Get Mystery Box with random crypto!

ዘሪሁን ገሠሠ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zerihunkocha — ዘሪሁን ገሠሠ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zerihunkocha — ዘሪሁን ገሠሠ
የሰርጥ አድራሻ: @zerihunkocha
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.77K
የሰርጥ መግለጫ

በመረጃ እንቀራረብ! በመረጃ እንተሳሰር!

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 37

2022-11-30 22:03:41
3.3K views19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-30 22:03:32 በአርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ የሚኖሩ ወገኖቻችን ፥ ዛሬም ከጨፍጫፊው ቡድን ጋር ተፋጠው ፥ የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ይገኛሉ!

በአርሲ የተለያዩ አካባቢዎች ላለፉት ወራት ያለእረፍት በመፈፀም ላይ ያለውና ብዙዎችን የቀጠፈው ጭፍጨፋና ማሳደድ አሁንም ቀጥሎ ዜጎች እያንዳንዷን ደቂቃ በስጋትና በጭንቀት ውስጥ ለማሳለፍ ተገደዋል፡፡

በአርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ መርቲ ቀበሌ ቆስጣ የሚባል ሰፈር ትናንት ህዳር 20/2015 ዓ.ም ከቀኑ 5:00-7:00 ሰዓት ድረስ በሰላማዊ ነዋሪዎች ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ ጥቃት የከፈተው የኦነግ የሽብር ቡድን ፥ አካባቢውን ተቆጣጥሮ በነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ዘረፋና ድብደባ በመፈፀም ብሎም " ለውጊያ የደረሱ ልጆቻችሁን ስጡን" በማለት ህዝቡን ሲያሸብር ውሎ ወደሌሎች ቀበሌዎች ሲያመራ ፥ ከግማሽ ኪሎ ሜትር በማይበልጥ ርቀት ላይ ሰፍሮ የሚገኘው የመንግሥት ሰራዊት በዝምታ ከመመልከት ውጭ ዜጎችን ሊታደግ አለመቻሉ ፥ ለጥቃት የተዳረገው ህዝብ ተስፋ ቆርጦ ከአካባቢው እንዲሰደድ እያደረገው መሆኑ ተገልጿል ፡፡

ቡድኑ በዚህ ሰአት በዚሁ ዞን ጀጁ ወረዳ መርቲ ቀበሌ እና በአዋሳኞቹ ተስፋ ህይወት ፣ አጫሞ ፣ አዲስ ሂወት ፣ መንበሪ ሂወት የሚባሉት ቀበሌዎች ላይ ባለሀብትና ገንዘብ አላቸው ተብለው የሚታመኑ ነዋሪዎችን ፥ በየቤቱ እየገባ በመዝረፍና በማሸበር ላይ የሚገኝ ሲሆን ነዋሪዎቹ በከፍተኛ ፍርሃት እና ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

የሽብር ቡድኑ ባለፉት ሳምንታት በእነዚህ ቀበሌዎች ህፃናትና ሴቶችን ጨምሮ በርካቶችን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉና ማፈናቀሉ የሚታወስ ነው፡፡
3.4K views19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-30 17:12:31 ማንኛችንም አሸናፊና ተራፊ ወደማንሆንበት ፥ የእልቂት ውቅያኖስ እየተዘፈቅን ነው!

ከስልጣኔ ማማ ላይ የተቆናጠጡት ጀርመኖች ያንን የፋሽስታዊ ስርአት የዘር ፍጅት " የምናፍርበት ታሪካችን!" ብለው በሙዚየም ለአለም መማሪያነት ያስጎበኛሉ፡፡

ዛሬ ላይ " ሁቱና ቱትሲ" ተባብለው ለመጠራራት ሁሉ የሚፈሩት ሩዋንዳውያን በቀናት ሚሊየኖችን ጭጭ ምጭጭ ያደረገውን አስከፊ ጭፍጨፋ " አይደለም እንደዚያ አይነቱ ጥቁር ታሪክ ሊደገምና ፥ የግለሰቦች ፀብ እንኳ መስማት አንሻም!" ሲሉ ከትናንት እልቂት ተምረው ፥ በጥሩ ሀገራዊ የእድገትና የሰላም መንገድ ላይ እየተጓዙ ይገኛሉ!

እኛ ግን ላለፉት 5 አመታት ፍጅትና እልቂት እየተፈፀመ "በቃ!" ማለት ተስኖን ፥ ከሩዋንዳም ሆነ ከጀርመን ከፍ ባለ ደረጃ ፥ ወደፍጅት ውቅያኖስ መንደርደራችንን ቀጥለናል!

ላለፉት 5 አመታት በአብዛኛው የተፈጀውና እየተጨፈጨፈ ብሎም እየተፈናቀለ ያለው የአማራ ህዝብ ብቻ ቢሆንም ፥ እመኑኝ! ይህ ጭካኔና "ነግ በእኔ" የማያስብል የዝምታ መንገዳችን ፥ ማንኛችንንም ወደማያስተርፍ የእልቂት አዘቅት እያንደረደረን ነው!

"ልብ ያለው ፥ ልብ ይበል!"
3.9K viewsedited  14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-30 16:55:47
3.4K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-30 16:55:42 አሳዛኝ ዜና!

የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፣ ባለቆንዳላ የኦነግ ሸኔ አባላት ፣ የሚሊሻ አባላት እና ወጣቶች በጋራ በመሆን በሀሮ አዲስ ዓለም አማራዎች ላይ ተኩስ ከፍተዋል!

በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሞ ወረዳ ሀሮ አዲስ ዓለም ቀበሌ ላይ ህዳር 21/2015 ከቀኑ 7:30 ጀምሮ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፣ ባለቆንዳላ የኦነግ ሸኔ አባላት፣ የሚሊሻ አባላት እና ወጣቶች በጋራ በመሆን በይፋ ጦርነት ከፍተዋል የሚሉት የአካባቢው ነዋሪዎች በየጫካው በመሳደድ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ዲሽቃን ጨምሮ ሌሎች የቡድን መሳሪያዎችን በመጠቀም በሀሮ አዲስ ዓለም ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ የተጠናከረ ወረራ እየተፈጸመ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል።

ህዳር 9 ፣ 10 ፣11 እና 20/2015 ዓ.ም በኪረሞ ፣ በጃርዴጋ ፣ በሰቀላ እና በአካባቢው በርካታ አማራዎችን ከኦነግ ሸኔ ጋር በመሆን የጨፈጨፈው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፥ ዛሬ ህዳር 21/2015 በሀሮ አዲስ ዓለም ተፈናቃይ ህዝብ ላይ ይፋዊ የወረራ ጦርነት ከፍቶ ከተማዋን እያወደመ እና ህዝቡን እያሳደደ መሆኑ ተገልጧል።

ሀሮ አዲስ ዓለም ከነሃሴ 2013 ጀምሮ ባለፉት ዓመታት ከመረጋ ጅሬኛ ፣ ከስኒ ዶሮ ፣ ከቦቃ እና አካባቢው እንዲሁም ከሌሎች የኪረሞ ቀበሌዎች በግፍ የተፈናቀሉ ብቻ ከ50 ሽህ በላይ አማራዎችን ያስጠጋ አካባቢ ነው።

በተጨማሪም ከህዳር 9 እስከ 20/2015 ከኪረሞ ፣ ከወዴሳ ዲማ እና አካባቢው በኦሮሚያ ልዩ ኃይል የተፈናቀሉ ከ52 ሽህ በላይ አማራዎችን ተቀብሎ እያስተናገደ ይገኛል።

በጥቅሎ ነዋሪዎችን ጨምሮ በመቶ ሽህ የሚቆጠር የአማራ ህዝብ የሚኖርበት ሀሮ አዲስ ዓለም ከነቀምት እና ከኪረሞ በእነ አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተላከው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሾችና ቄሮዎችን ጨምሮ ከባለቆንዳላው አሸባሪው ኦነግ ሸኔ ጋር በመተባበር ይፋዊ ጦርነት የተከፈተባቸው መሆኑ ታውቋል።

መንግስት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ያደረጉት በጫካ እየተሳደዱ ያሉ ነዋሪዎች በአስቸኳይ ድረሱልን ሲሉ ጥሪ አድርገዋል።

ዘገባውን ያደረሰን "አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ " ነው፡፡
3.5K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-28 16:33:39
2.9K views13:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-28 16:33:32 ኢትዮጵያ ውስጥ ስንት ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች አሉ ? ማነው ብሔር ? ማንኛውስ ነው ብሔረሰብ ? ህዝብስ ማን ነው?

