የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድሮች የዕጩዎች ምዝገባ ቀንን ይፋ አደረገ፡፡
ቦርዱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በኦሮሚያ እና በሃረሪ ክልላዊ መንግስታት የሚወዳደሩ እጩዎች የሚመዘገቡበትን ቀንም ይፋ አድርጓል፡፡
በመሆኑም በሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች እና ቀደም ሲል በተጠቀሱት ክልሎች የሚገኙ እጩዎች ምዝገባ ከየካቲት 8 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11፡30 እንደሚከናወን ቦርዱ አስታውቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa