Get Mystery Box with random crypto!

️ ንስር አማራ🦅

የሰርጥ አድራሻ: @nisireamhra
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 32.62K
የሰርጥ መግለጫ

የተቀደሰን ነገር በእግሩ ለሚረግጥ ፥ ተመልሶም ያጎረሰውን እጅ ለሚናከስ ርኩስ መጫወቻ የማይሆን የነቃ ማህበረሰብ እስክንፈጥር ድረስ ብዕራችን አይነጥፍም።
አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ፥ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ።
💚💛❤️
እኛን በውስጥ ለማናገር @NISIREamhraa_bot 👈 ይችን አድራሻ ይጠቀሙ🦅
ንስር አማራ🦅
#የግፉአን_ድምፅ
t.me/NISIREamhra

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-05-30 15:22:37 ቀን 21/9/2016 ዓ.ም

ከ:    አማራ ፋኖ በጎንደር የተሰጠ መግለጫ፤
ጉዳዩ:   የምህረት አዋጁ ለተጨማሪ 15 ቀናት መራዘሙን ስለማሳወቅ፤
ለ:       የጸጥታ አካላትና የታችኛው መዋቅር አካላት፦

 አድማ ብተና
 ሚሊሻ
 ህዝባዊ ፖሊስ (አማራ ፖሊስ)
 መከላከያ ሰራዊት
 ፌዴራል ፖሊስ
 መረጃና ደህንነት አካላት
 ለታችኛው የአገዛዙ መዋቅር አካላት በሙሉ፤

የአማራ ፋኖ በጎንደር ለጸጥታና የታችኛው መዋቅር አካላት ያወጣው የምህረት አዋጅ ከግንቦት 6 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የምህረት አዋጁ ጠቀሜታ ላቀ ያለ ሆኖ በመገኘቱ ሳቢያ ለተጨማሪ 15 ቀናት ማለትም ከዛሬ ግንቦት 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲራዘም ተወስኗል፡፡

ከዚህ ቀደም እንደሚታወቀው የአድማ ብተና፣ ሚሊሻ፣ ህዝባዊ ፖሊስ (አማራ ፖሊስ)፣ መከላከያ ሰራዊት፣ ፌዴራል ፖሊስ፣ መረጃና ደህንነት አባላት እንዲሁም የታችኛው መዋቅር የአገዛዙ አካላት በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጦርነት አውጆ ህዝብ እየጨፈጨፈ፣ ቤት ንብረት እያወደመ፣ እንስሳትን እየገደለና የአማራን ህዝብ በቃላት ሊነገር የማይችል ሰቆቃ ውስጥ የጣለው የብልጽግና ሰው በላ አረመኔ አገዛዝ መሳሪያ ሆናችሁ ስታገለግሉ ቆይታችኋል፤ በገዛ ህዝባችሁ ላይም መአት አውርዳችኋል፡፡ እናንተ የምታገለግሉት ክፉና ጨካኝ አገዛዝ ጸረ አማራ እና ጸረ ኢትዮጵያ ከመሆን አልፎ እንስሳትን የሚረሽን፣ ሰብል የሚያቃጥልና የሚያበላሽ፣ እና ቤት ንብረት የሚያወድም፤ ህጻናት ሴቶችን እና እናቶችን ሚደፍር፤ የስድስት አመት ወንድ ህጻን ሳይቀር የሚደፍር አውሬ ስርአት አገልጋዮች ሆናችሁ መቆየታችሁን በዋላችሁባቸው አውደውጊያዎችም ሆነ ውጊያ ባልተደረገባቸው ሰላማዊ መንደሮች በአይናችሁ በብረቱ ተመልክታችኋል፡፡ የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለው ወንጀል ሰማይ ብራና፣ ባህር ቀለም ቢሆን እንኳ ተጽፎ የማያልቅ መሆኑ መቸም ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ የአማራ ህዝብ ተፈጥሮ የሰጠቸውን የመኖር መብት እንደ ወንጀል ቆጥሮ የአማራን ህዝብ ዘር የማጥፋት ወንጀል (Amhara Genocide) የሚፈጽም እና ህዝባችንን ለስደት፣ ለጉስቁልናና ለመጠነ ሰፊ ውድመት የዳረገውን ይህንን አውሬ አገዛዝ ያገለገለ በሙሉ የታሪክ እዳ፣ የሞራል ተጠያቂነት፣ የህሊና ክስ፣ እና የዳኝነት ፍርድ አለበት፡፡ የዚህ ጥቁር ታሪክ ተሳታፊ የሆነ በሙሉ ለማንም የማይገዛውን ኩሩ እና መንፈሰ ጠንካራ የአማራ ህዝብ እሴት የካደ እና ባርነትን ወዶና ፈቅዶ የተሸከመ አሳፋሪና ክብሩን በምስር ወጥ የለወጠ ከሀዲ በመሆኑ የትውልድ አተላ ተብሎ ይቆጠራል፡፡

ይሁንና የአማራ ፋኖ በጎንደር እነዚህ የጸጥታና የታችኛው መዋቅር አካላት የአገዛዙ ታዛዦች ወይም ትእዛዝ ፈጻሚዎች መሆናቸውን ይገነዘባል፡፡ ይህንንም በመረዳት ዛሬ ለአድማ ብተና፣ ሚሊሻ፣ ህዝባዊ ፖሊስ (አማራ ፖሊስ)፣ መከላከያ ሰራዊት፣ ፌዴራል ፖሊስ፣ መረጃና ደህንነት አባላት እንዲሁም የታችኛው መዋቅር የአገዛዙ አካላት ከአሁን በፊት ከግንቦት 6 ቀን እስከ ግንቦት 21 ቀን ለ15 ቀናት እንዲቆይ ሆኖ የጸደቀው የምህረት አዋጅ ለተጨማሪ 15 ቀናት፤ ከግንቦት 22 እስከ ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲራዘም ተወስኗል፡፡


የምህረት አዋጁም የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች ይዟል፦

1) የአማራ ፋኖ በጎንደርን ለመቀላቀል እና ይሄንን ሰው በላ አገዛዝ ለማስወገድ የሚደረገውን ትግል መቀላቀል ለሚፈልጉ የጸጥታ አባላት እና የታችኛው መዋቅር አካላት ሙሉ ምህረት ማድረጉን ያሳውቃል፡፡ ወደ አማራ ፋኖ በጎንደር የሚገቡ የጸጥታና የታችኛው መዋቅር አካላት ትጥቃቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆላቸው፤ ምንም አይነት ጥያቄ ሳይቀርብባቸው፣ አስፈላጊው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷቸው ትግሉን እንደሚቀላቀሉ ሙሉ ማስተማመኛ እንደምንሰጥ እናረጋግጣለን፡፡

2) ወደየቤተሰባቸው መሄድ ለሚፈልጉ የጸጥታ አካላት እና የታችኛው መዋቅር አካላት የአማራ ፋኖ በጎንደር ሙሉ ጥበቃ፣ የትራንስፖርት ገንዘብና አልባሳትን የሚያቀርብላቸው ሲሆን በሰላም ወደቤተሰባቸው እንዲቀላቀሉ ለማስቻል መዋቅራዊ አሰራሩን ሙሉ በሙሉ የሚጠቀም መሆኑን ያሳውቃል፡፡ ይህንን የምህረት አዋጅ ያለምንም እንከን ለማከናወንም የአማራ ህዝብ፤ የአማራ ፋኖ በጎንደር የሰጠውን ትእዛዝ በመፈጸም ለምህረት አዋጁ ተጠቃሚ የጸጥታና የታችኛው መዋቅር አካላት ቀና ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

