Get Mystery Box with random crypto!

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ addiscitycon — Addis Ababa Design And Construction Works Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ addiscitycon — Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @addiscitycon
ምድቦች: የውስጥ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.92K
የሰርጥ መግለጫ

Government Organization

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 18:12:10 …….በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም እንዳሉት ማዕከሉ በግብዓት ተደራጅቶና ልምድና ክህሎትን አጣምረው በያዙ የተቋሙ መምህራኖች ታግዞ በሚሰጠው ዘመኑን የዋጀ ስልጠና በርካቶችን የታላቅ ሞያ ባለቤት በማድረግ የሀገራችን የሆቴልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪ ዕድገት ላይ የራሱን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነሐሴ 26/2014 ዓ/ም

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity
924 viewsBizuayehu G., 15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:11:34
የሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል G+4 ሕንፃ በይፋ ተመረቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ባለቤትነት እና በመላኩ ግርማ ሕንፃ ስራ ተቋራጭ ተገንብቶ የተጠናቀቀው የጄነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል G+4 ሕንፃ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ፣የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም፣የጉለሌ ክፍለከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል፡፡

የማዕከሉ ግንባታ በተለያዩ ምክንያቶች ሲጓተት ቆይቶ የነበረ ሲሆን የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቢሮው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ባሳለፈው ውሳኔ እና ባደረገው ልዩ ክትትል ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል፡፡

ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ማዕከሉ በ950 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን ሰልጣኞች የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና የሚወስዱባቸው የመማሪያ ክፍሎችና ቢሮዎች፣ባርና ሬስቶራንት፣የሴቶችና የወንዶች የውበት ሳሎን የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣የመኪና ማቆሚያ እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ መሰረተ-ልማቶች ተሟልተውለታል፡፡.........
922 viewsBizuayehu G., 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 17:00:01
አገልግሎት አሰጣጡን ወደላቀ ደረጃ ለማሳደግ ዓቅም የሚፈጥሩ ፕሮጀክቶች በዛሬው ዕለት በጉለሌ ክፍለከተማ በይፋ ተመርቀዋል፡፡

በክፍለከተማው ከተመረቁ ፕሮጀክቶች ውስጥ የሚጠቀሰው ባለ 3 ወለሉ የወረዳ 01 አስተዳደር ህንፃ አንዱ ሲሆን በክፍለከተማው ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ፅ/ቤት ባለቤትነት እንዲሁም በታቡ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ስራ ተቋራጭነት ግንባታው ተከናውኖ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል፡፡

በ230 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈውና ለወረዳው የተለያዩ ፅ/ቤቶች የቢሮ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ ግንባታው ተጠናቆ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይና ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ክብርት ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም እንዲሁም የጉለሌ ክፍለከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ክብርት ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል፡፡

ይህ ሕንፃ የወረዳውን አስተዳደር የቦታ ጥበት በመቅረፍ ለተገልጋዩ ሕብረተሰብ ምቹ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ዓቅም ከመፍጠርም ባለፈ ለሰራተኛውም ምቹ ከባቢን በመፍጠርና የስራ ተነሳሽነቱን ወደላቀ ደረጃ ከፍ በማድረግ ምርታማነቱን የማሳደግ አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በመንግስት ወጪ የተገነቡ 17 ፕሮጀክቶችን ጨምሮ 104 የቤት ዕድሳት ስራዎችና ሌሎች ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነሐሴ 26/2014 ዓ/ም
889 viewsBizuayehu G., 14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 15:59:49
የጉለሌ ክፍለከተማ ሲያስገነባቸው የቆዩትን የልማት ፕሮጀክቶች በዛሬው ዕለት በይፋ አስመረቀ፡፡

በክፍለከተማው የተገነቡና ከ171.2 ሚሊዮን ብር በላይ በመንግስት ወጪ የተደረገባቸው 17 የልማት ፕሮጀክቶች እንዲሁም 52 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው 104 ቤት ዕድሳት ስራዎችና 33.7 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የኮብልስቶን፣የፖሊስ ኮሚኒቲ ማዕከል፣የድጋፍ ግንብ የዲች ዝርጋታና የካልቨርት ስራዎችና ሌሎችም የልማት ግንባታዎች በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይ በተገኙበት በይፋ ተመርቀዋል፡፡

በጉለሌ ክፍለከተማ ከተገነቡ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ያስገነባውና መገኛው በአዲስ ከተማ ክፍለከተማ የሆነው የጄነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከል ባለ 5 ወለል ሕንፃ፣የወረዳ 01 አስተዳደር ባለ 3 ወለል ሕንፃ፣የጉቶሜዳ ስፖርት ማዘውተሪያ በዛሬው ዕለት ከተመረቁ ከተመረቁ ፕሮጀክቶች ውስጥ የሚጠቀሱ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪም በክፍለከተማው የመጀመሪያ የሆነው የተስፋ ብርሀን ምገባ ማዕከል ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተጥሏል፡፡

በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ክብርት ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም፣የጉለሌ ክፍለከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ክብርት ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነሐሴ 26/2014 ዓ/ም
1.0K viewsBizuayehu G., 12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 16:20:57
1.2K viewsBizuayehu G., 13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 15:57:38
1.1K viewsBizuayehu G., 12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 23:19:50
1.5K viewsBizuayehu G., 20:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 22:36:18
1.3K viewsBizuayehu G., 19:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