2022-08-30 06:29:10
ጃዕፈር ኢብን አቡጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁ
┈┈•••✿❒ ❒✿•••┈┈
ክፍል አንድ
✿•••✿•••✿
《ጀዕፈርን፥ ጀነት ውስጥ ሁለት በደም የደመቀ ክንፎች ባለቤት ሆኖ አየሁት።》
« ነብዩ ሙሐመድ ﷺ»
ምንም እንኳን በቁረይሾች ታላቅ የክብር አይን ቢታዩም የረሱል ﷺ አጎት አቡ-ጧሊብ በሀብት ረገድ ድሀ ነበሩ።
ቤተሰባቸውን መቀለብ የተሳናቸው የብዙ ልጆች አባት የሆኑት አቡጧሊብ ምድረ ዓረቢያን ድርቅ ሲመታት ችግሩ ተባባሰባቸው። ሰብሎችን ያጠፋውና ከብቶችን የፈጀው ረሃብ፥ ህዝቡ ከሞት ለማምለጥ ሲል አጥንት እንዲቆረጥም አስገድዶት ነበር። ነብዩ ረሱል ﷺ ለነብይነት ገና ባልታጩበት በዚህ ቀውጢ ወቅት አጎታቸውን አባስን «የወንድምህ የአቡ-ጧሊብ ቤተሰቦች ብዙ ናቸው። ሰው በረሃብ እያለቀ ስለሆነ የተወሰኑትን በመውሰድ እንርዳው» በማለት ሀሳብ አቀረቡ።
አባስም በሀሳቡ ተስማማ አባስ ከረሱል ﷺ ጋር ወደ አቡ ጧሊብ ሄደው ሀሳባቸውን አቀረቡ። አቡ ጧሊብ የዓሊይን (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ታላቅን አቂልን ትተው ከሌሎቹ መርጠው መውሰድ እንደ ሚችሉ ነገሯቸው።
ረሱል ﷺ #ዓሊይን ረ.ዐ አባስ ደግሞ #ጃዕፈርን ረዲየሏሁ ዐንሁን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለመቀላቀል ወሰዷቸው።
ከሃሺም ጎሳ #አምስት ሰወች ነብዩ ሙሀመድን ﷺ በመልክ በጣም ይመስሉ ነበር ይባላል።
ያጎታቸው ልጆች #አቡሱፍያን ኢብን አል-ሃሪስና #ቁሳም ኢብን አል አባስ፤ የኢማሙ ሻፊኢይ አያት #አስ-ሳኢብ ኢብን ኡበይድ እንዲሁም ከሁሉም በጣም የሚመስሏቸው የልጃቸ ው ልጅ #ሐሰን ኢብን ዓሊይና የአጎታቸው ልጅ #ጀዕፈር ኢብን አቡ ጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁም ነበሩ።
የትዳር እና የኢስላም ህይወት
┈┈•••✿❒ ❒✿•••┈┈
ጀዕፈር ረዲየሏሁ ዐንሁ በወጣት እድሜው #አስማ ቢንትዑመይስን ረዲየሏሁ ዐንሀ አግብቶ ከአባስ በመለየት ጎጆ መሰረተ። በአቡበክር አስ-ሲዲቅ ረዲየሏሁ ዐንሁ አማካኝነት ከሚስቱ ጋር ኢስላምን በመቀበል ከመጀመሪያወቹ ሙስሊሞች ሆነ። የጀነት መንገድ በሾክ መሞላቷን የተረዱት ጀዕፈርና ሚስቱ ረዲየሏሁ ዐንሁም በቁረይሽ የሚደርስባቸውን ጭካኔና ግፍ በትዕግስት ሊወጡት ቢሞክሩም ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ የመጣው የ ቁረይሽ ሴራ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ፦
