆቦ ግራና ቀኝ ዞብል ተራራ፣ ቢሶብርና ወትወት በተባሉ አካባቢዎች ንጋት ላይ ውጊያ መክፈቱን ሜ/ጀኔራሉ ጨምረው ገልጸዋል።

2፤ ሕወሃት የተኩስ አቁሙን ውሳኔ በመጣስ ዛሬ ንጋት ላይ በምሥራቅ ግንባር ቢሶብር፣ ዞብልና ተኩለሽ በተባሉ አካባቢዎች ጥቃት መክፈቱን የመንግስት ኮምንኬሽን አገልግሎት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የመንግሥት ኃይሎች ጥቃቱን በተቀናጀ መንገድ እየመከቱ መሆኑን መግለጫው አውስቷል። ሕወሃት በበኩሉ፣ የመንግሥት ኃይሎች በጩቤበር፣ ጃኖራ፣ ጉባጋል፣ አላማጣና ሌሎች ግንባሮች ጥቃት ከፍተውብኛል ሲል ከሷል። ፌደራል መንግሥቱ በሰብዓዊነት ላይ የተመሠረተ የተናጥል ተኩስ አቁም ያወጀው ባለፈው መጋቢት ነበር።

3፤ መንግሥት በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን አገሪቱን ለመበተን የቆረጠው "የሕወሃት የጥፋት ኃይል" የከፈተውን አዲስ ወታደራዊ ጥቃት በአንድነት እንዲመክቱ በቃል አቀባይ ቢሮው በኩል ባወጣው መግለጫ ጥሪ አድርጓል። ሕወሃትን በግድም ይሁን በውድ ወደ ሰላም ለማምጣት ሁሉንም ርምጃዎች እንደሚወስድ የገለጸው መንግሥት፣ ባሁን ወቅት መንግሥትና ጸጥታ ኃይሎች ጥቃቱን ለመቀልበስ ሙሉ አቅማቸውንና ኃይላቸውን አንቀሳቅሰዋል ብሏል። መግለጫው ሕወሃት ላለፉት ስድስት ወራት በምዕራባዊና ደቡባዊ ግንባሮች ያደርጋቸውን ተደጋጋሚ የጥቃት ሙከራዎች መከላከያ ሠራዊት አክሽፎ ግጭቱ እንዳይባባስ ማድረግ ችሎ እንደነበር ጠቅሷል።

4፤ ምርጫ ቦርድ በስድስት የደቡብ ክልል ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች የክልልነት ጥያቄ ላይ ሕዝበ ውሳኔ የሚያካሂድበትን የጊዜ መርሃ ግብር በሕገ መንግሥቱ ገደብ ውስጥ መወሰን የራሱ ሥልጣን መሆኑን ለፌደሬሽን ምክር ቤቱ በላከው ደብዳቤ አስታውቋል። ቦርዱ ይህን ያለው፣ ሕዝበ ውሳኔውን በሦስት ወር ውስጥ እንዲያካሂድ ፌደሬሽን ምክር ቤት ለጻፈለት ደብዳቤ በሰጠው ምላሽ ነው። የሕዝበ ውሳኔውን ማካሄጃ ጊዜ ወደፊት እንደሚገልጽ የገለጠው ቦርዱ፣ ፌደሬሽን ምክር ቤት የወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዖና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም የደራሼ፣ አማሮ፣ ቡርጂ፣ ባስኬቶና አሌ ልዩ ወረዳዎች አንድ አዲስ ክልል ለማዋቀር ውሳኔ ያሳለፉባቸውን ሰነዶች እንዲልክለት ጠይቋል።

5፤ ንግድ ሚንስቴር ግለሰቦች ብቻቸውን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ንግድ ኩባንያ እንዲያቋቁም የሚፈቅድ ረቂቅ መመሪያ ማዘጋጀቱን ሪፖርተር አስነብቧል። ሆኖም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሚያቋቁሙ ግለሰብ ባለሃብቶች፣ አንድ ሕጋዊ የንብረት አደራ ተቀባይ ማስመዝገብ እንደሚኖርባቸው ረቂቅ መመሪያው ያዛል። ከዓመት ከመንፈቅ በፊት በጸደቀው አዲሱ የንግድ ሕግ መሠረት የተረቀቀው መመሪያ፣ አሁን ሥራ ላይ ያለውን የንግድ ኩባንያዎች የምዝገባ፣ ፍቃድ አሰጣጥና የቁጥጥር መመሪያ የሚተካ ነው። ለ60 ዓመታት የቆየው የንግድ ሕግ፣ ኃ/የተ/ የግል ኩባንያ እንዲያቋቁሙ የሚፈቅደው ለሁለትና ከሁለት በላይ ለሆኑ ግለሰቦች ነበር።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ3909 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ4387 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 58 ብር ከ7641 ሳንቲም፣ መሸጫው 59 ብር ከ9394 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ51 ብር ከ9718 ሳንቲም ሲገዛ እና በ53 ብር ከ0112 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል።
681 viewsMAK story, 17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 17:18:37 ሰበር ዜና