በመሆኑም የአማራ ፋኖ በጎንደር ለአድማ ብተና፣ ሚሊሻ፣ ህዝባዊ ፖሊስ (አማራ ፖሊስ)፣ መከላከያ ሰራዊት፣ ፌዴራል ፖሊስ፣ መረጃና ደህንነት አባላት እንዲሁም የታችኛው መዋቅር የአገዛዙ አካላት ይሄንን የምህረት አዋጅ እድል በአስቸኳይ እንዲጠቀሙ ሲል ጥሪውን ያቀርባል፡፡ የተሰጠው ቀነገደብ ካለቀ በኋላ እድሉን ሳትጠቀሙበት ብትቀሩ ግን ለሚወሰድባችሁ እርምጃ ሀላፊነቱን ራሳችሁ የምትወስዱ ይሆናል፡፡
ይህንን የምህረት አዋጅ እንዲያስፈጽሙ ጥብቅ ትእዛዝ የተሰጣቸው የአማራ ፋኖ በጎንደር ክፍለጦሮች እና ብርጌዶች የሚከተሉት ናቸው፤

1) ጉና ክፍለጦር
2) ራስ ደጀን ክፍለጦር
3) ዘርዓይ ክፍለጦር
4) አድዋ ክፍለጦር
5) ገብርዬ ክፍለጦር
6) ሜ/ጄ ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለጦር
7) አጼዎቹ ክፍለጦር
8) ቴዎድሮስ ክፍለጦር
9) ተከዜ ክፍለጦር
10) ጥቁር አንበሳ ብርጌድ
11) አስቻለው ደሴ ብርጌድ
12) ነበልባሉ ብርጌድ
13) ድልበር ብርጌድ
14) ቻላቸው እንየው ብርጌድ
15) ጫንድባ ብርጌድ
16) ወንድማማቾች ብርጌድ
17) ተከዜ ተፋሰስ ናደው ብርጌድ

ላለፉት 15 ቀናት የወጣውን የምህረት አዋጅ በመጠቀም በሽህዎች የሚቆጠሩ የጸጥታ አካላትና የታችኛው መዋቅር አካላት እጃቸውን ሰጥተዋል፡፡ አረመኔውን አገዛዝ መታገል የፈለጉት፤ በተለይም ሚሊሻ እና አድማ በታኝ አባላት በገፍ ወደ ፋኖ ሰራዊት ተጠቃለው አስፈላጊው ስልጠና እየተሰጣቸው ይገኛል፡፡ ወደየቤተሰቦቻቸው መሄድ የፈለጉትም እድሉ ተመቻችቶላቸው በሰላም እንዲሄዱ ተደርገዋል፡፡ አሁንም የቀራችሁት የጸጥታና የታችኛው መዋቅር አካላት በእነዚህ 15 ቀናት ውስጥ የምህረት አዋጁን እንድትጠቀሙ ሲል የአማራ ፋኖ በጎንደር ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ የምህረት አዋጁ ከተራዘመበት ግንቦት 22 እስከ ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ጸንቶ የሚቆይ ይሆናል፡፡ የአማራ ፋኖ በጎንደር ይህ የምህረት አዋጅ የመጨረሻ የምህረት አዋጅ መሆኑን በጥብቅ ያሳስባል፡፡

ድል ለፋኖ! ድል ለአማራ ህዝብ!

አርበኛ ባዬ ቀናው፤     
የአማራ ፋኖ በጎንደር ሰብሳቢ
10.1K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-30 13:27:27 #ደምበጫ ..

ከፍኖተሰላም በቀበሮ ሜዳ ቆርጦ ወደ የዘለቃ ለመግባት የሞከረው የጠላት ሀይል ብር ወንዝ ላይ የደንበጫ አናብስቶች ተቀብለው በመጣበት ልክ እያስተናገዱት ነው። በዚህ የአወድ ዉጊያ ቀጥታ እየተሳተፉ የሚገኘው የአማራ ፋኖ በጎጃም ኢንጅነር ክብረ ተመስገን ብርጌድ እና የአከባቢው አርሶአደር በቅንጅት ጠላትን እየለበለቡት ነው።

በተያየዘ ደንበጫ ልዩ ስሙ የዘለቃ ላይ ዛሬ 3ኛ ቀኑን በያዘዉ አዉደ ዉጊያ በሻለቃ ይርሰዉ የሚመራው  ብርጌዱ እስካሁን ድረስ ጠላትን እየቀጠቀጡት ነው። የዘለቃ ላይ የተገኘው ድል ልብ የሚያሞቅ ነው። ዝርዝሩን እንመለስበታለን።


#እናሸንፋለን
#አማራ_ላይጨርስ_አይጀምርም
#ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ
#ድል_ለአማራ_ህዝብ

22/09/16 ዓ.ም

@NISIREamhra
9.5K viewsedited  10:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-30 12:26:35 #የጥንቃቄ መረጃ ደምበጫ ..