«ጌታችን አላህ አንድ ነው» ስላሉ ብቻ በደል እየተፈፀመባቸው ያሉት ንፁሃን ሰዎች ዕጣ ያሳዘናቸው ነብይ ﷺ ወደ ሀበሻ እንዲሰደዱ ትዕዛዝ ሰጡ።
ስደት ወደ ሐበሻ
┈┈•••✿❒ ❒✿•••┈┈
በጀዕፈር ረዲየሏሁ ዐንሁ መሪነት ወደ አቢሲኒያ (ኢትዬጵያ) የመጀመሪያው ስደት ተደረገ። በፍትሀዊው የኢትዮጵያ ንጉስ ነጃሺ ጥላ ስር በመሆን ሃይማኖታ ቸውን በነፃነት በመተግበር አላህን የመገዛትን ጣዕም ሊቀምሱ ቻሉ። የስደተኞቹ በሰላም መኖር የእግር እሳት የሆነባቸው የቁረይሽ ሹማምንት ወደ መካ የሚመልሱባቸውን መንገድ ያውጠ ነጥኑ ጀመር።
ለዚህ ተግባር የቁረይሽ ግፈኞች #አምር ኢብን አልአስና #አብዱላህ ኢብን አቢ ራቢያን በመወከል ከበርካታ ስጦታወች ጋር ወደ ንጉሱና ጳጳሳቱ ላኩዋቸው።
ኢትዮጵያ እንደደረሱ ለስጦታ ያመጧቸውን ንብረቶች ለጳጳሳቱ በመለገስ «በንጉሱ መሬት የሚንቀሳቀሱ አመፀኛ ወጣቶች አሉ። በአባቶቻቸው ሀይማኖት ላይ ያፌዛሉ፣ ይኮንኑታልም። በህዝባችን መካከል ሁከትና መከፋፈልን ፈጥረዋል። ንጉሱን ስናነጋግር ስለ ሃይማኖታቸው ምንነት ሳይጠይቋቸው እንዲያስረክቡን ጎትጉቱልን። የተከበሩት የህዝባችን መሪወች ስለ እነሱም ሆነ ስለ ሀይማኖታቸው ከሁሉም በላይ ያውቃሉ» አሏቸው። ጳጳሶቹም ተስማሙ።
አምርና ዐብደላህ ብስጦታቸው ለተደሰተው ነጃሽ 《ንጉስ ሆይ! ርኩሳን ወጣቶች ከኛ አምልጠው ወደ ግዛተዎ መጥተዋል። እኛም እርሶም የማናውቀውን ሃይማኖት ይከተላሉ። በወላጆቻቸው እና በህዝባቸው ላይ ያመፁ አፈንጋጮች እንድትመልሱልን የተከበሩ መሪዎቻችን ልከውናል።» ሲሏቸው ንጉሱ ወደ ጳጳሳቱ ዞር ብለው ሲመለከቷቸው።
«ንጉስ ሆይ! እውነታቸውን ነው የተንናገሩት። በህዝባቸው ላይ ምን ፈፅመው እንደመጡ ስለሚያውቁ ለፍትሀዊ ፍርድ ወደነርሱ ይላኩዋቸው» አሉ።
በአስተያየታቸው የተቆጡት ንጉስ ነጃሽ «በፈጣሪ ይሁንብኝ! ለምን እንደተወነጀሉ እራሴ ሳላጣራ አሳልፌ አላስረክባቸወም። እነዚህ ሁለት ሰዎች የሚሉት እውነት ከሆነ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ። ካልሆነ ግን የእኔን ጥበቃ እስከፈለጉ ድረስ በኔ ምድር ይኖራሉ።» በማለት አስደነገጧቸው።
ንጉሱ ሙስሊሞቹ ለችሎት እንዲቀርቡ
አዘዙ። ሙስሊሞቹ ከመሄዳቸው በፊት እነሱን ወክሎ #ጀዕፈር ኢብኑ አቢ-ጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁ ብቻ እንዲናገር ተስማሙ በንጉሱ ቤተ መንግስት ጳጳሳቱ የሚያምር አረንጓዴ ልብስና ማራኪ ቆብ ደፍተው ከንጉሱ ወንበር ግራና ቀኝ ቁጭ ብለዋል ሙስሊሞቹ ሲገቡ ቁረይሾቹ ቦታቸውን ይዘው ነበር። ንጉሱ መጡ።
