ግብርና ሚኒስቴር ፀረ ተባይ እና የግብርና ኬሚካሎችን የሚረጩ አውሮፕላኖችን በኪራይ ሊያቀርብ ነው ተባለ
የግብርና ሚኒስቴር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት በማሰብ እርሻዎች ላይ ፀረ ተባይ እና ሌሎች የግብርና ኬሚካሎችን ለመርጨት የሚያስችሉ አውሮፕላኖችን በኪራይ ሊያቀርብ መሆኑን ሪፖርተር አስነብቧል።
ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ በምስራቅ እና ሰሜን የአንበጣ ወረራ መከሰቱን ተከትሎ 5 አውሮፕላኖች መግዛቱን ሲገልፅ የኢንሹራንስ እና የጥገና ወጪዎችን እንዲሁም ተባዮችን ለመቆጣጠር የሚያስችል አቅም ለማዳበር አውሮፕላኑን ለግሉ ዘርፍ ሊያከራይ እንደሆነ ገልጿል።
የግብርና ሚኒስቴር ግርማ አመንቴ እነዚህን አውሮፕላኖች ለግሉ ሴክተር እና ለትልልቅ እርሻዎች አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችለውን አሰራር ለመዘርጋት መመሪያ መዘጋጀቱን የገለፁ ሲሆን አገልግሎቱ በቅርቡ ይጀምራል ብለው እንደሚጠብቁ ገልፀዋል።
@TikvahethMagazine