Get Mystery Box with random crypto!

ምርጫ ቦርዱ ለ6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ የ49 ሺህ 407 የምርጫ ጣቢያዎችን ዝርዝር ይፋ አደረገ! | YeneTube

ምርጫ ቦርዱ ለ6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ የ49 ሺህ 407 የምርጫ ጣቢያዎችን ዝርዝር ይፋ አደረገ!

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው 6ኛው አገር አቀፍ የምርጫ ሰሌዳ ላይ በተገለጸው መሰረት የካቲት 03 ቀን የምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ይፋ ማድረጊያ ቀን ነው። በዚህም መሰረት በዛሬው እለት ቦርዱ የምርጫ ምልክት በመውሰድ ለምርጫ ለመወዳደር ዝግጅት እያደረጉ ያሉ ሁሉም ፓርቲዎች የምርጫ ጣቢያዎቹን ዝርዝር በፍላሽ እንዲደርሳቸው ማድረጕን አስታወቋል።

የምርጫ ጣቢያዎቹን ዝርዝር በምርጫ ቦርዱ ድረ-ገፅ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።

በዚህ መሰረት:

በአዲስ አበባ ከተማ - 1,848
በሲዳማ ክልል - 2,247
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል - 699
አፋር ክልል- 1,432
አማራ ክልል- 12,199
ድሬዳዋ ክልል- 305
ጋምቤላ ክልል- 431
ሃረሪ ክልል- 285
ኦሮሚያ ክልል- 17,623
ደ/ብ/ብ/ህ ክልል- 8,281
ሶማሌ ክልል- 4,057

በአጠቃላይ 49 ሺህ 407 የምርጫ ጣቢያዎች ለ6ተኛው ጠቅላላ ምርጫ አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን የምርጫ ጣቢያዎቹን ዝርዝር ከስር ከሚገኘው ሊንክ ላይ ማግኘት ይቻላል።

https://nebe.org.et/am/polling-stations

@YeneTube @FikerAssefa