Get Mystery Box with random crypto!

★★የሱሀቦች ዘመን

የቴሌግራም ቻናል አርማ suhabaa — ★★የሱሀቦች ዘመን
የቴሌግራም ቻናል አርማ suhabaa — ★★የሱሀቦች ዘመን
የሰርጥ አድራሻ: @suhabaa
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.92K
የሰርጥ መግለጫ

🌹የሱሀቦች ዘመን 🌹
አላህ ዘንድ (የተወደደ) ሃይማኖት ኢስላም ብቻ ነው፡፡ (ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 19)
https://t.me/lYllYi

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-28 17:27:41 አላህ ሀገራችንን ሰላም አማን ያድርግልን ይጠብቅልን አሏሁመ አሚን አሚን ነብዩ ሙሀመድ ( ሰ.ዐ.ወ ) እንዲህ ብለዋል ፡ ኢትዮጵያ/ሀበሻን/አቢሲኒያ አትንኩዋት !!
በኢስላማዊ ታሪክ ብዙ የኢስላም ታሪክ እና ግኝቶች መገኛ ሀገራችን ኢትዮጵያ (የሀበሻ /የአቢሲኒያ ምድር) ፡፡ ኢትዮጵያ ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) የመረጣት አትንኩዋት ያሉዋት እና ሱሀባዎች የተሰደዱባት ሀገር!! ኢትዮጵያ የቢላል ኢብኑ ረባህ (ረ.ዐ) ሀገር መገኛ !! ኢትዮጵያ የእንቁ ሴት የኡሙ አይመን (በረካ) ነብዩ ሙሀመድን ያሳደገች ሀገር መገኛ !! ኢትዮጽያ የፍትሀዊ ንጉሥ ነጃሺ መገኛ !!
ሐበሻው ቢላል ኢብኑ ረባሕ (ረዐ) የአቡበክር (ረ.ዐ) ስም ሲነሳ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) እንዲህ ይሉ ነበር፦ «አቡበክር ልዑላችን ነው። የኛን ልዑልም ነፃ አውጥቶልናል።» ቢላል ኢብኑ ረባሕ ነው። የኢስላም ሙአዚን እና የጣዖታት አሳፋሪ ሰው ነው። የእምነትና የእውነተኝነት (ኢማንና ሲድቅ) ወርቃማ ፍሬ ነው። በየትኛውም ጊዜና ቦታ ከሚገኙ ሙስሊሞች መካከል ቢያንስ ከአስር ሰባቱ ቢላልን ያውቁታል። ስሙን ዝናውን እና ሚናውን በሚገባ ያወሱታል።
የዚችን እንቁ የሆነች የኡሙ አይመን (የአይመን እናት) (በረካ)ረዲየላሁ ዐንሃ ረሱልን ተንከባክባ ልክ እደልጇ አርጋ ያሳደገች ዱንያ ላይ የጀነት እደሆነች ረሱል ያበሰራት እንቁ ነች ኮ ታሪኩን ባካችሁ ወላሂ በጣም ደስ የሚል ነዉ አብቡት ረሱል ሰለሏህ ወአለይ ወሰለም እዲህ ብለዋል የጀነት ሴት ማግባት የሚሻ ኡሙ አይመንን (በረካን( ያግባ)፡፡
ጀዕፈር ኢብን አቡ ጧሊብ
የጀነት መንገድ በሾክ መሞላቷን የተረዱት ጃዕፈርና (ረዐ) ሚስቱ በቁረይሽ የሚደርስባቸውን ጭካኔና ግፍ ሊወጡት ቢሞክሩም ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ የመጣው የቁረይሽ ሴራ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ (ጌታችን አላህ አንድ ነው ) ስላሉ ብቻ በደል አየተፈፀመባቸዉ ያሉት ንፁሃን ሰዎች እጣ ያሳዘናቸዉ ነብዩ ሙሀመድ (ሰዐወ) በመጨረሻም ወደ ሀበሻ እንዲሰደዱ ትዕዛዝ ሰጡ ፡ በጀዕፈር መሪነት ወደ ሀበሻ /አቢሲኒያ ( ኢትዮጵያ ) የመጀመሪያ ስደት ተደረገ ፡፡
በፍትሃዊዉ የኢትዮጵያ ንጉስ ነጃሺ ጥላ ስር በመሆን ጊዜ ሃይማኖታቸዉን በነፃነት በመተግበር አላህን የመገዛትን ጣዕም ሊቀምሱ ቻሉ ፡፡
አላህ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን ይጠብቅልን አሏሁመ አሚን አሚን
ሳኒ ይመር ( @USTAZSANI )
የሱሀቦች ዘመን
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
474 views14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:10:50 #የሰላት_ማዕዘናት

#አስራ_አራት_ናቸው፡፡

❶ ችሎታ ያለው ሰው መቆም

❷ የመግቢያ ተክቢራ ማለት

❸ ፋቲሐን ማንበብ

❹ ማጎንበስ(ሩኩዕ)

❺ ከአጎነበስንበት ቀጥ ብሎ መቆም

❻ በሰባት የሰውነት አካላት ሱጁድ ማድረግ

❼ ከእሱም መነሳት

❽ በሁለት ሱጁዶች መካከል መቀመጥ

❾ በማንኛውም የ ሰላት ተግባራት እንቅስቃሴ ውስጥ መረጋጋት

❿ ቅደም ተከተል መጠበቅ

❶❶ የመጨረሻውን አተህያቱ(ተሸሁድ)ማንበብ

❶❷ለእሱም መቀመጥ

❶❸ በነብዪ ሙሀመድ (ሰ.ዕ.ወ)ሰለዋት ማውረድና

❶❹ በሁለቱም ጎን ሰላምታ (አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላህ)ማለት ናቸው::
#ኡስማን1424
ሳኒ ይመር ( @USTAZSANI )
የሱሀቦች ዘመን
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
208 views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:10:00 «በኡመቶቼ ላይ አምስት ነገርን ወደው አምስት ነገርን የሚረሱበት ዘመን ይመጣባቸዋል
ዱንያን ይወዳሉ⇨አኺራን ይረሳሉ! ህይወትን ይወዳሉ⇨ሞትን ይረሳሉ! ፎቅን ይወዳሉ⇨ቀብርን ይረሳሉ!
ብርን ይወዳሉ⇨ ሂሳብን{ምርመራ}ይረሳሉ! ፍጡርን ይወዳሉ⇨ፈጣሪን ይረሳሉ
ረሱል ﷺ»
አይ የኛ ነገር ምኑ ተወርቶ
ሊያልቅ!!
ዱንያ ጠፊ ናት ይላሉ ጠፊ እንደሆነችም ያውቃሉ ግን ዘላለማዊ እንደሆነች ይገነባሉ።

ሞት አይቀርም ይላሉ እንደሚሞቱም ያውቃሉ ። ነገር ግን እንደሚኖር ሰው ይለፋሉ።

የተፈጠርነው አላህን ለማገልገልና ባርነታችንም ለአላህ ነው ይላሉ። ጌታ እንደሌለው ነፃ እንደሆነ ሰው ይዝናናሉ።

ርዝቅ ከአላህ ነው ይላሉ። ነገር ግን በራሳቸው ጥረት ብቻ የሚያገኙ ይመስል ይፈጋሉ።

አላህ መሃሪና አዛኝ ነው ይላሉ። ግን በተውባ ወደሱ አይመለሱም።
ከሚሰሩትም ኃጢአትም አይመለሱም።

የአላህ ቅጣቱ ብርቱና አያያዙም የከፋ ነው ይላሉ። ነገር ግን ቅጣቱን እንደሚፈራ ሰው አይፈሩም።
ትዕዛዛቱን ይጥሳሉ ህግጋቱንም ይደፍራሉ።

ብሎም በስቅና በዛዛታ ወሮ ይጠመዳሉ !!
ለዚህም ነው የአላህ መልክተኛ እንዲህ ይላሉ:-

يقول عليه الصلاة والسلام: -
لو تعلمون ما أعلم لضحكتم قليلا ولبكيتم كثيرا እኔ የማውቀውን ነገር እናንተ ብታውቁ ኖሩ ጥቂትን ስቃችሁ ብዙውን ታለቅሱ ነበር።
አላህ ይድረስልን!!

✹••••━━✿ ✿━━••••✹

ሳኒ ይመር ( @USTAZSANI )
የሱሀቦች ዘመን
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
143 views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:09:59 ታጋሾችን አበስራቸው›› (2:155)

ትዕግስት የሰው ልጅ ሊኖረው ከሚገቡ ድንቅ ስብዕናዎች መካከል አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ በተለይ በአላህ ያመኑ ሙዕሚኖች ሊሸለሙበት የሚገባ ውድና ድንቅ ጌጥ ነው፡፡ አላህ በተለያዪ የቁርአን አንቀፆች ስለ ትእግስ አውስቷል መልዕክተኛው በሀዲሳቸው አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፣ በህይወታቸውም ብዙ ስቃይና መከራዎችን በትእግስት በማለፍ ተግባራዊ ትምህርት ሰጥተው አሳይተዋል፡፡ የሰው ልጅ በህይወቱ አንዴ በችግርና ሰቆቃ እየታሸ ሌላ ጊዜ ድሎትና ምቾት ፈንጠዝያ እየተፈተነ የሚኖር ፍጡር ነው።

አምላካችን አላህ በተከበረ ቃሉ ቁርአን ስለ ሶብር እንዲህ ብሏል፦

‹‹ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎች በመቀነስ በእርግጥ እንፈትናችኃለን፡፡ ታጋሾችንም (በጀነት) አበስራቸው››
(አል በቀራህ:155)

‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ ታገሱ››
(አል-ዒምራን፡200)

የኢስላም ሊቃውን አንድ ሰው አላህ መልካም ችሮታውን ውሎለት ቢያመሰግን ይሻለዋል ወይስ ፈተና ገጥሞት በዚያ ላይ ቢታገስ በሚለው ሀሳብ ላይ የተለየዩ ሀሳቦችን ከሰነዘሩ ከባድ ልዩነትን ካንፀባረቁ በኃላ በመጨረሻ የደረሱበት መቋጫ ሀሳብ ግን በችግር ላይ መታገስ ይሻለዋለዋል የሚል ነበር።
ምክንያቱም ታላቁ አምላካችን እንዲህ ብሏልና ነው፦

‹‹ታጋሾቹ ምንዳቸውን የሚሰጡት ያለግምት ነው›› (ዙመር፡10)

ያለ መለኪያ፣ያለ ሚዛን ለሰብረኞች ምንዳቸውን ይሰጣቸዋል፡፡ አላህ ካዘጋጃቸው ምንዳዎች ለታጋሾች ከተዘጋጀው የሚበልጥ ምንደ ያለው የለም፡፡

ምንዳ የሚባለውን ነገር ለምሳሌ እንደ "ፍሬ" አድርገን ብንወስደው አመስጋኞች ከፍሬው ተቆጥሮ ሲሰጣቸው ታጋሾች ግን እየታፈሰ ያለገደብ ይሰጣቸዋል።
ስለዚህም ታገስ ምንዳህን ያለ ሀሳብ ያለ ገደብ እፈስ!

‹‹የታገሰና ምህረት ያደረገም ሰው ይህ ከምርሮቹ (ከተፈላጊዎቹ) ነገሮች ነው፡፡›› (ሹራ፡43)
‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በመታገስና በሶላት ተረዳዱ፡፡ አላህ ከታጋሾች ጋር ነውና››(አል በቀራ፡153)

የአኼራን ምንዳን በመፈለግ ነፍስን ከመጥፎ በመከልክል አላህን ከማመፅ በማቀብ ታገዙ፡፡
‹‹ከእናንተም ታጋዮቹንና ታጋሾቹን እስከምናውቅ፣ ወሬዎቻችሁንም እስከምንገልፅ ድረስ በእርግጥ እንሞክራችኃለን›› (ሙሀመድ፡31)

ይህ ማለት እውነተኛው ታጋሽ አማኝ ከውሸተኛው እስከሚለይ ድረስ ላማለት ነው፡፡ ስለዚህ አማኞች ነቃ ብለው ራሳቸውን ሊፈትሹ ይህን ፈተና ለማለፍ ቀን ከሌት ሊጥሩ ይገባል! ለዚህም ትእግስት ያስፈልጋልና ታገሱ
ሳኒ ይመር ( @USTAZSANI )
የሱሀቦች ዘመን
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
138 views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:09:59 "“ኢማን ብዙ ቅርንጫፎች አሉት ከፍተኛውና በላጩ " ላኢላሀ ኢልለላህ»ን ማለት (ከአላህ ሌላ የሚመለክ ኃይል እንደሌለ መመስከር) ሲሆን፣ የመጨረሻውና ዝቅተኛው ከመንገድ ላይ እንቅፋትን ማስወገድ ነው።
«ሐያእ» የኢማን አንዱ ዘርፍ ነው።” ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)
(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
የአንድ የአላህ ባሪያ(ላ ኢላሀ ኢልለሏህ አሏሁ አክበር) ሲል የበላይና የላቀ የሆነው ጌታ እንዲህ ይላል/ባሪያየ እውነት ተናገረ፥ከኔ በቀር አምላክ የለም እኔ ታላቅ ነኝ። ባሪያዉ
(ላ ኢላህ ኢልለሏህ ወህደህ)ሲል ደግሞ (ባሪያየ እውነት አለ ከእኔ ብቻ በቀር አምላክ የለም)።ይላል። (ባሪያዉ) (ላ ኢላህ ኢልላሏህ ላሸርከለሁ) ሲል ባሪያየ እውነት አለ፥ከኔ በቀር አምላክ የለም፤ ለኔም ሽርክ (አጋር)የለኝም። ይላል አላህ(ሱ፡ወ)። የአላህ ባሪያ (ላ ኢላሀ ኢላሀ ኢልለሏህ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሀምዱ) ሲል ባሪያየ እውነት አለ፥ ከኔ በቀር አምላክ የለም። ሥልጣን የኔ ነው። ምስጋናም ለኔ ነዉ።ይላል።የአላህ ባሪያ(ላ ኢላህ ኢልለሏህ ወላ ሀዉለ ወላ ቁወት ኢልላ ቢላህ) ሲል) አላህ(ባሪያየ እውነት አለ፥ከኔ በቀር አምላክ የለም። ኃይልም ብርታትም በኔ እንጂ አይኖርም (አይገኝም)። ምላሽ ይሰጣል። (ኢብን ማጆህ፣ቲርሚዚና ኢብን ሂባን ዘግበውታል።)
ሳኒ ይመር ( @USTAZSANI )
የሱሀቦች ዘመን
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