የኢትዮጵያን የአየር ክልል ጥሶ ወደ ትግራይ ክልል ሊገባ የነበረ የጦር መሳሪያ የጫነ አዉሮፕላን መመታቱን የኢትዮጵያ መከላከያ አስታወቀ፡፡

በሱዳን አድርጎ የኢትዮጵያን አየር ክልል  ጥሶ በሁመራ ሰሜናዊ ክፍል በኩል ወደ ትግራይ ሊያልፍ የነበረና ለሽብር ቡድኑ የጦር መሳሪያ ሊያቀበል የነበረ ማንንቱ ያልታወቀ አውፕላን በጀግናው አየር ሃይል ሌሊት አራት ሰዓት ላይ ተመትቶ መውደቁን መከላከያ አስታዉቋል፡፡


በሀገር መከላከያ ሠራዊት የመከላከያ ህብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊ ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት፤የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስደፈር የሽብር ቡድኑን እየጋለቡ ያሉ ሃይሎች  አሉ ብለዋል፡፡

ይሁን እንጅ  የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን ለማስክበር በተጠንቀቅ ላይ  መሆናቸውን  ሜጀር ጀነራሉ ተናግረዋል፡፡

በቀጣይም የሽብር ቡድን ሀገር የማፍረስ ህልሙን ትቶ ወደ ሰላማዊ መፍትሔ ካልመጣ እስከመጨረሻው ርምጃ ለመውሰዱ ሙሉ ዝግጅተ መደረጉን  አስታዉቋል፡፡

ላለፉት በርካታ ወራት ከፍኛ ወታደራዊ ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው አሸባሪው ህወሃት ካለፉት ሁለት ሳምንታት ጀምሮ ኃይሉን ለውጊያ ሲያስጠጋ ነበር ተብሏል።


አድስ ዜና
714 viewsMAK story, edited  14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 20:28:28 አጫጭር ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያና ሱማሊያ ግንኙነት መሻከር ጀምሯል ሲል ደይሊ ኔሽን አስነብቧል። ፕሬዝዳንት ሞሐመድ የቀድሞው የአልሸባብ ምክትል አዛዥ ሙክታር ሮቦውን በሚንስትርነት ማስሾማቸው ኢትዮጵያን አስቆጥቷል ያለው ዘገባው፣ ይህንኑ ተከትሎ ኢትዮጵያ ከሱማሊያ ፌደራል ክልሎች ጋር የተናጥል ግንኙነት መጀመሯን ጠቅሷል። የደቡብ ምዕራብ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ አዚዝ ጋሪን በቅርቡ በሚስጢር አዲስ አበባ ሂደው ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር መወያየታቸውን መስማቱን ዘገባው ጠቁሟል። የኢትዮጵያ ጦር መኮንኖች ልዑካን ቡድን ሰሞኑን በደቡብ ምዕራብ፣ ሒርሸበሌ፣ ጁባላንድ ራስ ገዞች ባደረገው ጉብኝት፣ በጸጥታና ሽብርተኝነትን በጋራ በመዋጋት ዙሪያ ተወያይቷል።

2፤ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ መቀመጫውን ፍኖተ ሰላም ከተማ ላይ ያደረገው ምዕራብ ጎጃም ዞን ከሁለት እንዲከፈል የክልሉ ምክር ቤት ያሳለፈው ውሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ለዞኑ ደብዳቤ መጻፋቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። ዞኑ ከሁለት የሚከፈለው፣  ከአገልግሎት አሰጣጥና የልማት ተደራሽነት አንጻር ተጎጅ የሆኑ የአስተዳደር መዋቅሮች ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ነበር። አዲሱን ዞን የሚያዋቅሩት፣ የባሕርዳር ዙሪያ፣ ሰሜን ሜጫ፣ ደቡብ ሜጫ፣ ሰሜን አቸፈር፣ ደቡብ አቸፈር፣ ጎንጅ ቆላ እና ይልማና ዴንሳ ወረዳዎች ከመርዓዊ፣ ዱርቤቴ እና አዴት የከተማ አስተዳደሮች ጋር በመሆን ነው። አዲሱ ዞን በ2016 ዓ፣ም ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