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ከደቂቃዎች በፊት ፥ ሀዋሳ የሚከበረውን " የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን" አከባበር አስመልክቶ ለኢቢሲ መረጃ ሲሰጡ << …76ቱም ብሔር ብሔረሰቦች ባህላቸውን ፣ አለባበሳቸውን ፣ አመጋገባቸውን ፣ ….ወዘተ የሚያሳይ ዝግጅት አድርገው ሀዋሳ ይገባሉ! >> የሚል አይነት መግለጫ ሲሰጡ የመጣብኝ ጥያቄ ነው፡፡

በኢትዮጵያዊያ ውስጥ ወያኔ ይዞት ከመጣው የብሔር ፖለቲካና ይህን ተከትሎ ለፖለቲካ ፍጆታ ከሚከበረው "የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን" በፊትም ሆነ በኃላ በርካታ ብዘሀነት ፣ ባህል ፣ ወግ ፣ ቋንቋ ፣ አኗኗር ፣ ወዘተ ያላቸው ህዝቦች እንደሚኖሩ የታሪክ ፀሀፍቱም ፣ ከያኒውም ጎብኚውም ሲገልፅ እናውቃለን፡፡ ህገ-መንግስቱ የሚያውቃቸውም የማያውቃቸውም እንዳሉ ታዝበን አልፈናል፡፡ የተወለዱም የሞቱም "ብሔርና ብሔረሰቦች" እንደነበሩ የሚያመላክቱ መረጃዎች አሉ፡፡ ትምህርት ቤት "ኢትዮጵያ ከ83 ብሔርና ብሔረሰቦች አሏት!" ተብለን ስንማር አድገናል፡፡

ለመሆኑ ግን በኢትዮጵያ የፌዴሬሽን ምክር ቤቱም ሆነ "ህገ-መንግስት" የሚሉት የሀገር ማፍረሻ ውል የሚያውቃቸው " ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች" ስንት እንደሆኑ እርግጠኛ ሆናችሁ ታውቁታላችሁ ? ብሔር ማንኛው ነው? ብሔረሰብስ ? ህዝቦችስ ? ልዩነትና አንድነቱስ ምንድን ነው ?

የህግ-ባለሙያው ወንድማችን - Wubishet Mulat - ውብሸት ሙላት የዛሬ 5 አመት ገደማ ይሄን እኔ ያነሳሁትን ጥያቄ በአንድ ፅሁፉ አንስቶት እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡

ውብሸት ከተለያዩ ምንጮች አሰባስቦና ዋቢ ጠቅሶ ካሰፈረው ፅሁፉ ውስጥ ተከታዩ ይገኝበታል ፦

- በደርግ ፦

የኢትዮጵያ ብሔረሰቦች ጥናት ተቋም ጥናት ውጤት ላይ መረዳት እንደሚቻለው 89 ናቸው፡፡ ነገር ግን ጥናቱ 89 ብቻ አለመሆናቸውን ያስረዳል፡፡ ታሪካቸው በአጭሩ የተጻፈው የ75ቱ ብቻ ሲሆን የሌሎቹ ግን ስማቸው ብቻ ተዘርዝሯል፡፡

-በሽግግር ወቅት ፦

☞ በ1984 ዓ.ም. በወጣው አዋጅ ቁጥር 7/84 ላይ 63 ብቻ ተዘርዝረዋል፡፡

☞ በ1987 ዓ.ም. በተደረገው ሕዝብ ቤት ቆጠራ እና የፌደሬሽን ምክር ቤት በሕዝብና ቤት ቆርራው ሪፖርት መሠረት 84 ተቆጥረዋል፡፡

☞ የፌደሬሽን ምክር ቤት መቀመጫ የነበራቸው ደግሞ 67 ብቻ ነበሩ፡፡

☞ ከ1993 ጀምሮ በነበረው የፌደሬሽን ምክር ቤት ደግሞ ወደ 76 ከፍ ያለ ሲሆን ፤ በ2008 ዓ.ም ሥራውን የጀመረው የፌደሬሽን ምክር ቤት ደግሞ መቀመጫ ያላቸው 77 ናቸው፡፡

