Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በጎንደር ከተማ ያቋቋመውን የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማዕከል ሥራ አስጀመረ። | YeneTube

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በጎንደር ከተማ ያቋቋመውን የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማዕከል ሥራ አስጀመረ።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ 347 አባላትና ከ140 በላይ አባል ያልሆኑ ተገበያዮች እንዲሁም የኤሌክትሮኒክ የግብይት ማዕከላት በአዲስ አበባ፣ በሃዋሳ፣ በሑመራና በነቀምት ከ22 ሺህ በላይ ደንበኞች አሉት።

ዛሬ ደግሞ በጎንደር ከተማ ዘመናዊ የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማዕከልን ወደ ሥራ አስገብቷል። ማዕከሉ ከ90 በላይ ተገበያዮችን በአንድ የግብይት መርሐ ግብር ማስተናገድ የሚችል ነው።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የኢፌዴሪ ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበልና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድማገኝ ነገራን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው ወደ ሥራ መግባቱ የተበሰረው።

የአካባቢው ተገበያዮች ወደ አዲስ አበባ መሔድ ሳይጠበቅባቸው በቀጥታ የግብይት ውድድሩ አካል እንዲሆኑ የሚያስችላቸው ዘመናዊ አሰራር ነው። ይህም ከፍተኛ ወጭንና እንግልትን የሚቀንስ አሰራር ነው ተብሏል።

ምርት ገበያው የጥራጥሬና ቅባት እህሎችንና ቡና አቅራቢዎች ከሸማቾች ጋር በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት በመደራደር የሚገበያዩበት ዘመናዊና ቀልጣፋ አሠራር መሆኑን በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የንግድ ኦፕሬሽን ከፍተኛ ስፔሻሊስት አቶ ቸርነት ታመነ ለአብመድ ገልጸዋል።

@YeneTube @FikerAssefa