3፤ ኢሰመኮ በአዲስ አበባ ለሚቀርቡለት የሰብዓዊ መብት ጥሰት አቤቱታዎች ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት አመርቂ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችለውን የቅንጅት፣ የትብብርና የቅብብሎሽ ማዕቀፍ መዘርጋቱን አስታውቋል። አዲሱ ማዕቀፍ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለሚፈጸምባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች፣ ታራሚዎችና ተጠርጣሪዎች ከተለያዩ አካላት ጋር በመተባበር ነጻ የሕግ፣ የጤና፣ የመጠለያና የስነ ልቦና ድጋፎችን አሟልቶ መስጠት ያስችላል ተብሏል። ኮሚሽኑ አዲሱን ሥርዓት የዘረጋሁት፣ በፌደራል ማረሚያ ቤቶች፣ ፖሊስ ጣቢያዎችናጊዜያዊ ማቆያዎች የተጠቀሱት አገልግሎቶች አሰጣጥ ክፍተት በመኖሩ ነው ብሏል።

4፤ የኬንያው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተሸናፊ ራይላ ኦዲንጋ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የምርጫውን ውጤት ውድቅ እንዲያደርግ የሚጠይቅ አቤቱታ ዛሬ በበርካታ ማስረጃዎች አስደግፈው ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል። ኦዲንጋ አቤቱታውን ያቀረቡት፣ የምርጫ ኮሚሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶን የምርጫው አሸናፊ ያደረጋቸው በተጭበረበረ የምርጫ ውጤት ነው በማለት ነው። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ባአቤቱታው ላይ በ14 ቀናት ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል።

5፤ በኬንያ የብሪታኒያ አምባሳደር ጄን ማሪዮት በኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ጣልቃ ገብተዋል የሚሉ ክሶችን አስተባብለዋል። አምባሳደሯ በምርጫው ጣልቃ ገብተዋል የሚሉ ትችት የቀረበባቸው፣ ከምርጫ ኮሚሽኑ ሊቀመንበር ዋፉላ ቸቡካቲ ጋር ሰላምታ ሲለዋወጡ የሚያሳይ ፎቶ በኬንያ ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ከተለቀቀ በኋላ ነው። ብሪታኒያ በኬንያ ምርጫ ለይታ የምትደግፈው ፕሬዝዳንታዊ ዕጩ ወይም የፖለቲካ ፓርቲ የለም ያሉት አምባሳደሯ፣ ብሪታኒያ ከኬንያ ጋር ያላትን አጋርነት ለመስረዳት ከተለያዩ ተቋማት ጋር ግንኙነት እናደርጋለን ብለዋል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ3637 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ4110 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 59 ብር ከ1737 ሳንቲም፣ መሸጫው 60 ብር ከ3572 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ52 ብር ከ2324 ሳንቲም ሲገዛ እና በ53 ብር ከ2770 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል
880 viewsMAK story, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 14:19:02 አጫጭር ዜናዎች

1፤ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ 72 አገር በቀል ሲቪል ማኅበራት መንግሥት ለክልሉ የተቋረጡ መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንዲጀምር መማጸናቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። የሲቪል ማኅበራቱ ኅብረት፣ የክልሉ ሰብዓዊ ቀውስ ወደከፋ ሁኔታ እየተሸጋገረ መሆኑን ጠቅሷል።  የትግራይ እናቶችና ሴቶች በባንክ ያስቀመጡትን ገንዘብ ማግኘት አለመቻላቸው፣ ለከፋ ሕይወት እንደዳረጋቸው የክልሉ ሴቶች ማኅበር ገልጧል። መንግሥት የክልሉን መልሶ ግንባታ ተመድ እንዲያከናውነው የተደረሰው ስምምነት እስካሁን ተግባራዊ አልሆነም።