የዘለቃ ቀበሌ ያለው የጁላ ጦር ቅርቃር ውስጥ መግባቱን አስቀድመን የገለፅን ሲሆን አሁን ከፍኖተሰላም በ ብርሸለቆ ቀበሮሜዳ ሰንሰን በማድረግ ወደ የዘለቃ ቀበሌ 1ዙ23 እና ስምንት መኪና የጁላ ወታደር እየመጣ ስለሆነ ደፈጣ ይጣል ጥንቃቄ እንዲደረግ መልክት አድርሱ ደውሉ።

ይገባል ማንም አይወጣም።

#እናሸንፋለን
#አማራ_ላይጨርስ_አይጀምርም
#ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ
#ድል_ለአማራ_ህዝብ

22/09/16 ዓ.ም

@NISIREamhra
9.7K viewsedited  09:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-30 11:12:20 #መረጃ ደምበጫ ..

ባለፉት ሶስት ቀናት በደምበጫ ወረዳ የዘለቃ ቀበሌ ከፍተኛ ውጊያ እየተካሄደ እንደነበር መረጃ አድርሰናችሁ ነበር ዛሬ በቀን 22/09/2016 ዓ/ም በየዘረቃ ቀበሌ እየተገረፈ ያለው የጁላ ጦር የድረሱልን ጥሪ ማሰማቱን ተከትሎ ደምበጫ ከተማ ከትሞ የነበረው የጁላ ጦር ሽፋን ለመስጠት ወደ የዘለቃ ቀበሌ ለመንቀሳቀስ መሞከሩን ተከትሎ ፋኖ ከአራቱም አቅጣጫ በመንቀሳቀስ ሽፋን ለመስጠት ሲንቀሳቀስ የነበረውን የጁላ ጦር ከቀኑ 5 ሰአት ጀምሮ እያስጨነቀው ይገኛል።
ይገባል ማንም አይወጣትም ።

#እናሸንፋለን
#አማራ_ላይጨርስ_አይጀምርም
#ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ
#ድል_ለአማራ_ህዝብ

22/09/16 ዓ.ም

@NISIREamhra
9.8K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-30 09:40:01 #የጥንቃቄ መልክት ደጋ ዳሞት..

ደጋ ዳሞት ሀሙስ ገበያ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ የድሮን ጥቃት ሊፈጸም ዝግጅት ላይ ስለሆነ ጥንቃቄ ይደረግ አላስፈላጊ በሆነ ሁኔታ አትሰባሰቡ።

#እናሸንፋለን
#አማራ_ላይጨርስ_አይጀምርም
#ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ
#ድል_ለአማራ_ህዝብ

22/09/16 ዓ.ም

@NISIREamhra
10.1K views06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-30 00:55:43
"…ዐማራ የምትባል እየመጣሁልህ ነው…!

"…አዲስ አበባ ሰማሽ…? …እየመጣሁልሽ ነው አለ እኮ የኦሬክስ ኮማንዶ። ሂድባቸው። ሂድላቸው።

"…ይሄ እመንደሚመጣ ዐውቀው ቀደም ብለው የተዘጋጁቱማ ዝም ብለው እንደበግ አንታረድም። ቤታችን አይፈርስም፣ እንደ ከብት አንነዳም፣ እንደ ጭዳ ዶሮ አንጨፈጨፍም፣ ሚስትና ሴት ልጄን፣ እህቴንና እናቴን አይኔ እያየ አላስደፍርም፣ በግሩፕ በኦሮሞ ወታደር እህት፣ ሚስት እናት ልጄን አላስደፍርም፣ ለኤድስ፣ ለፈንገስ፣ ለጨብጥና ለተላላፊ፣ ለአባለዘር በሽታ አላጋልጥም፣ ካህኔን በደብሩ፣ ታቦቴን በመንበሩ አላስደፍርም፣ ሼኬን ኢማሜን በመስጊዴ አላስደፍርም ያሉ የነቁ፣ የባተቱ፣ የባነኑ ዐማሮችም ና ብለው እሳት አንድደው፣ ቃታ ስበው እየጠበቁት ነው። እንደፎከርክ ሂድና ግጠማቸው።

