Get Mystery Box with random crypto!

አድስ ዜና

የቴሌግራም ቻናል አርማ adszena — አድስ ዜና
የቴሌግራም ቻናል አርማ adszena — አድስ ዜና
የሰርጥ አድራሻ: @adszena
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.34K
የሰርጥ መግለጫ

ወቅታዊ፣ ጠቃሚ እና እንገብጋቢ መረጃወችን ከስር ከስር ለመከታተል የዚህ ቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ሆኑ!
ይጫኑ @adszena
Welcome to addis zena latest Ethiopian news channel you will get trust, usfull and latest news in and around the globe! STAY TUNED WITH ADDIS ZENA👍
@adszena

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-28 17:23:20
ፎቶ : እርቀ ሰላም !

በአዊ እና በመተከል ዞን አዋሳኝ ወረዳዎች በሚኖሩ ህዝቦች መካከል የሚፈጠሩ የግጭት መንስኤዎችን  በዘላቂነት ለማስወገድ ዛሬ የእርቀ ሰላም ስነ ስርዓት ተካሂዷል።

በሁለቱ ዞኖች አጎራባች በሆኑ ፓዊና ጃዊ ወረዳዎች በሚኖሩ ህዝቦች የሚፈጠረውን ግጭት በዘላቂነት ለማስወገድ ተስፋ የተጣለበት ይኸው እርቀ ሰላም በጃዊ ወረዳ ወርቅ ሀገር ቀበሌ ነው የተካሄደው።

Photo Credit : መተከል ኮሚኒኬሽን
1.0K viewsMAK story, 14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 13:23:26 የወልድያ ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላለፈ።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማው ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ እና ለጥምሩ ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዛሬ ጥሪ አቅርቧል።

" የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው "  ያለው የወልድያ ከተማ " የአካባቢው ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

ከተማ አስተዳደሩ " የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም " ያለ ሲሆን ሾልኮ ለማለፍና በወሬ ለመፍታት የተደረገው ስልትም እስካሁን አልሰመረም ብሏል።

የከተማ አስተዳደሩ ዛሬ መልዕክቱን ያሰራጨው የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ በአካላዊ እንቅስቅሴ ጭምር በማጣራት መሆኑን አመልክቷል።

ምንም እንኳን አሁንም መሳሪያ ወርዶ ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ እየቀረቡ ቢሆንም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። ህወሓት ከዚህ ቀደም ለሰብዓዊነት ሲባል ተኩስ አቁም በታወጀበት ወቅት ከነበረበት ቦታ ወደፊት በመምጣት የአማራ ክልል ቦታዎችን እየያዘ ነው።

በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ መንግስት እንደተገለፀው የኢትዮጵያ መከላከያ ከቆቦ ከተማ ለቆ ወጥቷል፤ በዚህም ቆቦ በህወሓት ስር ይገኛል።

መንግስት ፤ ህወሓት #የህዝብ_ማዕበል ስልት በመጠቀም ጥቃት እያደረሰ መሆኑን በመግለፅ የህዝብ ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ መከላከያው " ቆቦ " ን መልቀቁን በትለንትናው መግለጫ አስረድቷል።
1.0K viewsMAK story, 10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:36:57 ማምሻውን በወጣ ዜና- መከላከያ ሠራዊት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ከምትገኘው ቆቦ መውጣቱን የመንግሥት ኮምንኬሽን አገልግሎት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ሠራዊቱ ከከተማዋ የወጣው፣ በጦርነቱ ሳቢያ "የሕዝብን ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ" ሲባል እንደሆነ መግለጫው አመልክቷል። ሕወሃት "የሰው ኃይል ማዕበልን" በመጠቀም ቆቦ ከተማን በብዙ አቅጣጫዎች ከቦ እያጠቃ ነው ያለው መግለጫው፣ መከላከያ ሠራዊት ወደኋላ ተመልሶ ከከተማዋ ውጪ ወታደራዊ ይዞታዎችን ለመያዝ መወሰኑን ገልጧል። መንግሥት በዚሁ መግለጫው፣ ሕወሃት በሰርጎ ገቦቹ አማካኝነት በከተማዋ ውስጥ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለመጀመር ሁኔታዎችን እያመቻቸ ይገኛል በማለት ከሷል።
264 viewsMAK story, edited  18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 14:23:25 ሰበር ዜና