185 views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 16:49:21 ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.አ.ወ) እንዲህ አሉ ;-
የእኔ ዑማ ከሁሉም ዑማ በላጭ ነው። የሙስሊሞች ችግር ሳያሳስበው አምሽቶ ያነጋ ከኛ አይደለም ! አትጠላሉ፣ አትመቀኛኙ፣ ጀርባ አትሰጣጡ፣ አትቆራረጡ፣ የአላህ ባሪያዎች ወንድማማቾች ሁኑ፣ ሙስሊም ሙስሊም
#አደራችሁን (መጥፎ) ጥርጣሬን ራቁ ከወሬዎች ሁሉ ውሸቱ (መጥፎ) ጥርጣሬ ነው።
(በሰዎች ጉዳይ ላይ) አትመራመሩ (እርስ በራሳችሁ) አትሰላለሉ፣ (በዱንያ ጉዳይ ለምሳሌ በገንዘብ) አትወዳደሩ፣አትመቃቀኙ፣አትኮራረፉ፣ጀርባ አትስጣጡ።እሱ(አላህ) እንዳዘዛችሁ ወንድማማቾች የአላህ ባሪያዎች ሁኑ።ሙስሊም የሙስሊም ወንድም ነው። አይበድለውም፣አያዋርደውም፣አሳንሶ አይመለከተውም።ወደ ደረታቸው እያመለከቱ ተቅዋ እዚጋር ነች ተቅዋ እዚ ጋር ነች(አሉ)።አንድ ሰው ሙስሊም ወንድሙን አሳንሶ መመልከቱ መጥፎ ለመባል ይበቃዋል። ሁሉም ሙስሊም በሁሉም ሙስሊም ላይ ደሙን(ሊያፈስ)፣ ክብሩን (ሊንካ) ፣ገንዘቡን(ሊበላ) እርም ነው (ሀራም ነው አይፈቀድለትም) አላህ ወደ ሰውነት(ገፅታችሁ)፣መልኮቻችሁን አይመለከትም።ነገር ግን ልቦቻችሁንና፣ስራዎቻችሁን ነው የሚመለከተው።
*አላህ ቢረዳችሁ ለእናንተ አሸናፊ የለም፡፡ ቢያዋርዳችሁም ያ ከርሱ (ማዋረድ) በኋላ የሚረዳችሁ ማነው?*
#አላህ ከረዳን ማንም አያሸንፈንም ግን የአላህ እርዳታ ዝምብሎ ያለ ስራ አይመጣም!!!
አላህና መልእክተኛው ያዘዙን ኮቴ በኮቴ ስንፈፅም ያኔ ነስር(ድል) ይመጣል!!!ነገር ግን ትእዛዛቱን ትተን በእራሳችን መንገድ ስንንቀሳቀስ ያኔ ድል ሳይሆን ያለን ውርደት ነው
*በአላህም ላይ ብቻ ምእምናን ይመኩ፡፡*#በአላህ መመካት ሰበቡን ካደረስን በኋላ ነው እንጂ ምንም ሳንሰራ ተወኩል ማድረግ አይባልም ስንፍና ነው።የነብያቶችም መንገድ ይህ አልነበረም።አንዳንድ ሰዎች ያለስራ በአላህ ተወከልን ይላሉ ነገር ግን ማድረግ ያለባቸው የቻሉትን ያህል ሰበብ አድረሰው የውጤቱን ነገር ላይ በአላህ መመካት ነው።
ሀቢቡና ረሱል ﷺ