"…ምንም ማስተባበያ አያስፈልገውም። እንዲህ አድርገው ነው በዐማራ ጥላቻ አሳድገው የአሁኑ የኦሮሞ ቄሮ ዐማራ ሲያይ እረደው፣ እረደው የሚያሰኘው። የነቃ፣ የተጠነቀቀ፣ አስቀድሞ የባነነ በእንዲህ ዓይነት ጨፍጫፊ፣ አረመኔ አይታረድም። ቢያንስ ጥሎት ይወድቃል።

• መጣሁልሽ አዲስ አበባ አለ ቄሮው። አረመኔው አቢይ አሕመድ "መንግሥታችን ተነካ ብለው ከሰንዳፋ፣ ከቡራዩ፣ ከሱሉልታ መጡ፣ ጎረፉ እንዳለው መሆኑ ነው"

• የተጠነቀቀ እርሱ ይድናል። ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ። ተወው ምንአባቱ ያመጣል? ፈሳም፣ ሽንታም፣ ምንጥስዮ፣ ቀብጥርስዮ ማለቱን ትተህ ተዘጋጅተህ ጠብቅ። ኦሮሞ የዋህ ነው። ያሰበውን ነው የሚዘረግፍልህ። አሜሪካም፣ አውሮጳም ሁሉም ያውቁታል። ግን የሚጠፋው ዐማራ ነው ብለው እንደ ሩዋንዳ ዐማራ እስኪጨፈጨፍ ከዳር ቆመው በጉጉት ሞቱን ይጠብቁታል።

• ዐማራ የምትባለው እየመጣሁልህ ነው። ሴቭ አድርገው አለ። ይኸው ሴቭ አድርጉለት።

@ ዘመድኩን በቀለ

#ሰይፍን_በሰይፍ
10.5K views21:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-29 22:45:49 #መረጃና የጥንቃቄ መልዕክት...

በጎንደር #ኤንፍራንዝ አካባቢ ብአዴን ያደራጃቸው ሌቦች በታዘዙት መሰረት ፋኖ ነን እያሉ አማራዎችን ሲሰርቁና ሲያሰቃዩ የቆዩ 15 ሌቦች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል::

እነኝህ በኦነግ ብልፅግና እና አሽከራቸው በሆነው ብአዴን የተደራጁት ሌቦች በተለይም የእስልምና እምነት ተከታይ አማራዎችን ለይቶ በማፍን፣ መሬታቸውን በመንጠቅና በማፈናቀል ሁሌም የሚከሽፈውን የሃይማኖት ካርድ ለመምዘዝ ቢሞክሩም ሙስሊምና ክርስትያን በሆኑት ነበልባል ፋኖዎች በቁጥጥር ስር ገብተዋል:: ፋኖዎቻችን የተፈናቀሉትን አማራዎች ወደመሬታቸው እንዲመለሱ አድርገዋል::

በአማራ ህዝባዊ አብዮት ወደ መቃብሩ እያመራ ያለው ኦነግ ብልፅግና ለመትረፍ በሚያደርገው መፍጨርጨር በተለይም #በደቡብ_ወሎ ቤተ አማራ የሃይማኖት ተኮር ሴራዎችን ለማሴር አቅዷል ሲሉ የመረጃ ምንጮች ገልፀዋል:: ለዚህም ህዝባችን ንቁ ሆኖ የኦሮሙማውን ሴራ ለማክሸፍ ዝግጁ ሊሆን ይገባል::

#እናሸንፋለን
#አማራ_ላይጨርስ_አይጀምርም
#ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ
#ድል_ለአማራ_ህዝብ

21/09/16 ዓ.ም

@NISIREamhra
10.1K viewsedited  19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-29 20:47:10
የዋርካው ማሳሰቢያ ስለቀጣዩ ጦርነት…