ቀሳውስት፣ ጳጳሳት፣ ቁረይሽ ወዘተ.. ከሙስሊሞች በስተቀር ሁሉም ለንጉሱ አጎነበሱ።
ንጉሱ ሙስሊሞቹን ለምን የክብር ሰላምታ እንዳልሰጡ ሲጠይቋቸው
«እኛ ለአላህ እንጅ ለሌላ የማናጎነብስ ህዝቦች ነን። »በማለት ነበር በታሪክ የማይረሳውን ቃል ጀዕፋር ረዲየሏሁ ዐንሁ የመለሱት።
ንጉሱ በመገረም «ለመሆኑ ከህዝቦቻችሁ ጋር ሆድና ጀርባ ያደረጋችሁ እምነት ምን አይነት ነው? ወደ እኔ ወይም ወደ ሌላ ህዝቦች ሃይማኖት ለምን አልገባችሁም?» በማለት ጠየቁ።
ጀዕፈር ረዲየሏሁ ዐንሁ ወደፊት ቀረብ በማለት በቅን ልሳን የመካ ሰውን ሁኔታ፣ የኢስላምንና የረሱልን ﷺ ሚና ቁልጭ አድርጎ አቀረበ።
እንዲህ ነበር ያለቸው፦ «ንጉስ ሆይ! በድንቁርናና በምግባረ ብልሹነት የተዘፈቀን፣ ጣዖት አምላኪ፣ የሞተ እንስሳ ተመጋቢ፣ አሰቃቂ እና አፀያፊ ስራወችን የምንፈፅም፣ ዝምድናን የምንቆርጥ፣ እንግዳ የምናስከፋ ህዝቦች ነበርን። ኃይለኛውም ደካማውን የሚበዘብዝ በት ሁኔታ ነበር። በዚህ ሁኔታ ላይ እያለን አላህ ማንነቱን፣ ቤተሰቡንና እውነተኝነቱን የማንክደው መልእክተኛ ላከልን።
እሱም ፦ እውነትን ብቻ እንድንናገር፣ ውለታችንን እንድናከብር፣ ለዘመድ መልካም እንድንውል፣ ጎረቤቶቻችንን እንድንረዳ፣ ከተከለከሉ ነገሮች ሁሉ እድንርቅ፣ ያለ አግባብ ደም ከማፍሰስ እንድንታገድ፣ ከብልግና ተግባሮች እንድንርቅ፣ በውሸት እንዳንመሰክር፣ የሙት ልጅ ሀብት አጭበ ርብረን እንዳንወስድ፣ የንፁህ ሴቶችን ስም እንዳናጠፋና በሀሜት እንዳንለውስ፣ በአላህ ሳናጋራ እሱን ብቻ እንድናመልክ፣ ሶላት እንድንሰ ግድ...አዘዘን። ያዘዘንን በመስራት፥ ከከለከለን ነገር በመከልከል ከእሱና ከአላህ በመጣልን መልዕክት አመን።»
« ክቡር ንጉስ ሆይ! ህዝባችን አሰቃየን ሃይማኖታችንን ክደን ወደድሮው አስፀያፊ ጣዖት አመልኮት እንድንመለስ ለማድረግ አሰቃቂ ቅጣቶች ፈፀመብን። ጨቆነን። ህይወታችንን መምራት አቃተን።የእምነታ ችንን ግዴታወች ማከናወን ተሳነን ለዚህ ነው ሀገራችንን ጥለን በመሰደድ ከሁሉም በፊት እርሰወን መርጠን በመሬትዎ በፍትህና በሰላም ለመኖር የመጣነው።»
ንጉሱ በገለፃው ተማርከዋል። ቢሆንም ነገሩ በዚህ አልተገታም፦
===========
ኢንሻኣላህ ይቅጥላል..........
=========================
አቡ ተቅይ ቃዒድ
========================
ኩን ሰለፍያ አለልጀዳ አሰለፍይ መነሀጅ ኦፊሲላዊ ቻናል
https://t.me/AbuTeqiyPomeChannel
105 viewsአቡ ተቅይ ቃዒድ, 03:29