2፤ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የአዲስ አበባና ኦሮሚያ ክልልን አስተዳደራዊ ወሰን ባሁኑ ወቅት ማካለል ጠብ ጠማቂነት ነው በማለት አዲስ ባወጣው መግለጫ ኮንኗል። አስተዳደራዊ ወሰኑ መካለል ያለበት የፌደራል ሥርዓትና የሕገመንግሥት ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ ሊሆን ይገባ እንደነበር ፓርቲው ገልጧል። በቅርቡ በክልሉ እና በከተማዋ መካከል የተካለለው ወሰን፣ ሕገወጥ፣ ሕዝብ ያልመከረበት እና ቅቡልነት የሌለው ነው ብሏል።

3፤ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የጋራ ጸጥታ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በጋራ አዋሳኝ አካባቢዎች የሰላምና ጸጥታ ጸር የሆኑትን ሽብርን፣ ታጣቂ ቡድኖችንና የተደራጁ ወንጀሎችን በሃራ ለመዋጋት የሚያስችል ነው። ስምምነቱ ሕገወጥ የጦር መሳሪያና መድሃኒት ዝውውርን፣ የኢኮኖሚ አሻጥሮችንና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ወንጀሎችንም ለመዋጋት ያለመ ነው። ስምምነቱን የፈረሙት፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ደኅንነት ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጥሩነህ እና የሱዳኑ አቻቸው አኮር ኮር ኩክ ናቸው።

4፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም በአፍሪቃ ቀንድ ለተከሰተው ከባድ ድርቅ ባስቸኳይ 418 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ አስታውቋል። ገንዘቡ የሚያስፈልገው፣ ቦለቀጣዮቹ ስድስት ወራት በኢትዮጵያ፣ ሱማሊያ እና ኬንያ በድርቅ የተጎዱ ተረጅዎችን ምግብ ለማቅረብ እንደሆነ ድርጅት ገልጧል። በቀጠናው ለአራት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች ዝናብ ባለመዝነቡ፣ ባሁኑ ወቅት 22 ሚሊዮን ሕዝብ ለከፍተኛ ምግብ እጥረት ተጋልጧል።

5፤ የአልሸባብ ታጣቂዎች ትናንት ምሽት በሞቃዲሾ የመንግሥት ባለሥልጣናት የሚያዘወትሩትን አያት ሆቴል በኃይል እንደተቆጣጠሩ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ታጣቂዎቹ ሆቴሉን ሰብረው ከመግባታቸው በፊት፣ በአቅራቢያው መኪና ላይ የተጠመዱ ፈንጂዎችን አፈንድተዋል። ከቁስለኞች መካከል የሞቃዲሾ ደኅንነት ሃላፊ ይገኙበታል። የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች በርካታ ቁስለኞችንና ሕጻናትን ከሆቴሉ አስወጥተዋል ተብሏል። ሆቴሉን የተቆጣጠሩት ታጣቂዎች ብዛት አልታወቀም። ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ሥልጣን ከያዙ ወዲህ የመጀመሪያው ከባድ ጥቃት ነው። [
1.1K viewsMAK story, 11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 22:17:18
ከሰሞኑን በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 5 ሺህ ምዕመናን በተሰበሰቡበት በተነሳ የእሳት አደጋ የቤተክርስቲያኑን አገልጋይ ካህን እንዲሁም እድሜያቸው ከ3 እስከ 16 ዓመት የሚሆኑ 18 ሕጻናትን ጨምሮ 41 ምዕመናን ሕይወታቸውን አጥተው ነበር።

ይህን እጅግ አሳዛኝ ክስተት የሰማው የ #ሊቨርፑል እግር ኳስ ክለብ ኮከቡ ሞሀመድ ሳላህ ጉዳት የደረሰባት ቤተክርስቲያን ዳግም እንድትገነባ እንዲሁም ለተጎጂዎች ድጋፍ ማድረጉ ተሰምቷል።