- በ1999 ዓ.ም. በተደረገው ሕዝብና ቤት ቆጠራ

በዚህ ጊዜ በተደረገው ቆጠራ ደግሞ 85 ሲሆን በ1987 ላይ ከተጠቀሱት ውስጥ አምስቱ ያልተካተቱ ሲሆን ሌሎች ስድስት ግን ተጨምረዋል፡፡ አምስት “ሞተው” ስድስት “ተወልደዋል” ማለት ነው።

"መብታቸውን መልሻለሁ!" የሚል መንግሥት ያላት ፣ የአብዝኃኛው አገራዊ እና መንግሥታዊ መዋቅሮቻችን መሠረታት "ብሔር" የሆኑባት ፥ " የብሔሮች ፥ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን" የምታከብር ፤ ነገር ግን ብዛታቸውን እንኳን በቅጡ የማታውቅ ሀገር - ኢትዮጵያ!

" በኢትዮጵያ ስንት ብሔሮች ፥ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ይገኛሉ?" ቢባል በትክክል ማንም መመለስ የሚችል ያለ አይመስለኝም፡፡

ሠላም!
3.4K views13:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-27 15:40:43
አሁንም " ሳይቃጠል በቅጠል!" እላለሁ!

" ..የታሪክ ሽሚያ - የራሱን ታሪክ መፃፍ የማይችል ፥ የመከነ ትውልድ መገለጫ ነው!"
2.6K views12:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 19:27:52
እንደሰው ሊያመን ያልቻለው የኦሮሚያው እልቂት ባለታሪኮች!

<< ...ይሄ ብልፅግና ፓርቲ ከተመሠረተ ጀምሮ ለእኛ ጨለማ ነው! >>

<< የ6 ወር ነፍሰጡር የሆነችውን የልጄን ሚስት ከነልጇ አቃጥለዋታል! >>

<< ..በጥቅሉ 25 የስጋ ዘመዶቼን ገድለውብኛል! >> ይሉናል!

ሙሉውን ቃለ-መጠይቅ አማራ ሚዲያ ማዕከል / Amara Media Center ላይ ታገኙታላችሁ!

#ሼር
2.0K views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 17:31:31 ይድረስ ለፋኖ ወንድሞቻችን!

"የአማራ ፋኖ አንድነት ምስረታ!" የሚል መረጃ በተለያዩ መንገዶች በስፋት ሲስተጋባ እያየሁ ነው፡፡ እርግጥ ነው! እንቅስቃሴው የማያስደስተው ቢኖር እርሱ በተቃራኒዉ ምድብ ያለ ሀይል ነው፡፡ ነገርግን ከእስካሁኑ ብዙ ልምዶቻችን ተነስቼ እንደታናሽ ወንድማችሁ << ግዴላችሁም! ድምፃችሁን አጥፍታችሁና ከትናንታችሁ ተምራችሁ ፥ መሬት ላይ ከአለት የጠነከረ ተቋምና አደረጃጀት ገንቡ! >> በማለት የተሰማኝን ልገልፅላችሁ እወዳለሁ!

በተጨማሪ አንዳንድ የየቱብም ሆነ የሜንስትሪሚንግ ሚዲያዎች ብሎም የሳይበር አንቂዎች ፥ በሚመለከተው አካል ሳንሱር ተደርገው ከሚወጡ ፋይዳቸው የጎላ መረጃዎች ውጪ የፋኖን መሪዎችና አባላት ኢንተርቪ ከማድረግ ብሎም ያገኛችሁትን ሁሉ ወደአደባባይ ከማውጣት ብትታቀቡ ትርፉ የትየለሌ መሆኑን ሳልጠቁም አላልፍም!

በእኛ ሀገር ብልሹ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ፥ ድምፅን አጥፍቶ በወጀቡ የማይናወጥ ፥ መነሻና መድረሻ ግቡን በቅጡ የተረዳ ህዝባዊ አደረጃጀት መፍጠር ብልሀት እንጂ ፍርሀት አይደለም!
2.7K views14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