የተመረጡ የህዋሓት ወታደራዊ  ዐቅሞች ይመታሉ----መንግስት


መንግሥት እስከ አሁን ድረስ ለሰላም በሩን ክፍት አድርጎ ቢጠባበቅም አሸባሪዉ ህወሓት ጥቃቱን ቀጥሎበታል።

በመሆኑም የፌዴራል  መንግሥት ያለ ቅድመ ሁኔታ ለመነጋገር የገለጸው ዝግጁነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለአሸባሪዉ ፀረ ሰላም ዕብሪት ምንጭ የሆኑ ወታደራዊ ዐቅሞችን ዒላማ ያደረገ ርምጃ ይወስዳል ብሏል። 

የተመረጡ የህዋሓትን ወታደራዊ  ዐቅሞችም ይመታል።

ስለሆነም በትግራይ የምትኖሩ ወገኖቻችን በተለይም የአሸባሪዉ ህወሓት ወታደራዊ መሣሪያዎች እና ማሠልጠኛዎች ካሉባቸው አካባቢዎች ራሳችሁን እንድታርቁ ይመከራል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
707 viewsMAK story, 11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 10:34:46 የተመድ ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሊፖ ግራንዴ በኢትዮጵያ የቆመው ግጭት መቀጠሉ ስጋት እንዳሳደረ እና አሳሳቢ እንደሆነ ገልፀዋል።

የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝን መልዕክት እጋራለሁ ያሉት ግራንዴ አዲስ ግጭት መቀስቀሱ በሲቪሎች ላይ የበለጠ ስቃይን እንደሚያስከትልና በሀገሪቱ ውስጥ እና በድንበር የተፈናቃዮችን ቁጥር እንደሚጨምር ገልፀዋል።

ያሉ ችግሮች እንዳይባባሱ የተኩስ አቁም ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
720 viewsMAK story, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 10:34:15 ለቀጣይ 6 ወራት ተከራት ማስወጣት ፤ ኪራይ መጨመር አይቻልም !

በአዲስ አበባ ከተማ የመኖርያ ቤት ኪራይ መጨመርም ይሁን ተከራይን ማስወጣት የሚከለክለው ደንብ ለሚቀጥሉት #ስድስት ወራት ተራዝሟል።

ይህንን ክለከላ በመተላለፍ ተከራዮችን የሚያስወጡ እና የኪራይ ዋጋን የሚጨምሩ አካላት ላይ ማህበረሰቡ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች ጥቆማውን ለከተማ አስተዳደሩ ማድረስ እንደሚችል ተገልጿል።

አጭር ቁጥር ፡- 9977

የሞባይል ስልኮች 09-00640830 ፣ 09-00640789
696 viewsMAK story, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 10:33:50 #EthiopianAirlines

በአፍሪካ ግዙፉና በደህንነቱ አስተማማኝ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሽልማት ተበረከተለት።

አየር መንገዱ " Global Travel Magazine " ከመንገደኞች ባሰባሰበው ድምፅ መሰረት " የ2022 ዓ.ም ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ " ሽልማትን ማሸነፍ ችሏል።
635 viewsMAK story, 07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 20:06:43 ዐበይት ዜናዎች

1፤ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ዛሬ የሥራ ማቆምና ከቤት ያለመውጣት አድማ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ እንደተመታ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። በከተማዋ የንግድ መደብሮች እና ባንኮች ተዘግተው እና የትራንስፖርት አገልግሎትም ተቋርጦ መዋሉን ነዋሪዎች ተናግረዋል። የከተማዋ ሕዝብ አድማ የመታበት ምክንያት፣ የጉራጌ ዞን የክልልነት ጥያቄ ምላሽ ካለማግኘቱ ጋር የተያይዘ እንደሆነ ዘገባው አመልክቷል። የደቡብ ክልል ጸጥታ ዕዝ የንግድ መደብሮችንና የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ማቋረጥ ክልክል መሆኑን ትናንት አስጠንቅቆ ነበር።