ሞሀመድ ሳላህ ድጋፍ ያደረገው ሶስት ሚሊዮን የግብፅ ፓውንድ (156,664 ዶላር) መሆኑ ተነግሯል።

የሳላህ ድጋፍ በዝነኛው የግብፅ ስፖርት ጋዜጠኛ ኢብራሂም አብድል ጋዋድ የተረጋገጠ ሲሆን የተጫዋቹን በጎ ተግባር የሰሙ ሁሉ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከፍተኛ ምስጋና እያቀረቡለት ይገኛሉ ሲል ዘ ናሽናል በድረገፁ ላይ አስነብቧል።
1.3K viewsMAK story, edited  19:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 21:03:42 ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአዲስ አበባ ከተማና የኦሮሚያ ክልል ልዩ ዞኖችን አስተዳደራዊ ወሰን የማካለል ሥራ መጠናቀቁን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል። የከተማዋ አስተዳደር በከተማዋ ዙሪያ ወደሚገኙ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ዞኖች ዘልቆ በመግባት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያስገነባባቸው እንደ ኮየፈጨ፣ ቱሉዲምቱ እና ጀሞ ቁጥር ሁለት ያሉ ቦታዎች ለኦሮሚያ ክልል መካለላቸውን ከንቲባዋ ገልጸዋል። ለቡ አካባቢ ፉሪ ሃናን እና የኦሮሚያ ኮንዶሚኒየሞችን ጨምሮ እስከ ቀርሳ ወንዝ ድረስ ያሉ ቦታዎች ደሞ ወደ ከተማዋ የተካለሉ ሲሆን፣ ሌሎች አወዛጋቢ ቦታዎች ግን ባሉበት ይቀጥላሉ ተብሏል።

2፤ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ ባለፉት ቀናት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ዘመቻ ካደረጉበት አካላት ተወካዮች ጋር ትናንት በአካል መነጋገሩን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ኩባንያው በኢትዮጵያዊያን መካከል የቋንቋና ባህል አድልዖ እንደማያደርግ ለተወካዮቹ ማረጋገጫ መስጠቱን ገልጧል። የዘመቻውን አስተባባሪዎች ጥያቄዎች እና ስጋቶች በጥሞና ማደመጡን የገለጸው ኩባንያው፣ በማኅበራዊ ትስስር ዘዴዎች የተደረገበትን ዘመቻ በአጽንዖት እንደሚመለከተው ጠቁሟል። የኦሮሞ ብሄር መብት ተሟጋቾች፣ ኩባንያ በሠራተኛ ቅጥርና በአገልግሎት መስጫ ቋንቋዎቹ ለኦሮሞ ብሄር ተወላጆችና ለኦሮሚኛ ቋንቋ በቂ ትኩረት አልሰጠም በማለት ዕቀባ እንዲደረግበት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ሲቀሰቅሱ እንደቆዩ ይታወሳል።

3፤ የወላይታ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ወላይታ ዞን ከአጎራባች ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ጋር በክልልነት እንዲደራጅ የዞኑ ምክር ቤት ያሳለፈው ውሳኔ ለሕዝበ ውሳኔ እንዲቀርብ ለፌደሬሽን ምክር ቤት በላከው ደብዳቤ መጠየቁን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። ፓርቲው በደብዳቤው፣ የዞኑ ምክር ቤት ያሳለፈው ውሳኔ የወላይታ ሕዝብን ፍላጎት የማያንጸባርቅ እና ከሕዝቡ ጀርባ በድብቅ የተወሰነ ውሳኔ ነው ማለቱን ዘገባው አመልክቷል።

4፤ ብሄራዊ ባንክ አገር በቀል ንግድ ባንኮች በከባድ ፉክክር ሂደት ውስጥ እንዳይከስሙ የሚያግዝ ፖሊሲ እየቀረጸ መሆኑን የባንኩ ገዥ ይናገር ደሴ ባንድ የባንኮች ስብሰባ ላይ መናገራቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። ይናገር ብሄራዊ ባንክ ከብዙ ደካማ ባንኮች ይልቅ ጥቂትና የውጭ ባንኮችን ፉክክር መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ባንኮች እንዲኖሩ ፍላጎቱ መሆኑን ተናግረዋል። ባንኩ ንግድ ባንኮች ወደፊት በኢትዮጵያ ከሚሠማሩ የውጭ ባንኮችን ተፎካካሪነት ለመቋቋም እንዲዋሃዱ ሊያስገድድ እንደሚችል እንደተገለጸ ዘገባው ጠቁሟል።

5፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከዩክሬን ወደብ በመርከብ ያስጫነው 23 ሺህ ሜትሪክ ቶን እህል በኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ሱማሊያ እና የመን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የሚያከፋፍለው ዕርዳታ መሆኑን የድርጅቱ ሃላፊዎች ተናግረዋል። የምግብ እህሉን የጫነችው መርከብ ወደ ጅቡቲ ወደብ ጉዞ ጀምራለች። ባለፉት ቀናት ግን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች የምግብ እህሉ በድርቅና ጦርነት ለተጎዱ ኢትዮጵያዊያን ብቻ የሚውል አድርገው ሲዘግቡ እንደቆዩ ይታወሳል።