የአማራ ፋኖ በወሎ እዝ ወደ ክልሉ በገፍ የገባው የአገዛዙ ጦር ላይ ግዙፍ ጦርነት ሊያወጅ መሆኑን ገለጸ።

የአማራ ፋኖ በወሎ እዝ መሪ ዋርካው ምሬ ወዳጆ ብልጽግና አዳዲስ ምልምል ወታደሮችን እና አለኝ ያለውን ሃይሉን በሙሉ ወደ አማራ ክልል ማስገባቱን አስታውቋል፡፡

ይሁን እንጂ ይህን ሃይል በመጣበት መንገድ ቢመጣ በእኛ ተጋድሎ ተዋርዶ ከመሄድ በዘለለ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም በግፍ ከሚጨፈጨፈው አማራ በላይ አሁን እየታገለ የሚሞተው ስለማይብስ ሁሉም አማራ የትግሉ አካል መሆን እንዳለበትና ትግላችንም እስከ መጨረሻው ይዘልቃል ሲል ዋርካው ምሬ ወዳጆ ገልጿል፡፡

የአገዛዙ ሰራዊት በአማራ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ለማስቆም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የማያዳግም #እርምጃ ለመውሰድ ከባድ ውጊያ እንከፍታለን ሲልም ገልጿል፡፡

በመሆኑም መላው የአማራ ህዝብ ሰሞኑን #የትራንስፖርት_እንቅስቃሴ ገደብ ልንጥን ስላቀድን ህዝባችን ከወዲሁ ተዘጋጅቶ እንዲጠብቀን ሲል ጥሪ አቅርቧል፡፡

#እናሸንፋለን
#አማራ_ላይጨርስ_አይጀምርም
#ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ
#ድል_ለአማራ_ህዝብ

21/09/16 ዓ.ም
10.3K views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-27 15:55:43 3: በስቪል አመራርም ሆነ በወታደራዊ አመራር ሰርዓቱን እያገለገሉ የሚገኙ ግለሰቦች ልጆች እና የቅርብ ዘመዶች፦ እውነት ነው ለጊዜው በብዙ ጥቅማጥቅም አንበሽብሸዋቹህ ይሆናል። በተለይ በዚህ የኦዲት ስራ በሌለበት ወቅት የሚገኘው የህዝብ ሐብት ይበልጥ የሚያጓጓ እንደሆነ እንገነዘባለን። ነገር ግን ልናረጋግጥላችሁ የምንፈልገው ሐቅ ዘራፊ እና ባንዳ ቤተሰቦቻችሁ በጊዜ ወደ ቀልባቸው እንዲመለስ ካላደረጋችሁ በስተቀር የእዳ ደብዳቤያችሁ እስከ ሰባት ቤታችሁ ድረስ ይወራረዳል፤ በአዲሱ የአማራ ትውልድ እጅ ተባዝቶ ይቀመጣል።

4: ፋኖነት ከራስ ክብርና ጥቅም በላይ የሕዝብን ክብርና ጥቅም የማስቀደም፤ “እኔ የምከበረውና የምጠቀመው የሕዝቤ ህልውና ሲከበርና ነፃነቱ ሲረጋገጥ ነው” ብሎ ማመን ሆኖ ሳለ በፋኖ ስም የምታጭበረብሩ ህዝባችን ላይ የቀን ሰው የሌሊት አውሬ የሆናችሁ፤አጀንዳ ያላችሁም ሆናችሁ አጀንዳ የሌላችሁ ፤ለጊዜው ያልታወቃችሁ የመሰላችሁ ከጠላት በላይ ጠላት የሆናችሁ ትንሽ ግለሰቦች፤የቤት ስራችንን ጨርሰን ወደ እናንተ የተመለስን ቀን የኢትዮጵያ ምድር እናንተን አትደብቅም፤ኢትዮጵያ ትጠባችኋለች፤የእኛም ሰወኛ የርህራሄ ባህሪ ከእናንተ ላይ ይቀየራል፤ ለትውልዱ ሁሉ ባንዳነት በአማራ ምድር የተረገመ ተግባር እንደሆነ በእናንተ እናስተምራለን።
ትግሉ የሁሉም እና የዘወትር ነው፤ ሁሉችንም እናብር።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ድል ለአማራ ፋኖ!
የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ!
ግንቦት 19/2016 ዓ/ም
6.7K viewsedited  12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-27 15:55:15 ከአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
**