2፤ መንግሥት ሕወሃት ትናንት በመቀሌ የዘረፈውን የዓለም ምግብ ፕሮግራም ነዳጅ እንዲመልስ ዛሬ በቃል አቀባይ ቢሮው በኩል ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። መንግሥት ዓለማቀፍ ድርጅቶች ለነዳጅ ዝርፊያው ቡድኑን ተጠያቂ እንዲያደርጉና ሕወሃትም ሰብዓዊ ዕርዳታ ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንደሚውል ማስተማመኛ እንዲሰጥ ጠይቋል።  የነዳጅ ዝርፊያው የጦር ወንጀልና በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል መሆኑን የጠቀሰው መንግሥት፣ ሕወሃት ዝርፊያውን ለማስቆም የሞከሩ የሰብዓዊ ዕርዳታ ሠራተኞችን አስሯል በማለት ከሷል። ዝርፊያው ሕወሃት ዕርዳታን ለጦርነት ዓላማ ሲጠቀም እንደቆየ ማረጋገጫ መሆኑን መንግሥት ገልጧል።

3፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት ኢትዮጵያ በሱዳን በኩል ጦር መሳሪያ ጭኖ ወደ ትግራይ ሲገባ መትቼ ጣልኩ ካለችው ክስተት ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም ሲል በቃል አቀባዩ በኩል በሰጠው ቃል ማስተባበሉን ብሉምበርግ ዘግቧል። ዜና ምንጩ አንድ የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ የጸጥታ ሹም፣ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጦር መሳሪያ ጭኖ ወደ ትግራይ የገባ አውሮፕላን መትቶ ጥሏል በማለት እንደነገሩት ጠቅሷል። የሕወሃት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው፣ የመንግሥት መረጃ "ሐሰት ነው" ሲሉ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል። መንግሥት መትቼ ጥያለሁ ስላለው አውሮፕላን ከትናንት ወዲህ ተጨማሪ ማብራሪያ አልሰጠም።

4፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በትግራዩ ሕወሃት መካከል ድጋሚ ግጭት ማገርሸቱ አሳስቦናል ሲሉ አሜሪካ እና ቱርክ በየፊናቸው ስጋታቸውን ገልጸዋል።  የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን፣ መንግሥትና ሕወሃት ለሰላም መስፈን ከፍተኛ ጥረቶችን እንዲያደርጉ በትዊተር ገጻቸው አሳስበዋል። የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ ደሞ፣ መንግሥት እና ሕወሃት ወደ ሰላማዊ ንግግር እንዲመለሱና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጠይቋል።

5፤ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ክስ ላይ ዓቃቤ ሕግ ያቀረባቸውን ሰነዶች መርምሮና የተከሳሹን ጠበቆች አስተያየት ምርምሮ ብይን ለመስጠት ለነሐሴ 27 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ቤተሰቦቹ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል። ዓቃቤ ሕግ ያቀረባቸው ማስረጃዎች ጋዜጠኛው ማኔጅንግ ኤዲተርና ባለቤት በሆነባት "ፍትህ" መጽሄት ላይ የታተሙ 17 ጽሁፎችን ነው። ፍርድ ቤቱ በዓቃቤ ሕግ ማስረጃዎች ላይ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ይዞ የነበረው ለዛሬ ሲሆን፣ ሆኖም ሰነዶቹ ብዙ በመሆናቸው ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት እንደተገደደ ገልጧል።

6፤ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎችን አግተው ለኦነግ ሸኔ አሳልፈው ሰጥተዋል በተባሉ አምስት ተከሳሾች ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ በማሳለፍ ለነሐሴ 30 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን አዲስ ማለዳ ዘግቧል። ዛሬ የጥፋተኛነት ውሳኔ የተላለፈባቸው፣ ጋዲሳ ገለቱ፣ ናስር መሐመድ፣ ነብዩ በባክር፣ ከሊፋ አብዱራህማንና ዮሴፍ ጃረታ ናቸው። ጥፋተኞቹ የኦነግ ሸኔን ዓላማ ለማራመድና የዩኒቨርሲቲውን ተማሪዎች ለማገት ከቡድኑ ጋር ተስማምተው እንደነበር በክሱ ተጠቅሷል። ተማሪዎቹ ኅዳር 24፣ 2012 ዓ፣ም የታገቱት፣ ከደምቢዶሎ ወደ አማራ ክልል በሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሲጓዙ ነበር።