6፤ የኬንያው ራይላ ኦዱንጋ ትናንት የአገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን ሊቀመንበር ያወጁትን የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንዳደረጉት ዛሬ ራሳቸው በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ኦዲንጋ ለፍርድ ቤት አቤቱታ እንደሚያቀርቡ በይፋ ባይገልጹም፣ ሕገ መንግሥታዊና ሕጋዊ አማራጮችን ግን አሟጠው እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል። ኦዲንጋ የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ምክትል ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ምርጫውን አሸንፈዋል ብለው ያልተረጋገጠውን ውጤት በብቸኝነት ማወጃቸው፣ ኬንያን የሕግና ፖለቲካ ቀውስ ውስጥ አስገብቷታል በማለትም ኦዲንጋ ተናግረዋል። ኦዲንጋ ደጋፊዎቼ ትዕግስተኛ ባይሆኑ ኖሮ፣ የሊቀመንበሩ እወጃ ሁከት ሊያስነሳ ይችል ነበር ብለዋል።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ3067 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ3528 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 60 ብር ከ3731 ሳንቲም፣ መሸጫው 61 ብር ከ5806 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ53 ብር ከ3476 ሳንቲም ሲገዛ እና በ54 ብር ከ4146 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል።
1.1K viewsMAK story, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 21:48:24 አጫጭር መረጃዎች

1፤ የዩክሬን መሠረተ ልማት ሚንስትር ኦሌክሳንደር ኩብራኮቭ አገራቸው ሰሞኑን 23 ሺህ ቶን እህል በመርከብ ወደ ኢትዮጵያ እንደምትልክ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል። ጥራጥሬውን የገዛው የዓለም ምግብ ፕሮግራም እንደሆነ ሚንስትሩ ጠቁመዋል። ዩክሬን ጥራጥሬ ምርቷን ወደ ኢትዮጵያ የምትልከው፣ በጦርነቱ ምክንያት ወደቦቿ ላይ ተከማችቶ የከረመውን የእህል ምርቷን ለዓለም ገበያ እንድታቀርብ በሦስተኛ አደራዳሪዎች አማካኝነት ከሩሲያ ጋር በደረሰችው ስምምነት መሠረት ነው።

2፤ የሕዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር ውሃ ሙሌት ዛሬ በስኬት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። የግድቡ ውሃ ሙሌት መጠናቀቅ የተበሰረው፣ ፕሬዝዳንት ሳሕለወርቅ፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በግድቡ በተገኙበት ስነ ሥርዓት ላይ ነው። የግድቡ መካከለኛ ክፍል ከፍታ 600 ሜትር፣ የግራና ቀኙ ክፍል ደሞ 611 ሜትር መድረሱን ተከትሎ፣ ውሃው በግድቡ አናት ላይ ፈሷል።

3፤ መንግሥት ለትግራይ መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንደገና መጀመርን የድርድር ቅድመ ሁኔታ እንደማያደርግ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ዛሬ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን መግለጫውን የተከታተለው ዶይቸቨለ ዘግቧል። አገልግሎቶቹን እንደገና ለመጀመር ግን፣ የጸጥታ፣ የደኅንነትና የሕግ ጉዳዮችን መፈተሽ እንደሚያስፈልግ መለስ ጠቁመዋል። መንግሥት ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ዕቅድ አውጥተው ወደ ተግባር እንዲገቡ ፍላጎቱ መሆኑን መለስ ጨምረው ገልጸዋል።

4፤ ኢሰመጉ መንግሥት መንገደኞች ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የመግባት መብታቸውን እንዲያስከብርና በከተማዋ ዙሪያ ባሉ ፍተሻ ኬላዎች ላይ መንገደኞችን የሚያጉላሉ፣ የሚደበድቡ፣ የሚያስሩ እና ከመንገደኞች ጉቦ የሚቀበሉ የጸጥታ ኃይል አባላትን በሕግ እንዲጠይቅ ዛሬ ባወጣው ጠይቋል። ሸኖ፣ አለልቱ፣ በኪ፣ ሰንዳፋ እና ለገጣፎ የፍተሻ ኬላዎች ላይ ጸጥታ ኃይሎች መታወቂያ እያዩ የኦሮሚያና የአዲስ አበባ መታወቂያ የሌላቸውን ወደመጡበት እየመለሱ መሆኑን ኢሰመጉ ገልጧል። ሰላምና ትራንስፖርት ሚንስቴሮች በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡት ነሐሴ 3 ላይ መጠየቁንም ኢሰመጉ ጠቅሷል።