እንደሚታወቀው የአማራ ፋኖ በተቆጣጠራቸው የአማራ ግዛቶች የራሱን ስቪል አስተዳደር ዘርግቶ ከእናት እና አባቶቹ በወረሰው ሐገር በቀል የስነ መንግስት ስርዓት እያስተዳደረ ይገኛል። በጎንደር ክፍለ ሐገር ውስጥ በሚገኙ አምስት ዞኖች ስር የሚጠቃለሉ ወረዳወች እና የወረዳ ከተሞችም በአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ስር መሆናቸው ይታወቃል።

በእነዚህ ቀጠናዎች ያለው ማህበረሰብ እንደሚያውቀው የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ከዚህ በፊት ደም ምለሳ (በቀል) በሚባል ጎጅ ባህል የሚፈላለግን ባላንጣ ሳይቀር እያስታረቀ፣ እየዳኘ መቀጣት ያለበትን እየቀጣ ማህበረሰቡ ለዘመናት የናፈቀውን ማህበራዊ እረፍት ጭላጭል እያሳየ ይገኛል። ይህ እውነት ማህበረሰቡ እራሱ የሚመሰክረው ሐቅ ነው። በተለይ ጨለማን ተገን አድርገው ይሰርቁ የነበሩ ሌቦች ላይ በተወሰደ የማያዳግም እርምጃ ህብረተሰቡ ይናፈቀው የነበረውን የዘመናት እረፍት እንዲያገኝ ተደርጓል።

ይሁን እንጅ የህዝብ ጥግግታቸው ከፍተኛ የሆኑ ከተሞች ላይ ጦርነት ማድረግ የማህበረሰቡን ሶቀቃ መጨመረ እንደሆነ ከተሞክሯችን ስለተረዳን አስፈላጊ ግዳጅ ከሌለለ በስተቀር የዞን ከተሞችን እና ከፍተኛ የተሽከርካሪ ፍሰት ያለባቸውን ጎዳኖች ለጊዜው ከጦርነት ነፃ ቀጠና አድርገን እንደተውናቸው ይታወቃል። በመሆኑም እነዚህ ነፃ ቀጠናወች አራሱን የኢትዮጵያ መከላከያ ሐይል ብሎ በሚጠራ አሸባሪ ሐይል እና ሌሎች የስርዓቱ አገልጋይ ታጣቂዎች መሸሸጊያ ሆነዋል።

ነገር ግን ድሮውንም የአማራን ህዝብ ማህበራዊ እረፍት የማይፈልገው ይህ ገዳይ ቡድን ለጊዜው በእኛ ይሁንታ በተሸሸገባቸው አካባቢዎች በተለይ ጎንደር ከተማ ፣ ከባህርዳር -ጎንደር- ደብረታቦር መስመር፣ከድብረታቦር-ወልድያ መስመር፣ከጎንደር -መተማ መስመር፣ከጎንደር-ደባርቅ መስመሮች በከባድ መሳሪያ የታገዘ ዘረፋ እየፈፀመ እንደሆነ ማረጋገጥ ችለናል።