7፤ የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን መሐመድ ሥልጣን ከያዙ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ ወደ ፑንትላንድ ራስ ገዝ ማቅናታቸውን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከውጭ ጉዳይ ሚንስትራቸው አብሺር ሁርሴ ጋር ብቻ  ፑንትላንድ የገቡት ፕሬዝዳንቱ፣ ከፑንትላንዱ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ ጋር ተወያይተዋል ተብሏል። ደኒ በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው የፕሬዝዳንት ሞሐመድ ተቀናቃኝ ነበሩ። ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ፑንትላንድ የሄዱት፣ የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በራስ ገዟ ጉብኝት ባደረገና ከፕሬዝዳንት ደኒ ጋር በተወያየ ማግስት ነው።

8፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 52 ብር ከ4077 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ4559 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 59 ብር ከ0182 ሳንቲም፣ መሸጫው 60 ብር ከ1986 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ52 ብር ከ1142 ሳንቲም ሲገዛ እና በ53 ብር ከ1565 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል።
713 viewsMAK story, 17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 14:12:57
#USA

አሜሪካ በመቐለ የህወሓት ኃይሎች 12 የነዳጅ ቦቴዎች " መውሰዳቸው " እንደሚያሳስባት ገለፀች።

ሀገሪቱ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባወጣችው አጭር መግለጫ ፤ " ነዳጁ አስፈላጊ የነፍስ አድን ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ የሚውል ነው ፤ ለኢትዮጵያውያን የሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይደርስ የሚያደርጉ ማንኛውም አይነት ድርጊት እናወግዛለን " ብላለች።

" አሁኑኑ የተሰረቀውን ነዳጅ መልሱ " - WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ድርጅታቸው ለእርዳታ ሥራው የሚያውለውን 570,000 ሊትር ነዳጅ " የትግራይ ባለሥልጣናት ሰርቀዋል " ብለዋል።

" ምግብ ለማድረስ ነዳጅ ከሌለን በሚሊዮኖች ይራባሉ " ያሉት ቢዝሊ ድርጊቱን " የሚያስቆጣ እና አሳፋሪ " ብለውታል።

አሁኑን የተሰረቀው ነዳጅ እንዲመለስ ጠይቀዋል።
711 viewsMAK story, edited  11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 23:26:08 ተመድ በመቐለ ነዳጅ መዘረፉን ገለፀ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ ፤ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች በሰጡት መግለጫ ዛሬ ነሀሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም ጥዋት በትግራይ ክልል መዲና ፤ መቐለ ከተማ የሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) መጋዘን መዘረፉን ገልፀዋል።

ዱጃሪች ፤ ዛሬ ማለዳ የትግራይ ኃይሎች መቐለ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን በኃይል በመግባት 12 የነዳጅ ታንከር ተሽከርካሪዎችን 570,000 ሊትር ነዳጅ መውሰዳቸውን ገልፀዋል።

በቦታው የነበረው የዓለም ምግብ ፕሮግራም ቡድን ዘረፋውን ለመከላከል ጥረት አስርጎ እንደነበር ተናግረዋል።

የተዘረፈው ነዳጅ ለሰብዓዊ ድጋፍ ፣ ምግብ፣ ማዳበሪያና ሌሎች አስቸኳይ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የሚውል ነበር ያሉት ዱጃሪች " ነዳጁ በመዘረፉ በመላው ሰሜን ኢትዮጵያ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመድረስ የሚሰራው የሰብዓዊው ድጋፍ ስራ ላይ ተፅኖ ይኖረዋል " ብለዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሰብዓዊ ስራ ሊውል የነበረው ነዳጅ ላይ የተፈፀመውን ዝርፊ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል።
726 viewsMAK story, 20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