━━━━━ ━━━━━
የሱሀቦች ዘመን
━━━━━ ━━━━━
┄┄┉┉✽‌»‌ ✿ »‌✽‌┉┉┄┄
ሳኒ ይመር( @USTAZSANI )
┄┄┉┉✽‌»‌ ✿ »‌✽‌┉┉┄┄
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
413 views13:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 16:49:21 «መልካም ስራ ከመጥፎ አደጋ ትጠብቃለች፣ ድብቅ ሰደቃ የሚስጥር ሰደቃ የጌታን ቁጣታጠፋለች፣ ዝምድናን መቀጠል እድሜን ትጨምራለች»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ፦ሶሒሁል ጃሚዕ (3797)
«የበደለህን ይቅር በል፣ ዝምድናውን የቆረጠህን አንተ ቀጥለው፣ ያስቀየመህን አንተ መልካም ዋልለት፣ ሀቅን ተናገር በራስህ ላይ ቢሆንም እንኳን»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ፦ሶሒሁ ተርጊብ (2467)
«የሞቱ ሰወች ቀብራቸው ውስጥ በሚቀጡ ጊዜ ድምፃቸውን እንስሳቶች ይሰማሉ»
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ፦ሶሒሁል ጃሚዕ (1965)
ቀልብህ እንዲለሰልስ ከፈለግክ ዳሃን መግብ፣ የየቲምን ራስ ዳብስ (የቲምን እርዳ)»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ፦ሶሒሁል ጃሚዕ (1410)
«የአላህ ውዴታ የሚገኘው በወላጆች ውዴታ ውስጥ ነው፡ የአላህ ቁጣ የሚገኘው በወላጆች ቁጣ ውስጥ ነው»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ፦ሶሒሁ ቲርሚዚ (1899)
አንድ ሰው በሚቆጣ ጊዜ «አዑዙቢላህ» ካለ፣ወዲያው ቁጣው ይሰክንለታል»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ፦ሶሒሁል ጃሚዕ (695)
«መበቀል እየቻለ ቁጣውን ዋጥ ያደረገን ሰው፣አላህ የቂያማ ቀን ከፍጥረታቱ ሁሉ እርሱን ለይቶ ይጠራውና ከሁረል ዒኖች የምትፈልጋትን መርጠህ ውሰድ ይለዋል»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ቲርሚዚ ዘግበውታል
«ጥፍጥና ቆራጭ የሆነውን ሞትን ማስታውስ አብዙ»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ:-ሶሒሁል ጃሚዕ (1210)
ሳኒ ይመር ( @USTAZSANI )
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
293 views13:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 16:49:21 አላህ ቅጣተ ብርቱ መኾኑን አላህም መሓሪ አዛኝ መኾኑን እወቁ፡፡5:98
አላህ በሚል ጊዜ (አስታውስ)፡- «የመርየም ልጅ ዒሳ ሆይ! በአንተና በእናትህ ላይ (የዋልኩላችሁን) ጸጋዬን አስታውስ፡፡ በሕፃንነትና በከፈኒሳነት (የበሰለ ሰው ኾነህ) ሰዎችን የምትናገር ስትኾን በቅዱስ መንፈስ (በገብሬል) ባበረታሁህ ጊዜ፤ ጽሕፈትንና ጥበብንም ተውራትንና ኢንጂልንም ባስተማርኩህ ጊዜ፣ ከጭቃም የወፍ ቅርጽ ብጤ በፈቃዴ በምትሠራና በውስጧ በምትነፋ በፈቃዴም ወፍ በምትኾን ጊዜ፣ ዕውርም ኾኖ የተወለደንና ለምጻምንም በፈቃዴ በምታሽር ጊዜ፣ ሙታንንም በፈቃዴ (ከመቃብራቸው) በምታወጣ ጊዜ፣ የእስራኤልንም ልጆች በተአምራት በመጣህባቸውና ከእነሱ እነዚያ የካዱት ይህ ግልጽ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም ባሉ ጊዜ፣ (ሊገድሉህ ሲያስቡህ) ከአንተ ላይ በከለከልኩልህም ጊዜ (ያደረግሁልህን ውለታ አስታውስ)፡፡»5:110
አላህም፡- «የመርየም ልጅ ዒሳ ሆይ! አንተ ለሰዎቹ፡- እኔንና እናቴን ከአላህ ሌላ ሁለት አምላኮች አድርጋችሁ ያዙ ብላሃልን» በሚለው ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ጥራት ይገባህ፤ ለእኔ ተገቢዬ ያልኾነን ነገር ማለት ለኔ አይገባኝም፡፡ ብዬው እንደ ኾነም በእርግጥ ዐውቀኸዋል፡፡ በነፍሴ ውስጥ ያለውን ሁሉ ታውቃለህ፡፡ ግን አንተ ዘንድ ያለውን አላውቅም፡፡ አንተ ሩቆችን ሁሉ በጣም ዐዋቂ አንተ ብቻ ነህና» ይላል፡፡5:116
«በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን ተገዙ ማለትን እንጂ ለነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ በውስጣቸውም እስካለሁ ድረስ በነርሱ ላይ ተጣባበቂ ነበርኩ፡፡ በተሞላኸኝም ጊዜ (ባነሳኸኝ ጊዜ) አንተ በነሱ ላይ ተጠባባቂ ነበርክ፡፡ አንተም በነገሩ ሁሉ ላይ ዐዋቂ ነህ፡፡»5:117

الحمد لله على نعمة الإسلام
ሳኒ ይመር ( @USTAZSANI )
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
302 views13:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 11:00:17 ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
﴿إنَّ مِن أفضَلِ أيّامِكم يومَ الجُمعةِ، فأكْثِروا عليَّ الصلاةَ فيه؛ فإنَّ صلاتَكم مَعروضةٌ عليَّ.﴾
“ከቀናችሁ ሁሉ በላጩ የጁምዓ ቀን ነው። በዚህ ቀን በኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ። ሰለዋታችሁ ለኔ ይቀርብልኛልና።”
አቡ ዳውድ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል: 1531
የሱሀቦች ዘመን
ሳኒ ይመር ( @Jumeaeye )
https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA
363 views08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:21:01
360 views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