5፤ በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እና በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን በግጭትና ጦርነት ለወደሙ የትምህርትና ጤና መሠረተ ልማቶች መልሶ ግንባታ 3.6 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ መንግሥት ካዘጋጀው የመልሶ ግንባታ ሰነድ መመልከቱን ሪፖርተር ዘግቧል። የትምህርትና ጤና ሚንስቴሮች በዓለም ባንክ ድጋፍ በሦስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የሚተገበር የ5 ዓመት የመልሶ ግንባታ ዕቅድ አዘጋጅተዋል። በትምህርት መሠረተ ልማቶችና በመማር ማስተማሩ ሂደት ላይ የደረሰው ኪሳራ ብቻ 2.2 ቢሊዮን ዶላር እንደሚፈልግ በሰነዱ ተመልክቷል።

6፤ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ዓቃቤ ሕግ በሙስና ተጠርጣሪው የቀድሞው የብሄራዊ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ ላይ በ15 ቀናት ውስጥ ክስ እንዲመሰርት ዛሬ ማዘዙን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። ችሎቱ ትዕዛዙን የሰጠው፣ መርማሪ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ መዝገቡን ለዓቃቤ ሕግ ማስተላለፉን በገለጸውና ዓቃቤ ሕግም ለክስ መመስረቻ 15 ቀናት እንዲሰጠው በጠየቀው መሠረት ነው። ጠበቆች ደንበኛቸው የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ያቀረቡትን አቤቱታ ችሎቱ አልተቀበለውም።

7፤ ንግድ ባንክ ለሠራተኞቹ እና ከባንኩ ጋር ለሚሠሩት የኮመርሻል ኖሚኒስ ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን እና ቦነስ መስጠቱን በድረገጹ ባወጣው መረጃ አስታውቋል። ባንኩ የደመወዝ ጭማሪውን የፈቀደው፣ በሰኔ ወር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገቡ እንደሆነ ገልጧል። ባንኩ ባለቀው በጀት ዓመት ከዕቅዱ የ114.4 በመቶ አፈጻጸም በስመዝገብ 27.5 ቢልዮን በላይ ብር ትርፍ አግኝቻለሁ ማለቱ ይታወሳል።

8፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ2795 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ3251 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 60 ብር ከ9208 ሳንቲም፣ መሸጫው 62 ብር ከ1392 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ53 ብር ከ 9681ሳንቲም ሲገዛ እና በ55 ብር ከ0475 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል። አንድ የቻይና ዩዋን ደሞ በ7 ብር ከ0204 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ1608 ሳንቲም ተሽጧል።
1.3K viewsMAK story, 18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 11:09:49 " የቦነስ እና የደሞዝ እርከን ጭማሪ ፈቅዷል " - ንግድ ባንክ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሠራተኞች እና ከባንኩ ጋር ለሚሠሩ የኮሜርሻል ኖሚኒስ ሠራተኞች ቦነስ እና የደሞዝ እርከን ጭማሪ መፍቀዱን አስታወቀ።

ይህን የቦነስ እና የደሞዝ ጭማሪ የተፈቀደው ባንኩ በ2014 (2021/22) በጀት ዓመት አመርቂ ውጤት በማስመዝገቡ ምስጋና ለማቅረብ እና በአዲሱ በጀት ዓመት ከእስካሁኑ የላቀ ስኬትን ሰራተኞች እንዲያስመዘግቡ መሆኑን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በበጀት ዓመቱ ከእቅድ አንጻር የ114.4 በመቶ አፈፃፀም በማስመዝገብ 27.5 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን አስታውሷል።
1.1K viewsMAK story, 08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 10:40:59 ሰበር
ሶስተኛው ዙር ሙሌት በስኬት ተጠናቀቀ።

የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሶስተኛው ዙር ሙሌት በስኬት ተጠናቆ ውሃ በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የግድቡን ሙሌት በስኬት መጠናቀቅ ለማብሰር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መገኘታቸውን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።
991 viewsMAK story, edited  07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