ለዚህም ማሳያ የሚሆነው፦
በቅርቡ ወቅን ላይ በተሞከረ ዘረፉ ቆስሎ የተያዘ የቡድኑ አካል የመንግስት ሚሊሻ እንደነበረ እና ተልዕኮ ተሰጥቶት እንደሚሰራ መናገሩ፤ ከአሁን በፊት በቪዲኦ (Video) እንዳሳየነው ሲዘርፉ የተገኙት ሌቦች መንግስት የላከቸው እንደሆኑ መመስከራቸው፤ በኮማንድ ፖስት በሚመራው የጎንደር ከተማ ውስጥ ከመንግስት ተታጣቂወች ውጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በማይቻልበት ሁኔታ የአድማ ብተና የሚሊሻ እና የመከላከያ ሐይል ካንፕ ዙሪያውን በታጠረ ከተማ ውስጥ መትረጊስ እና ሌሎች የቡድን መሳሪያዎችን የታጠቀ ዘራፊ ሐይል የግቢ በርን በሐይል ሰበሮ በመግባት በአንድ ቀን ብቻ ሰባት ሰዎችን ማገቱ፤ እራሱ የአካባቢው ማህበረሰብ እንዳረጋገጠው ተደራጅተው የሚዘርፉ አካሎች እና የመንግስት ሐይሎች በቅርብ እርቀት እየተያዩ ምንም አይነት እርምጃ የመውሰድ ፍላጎት አለማሳየታቸው፤ ማንም ግለሰብ በቅርብ ካለው የመንግስት አመራር ማረጋገጥ እንደሚችለው ሰሞኑን በነበሩ የካድሪ ውይይቶች ላይ "ፋኖ በቅርቡ ዘረፋ ይጀምራል ዘረፋው እንዲቆም ከፈለጋችሁ ከእኛ ጋር እበሩ የሚል ጫና ማህበረሰቡ ላይ ማሳደር አለብን" የሚል አጀንዳ ለውይይት ማቅረባቸው፤ ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች መሰል ዝርፊያዎች አለመኖራቸው፤ ሁሉም ዝርፊያወች ከመንግስት ሐይል ካፕ ቅርብ እርቀት መፈፀማቸው፤ ስለ ጉዳዩ ሊያመለከቱ ለሔዱ አካላት እኛን ከደገፋችሁ ዝርፊያውን እናስቁምላችኋለን ካልሆነ ግን ፋኖ ያድናችሁ የሚል መልስ መስጠታቸው፣ ወዘተ. ዘረፋው መንግስት መር መሆኑን እና ዘራፊዎችን መንግስት እንደሚያውቃቸው ማሳያዎች ናቸው።

ህዝብ እንዲገነዘበው እና ለወደፊቱም እንዲያጤነው የምንፈልገው ጉዳይ በኮማንድ ፖስት በሚመራ ከተማ ውስጥ፣የፋኖ ሐይሎች በከተማው በሌሉበት ሁኔታ፣ያለ ምንም ውጊያ መትረጊስን ጨምሮ ሌሎቸ የቡድን መሳሪያዎችን ተጠቅሞ የሚዘርፍ ሐይል እራሱ የመንግስት ታጣቂ ወይም መንግስት ያቋቋመው ሐይል እነደሆነ ነው።

ዘረፋው በመንግስት ታጣቂዎች እና በከተማው ስቪል አስተዳደሮች በጥምረት የሚፈፀም ሲሆን በዋናነት ሁለት አብይት አላማዎች እንዳለው ከውስጥ መረጃዎች ለማረጋገጥ ችለናል። አንደኛው አላማቸው ዘረፋ የሚፈፅመው ፋኖ ነው በማለት ፋኖን ከማህበረሰቡ ጋር ማቃቃር ሲሆን ሁለተኛው የመንግስት ታጣቂዎች በደንብ እንዲያገለግሉ ማማለያ እንደሆነ ማረጋገጥ ችለናል።

በመሆኑም የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የሚከተለውን መልዕክት እና ማስጠንቀቂያ ለሚመለከታቸው አካላት ያስተላልፋል፦

1: የተከበርከው የጎንደር አማራ እኛ የአማራ ፋኖዎች የተደላደለ ኑሯችን ትተን በዱር በገደል እንደንኖር ያስገደደን የአማራ ህዝብ ስቃይ እና እንግልት ደካማ ጎናችን በመሆኑ እና ይህ ግፍና መከራ ያጎበጠው ህዝብ ሳይንገላታ ስርዓቱን የምናፈርስበትን ዘዴ ከከተማ ውጭ በሚደረግ ትግለ ነው ብለን ስለምናምን እንጅ የዞን ከተሞችን አይደለም የክልል ከተሞች ላይ ገብተን መዋጋት አቅሙ እንደማይገደን ከእናንተ የተደበቀ ሐቅ አይደለም። እኛ ለአጭር ሰዓት ለተልዕኮ ከተማ በምንገባበት ወቅት እንኳን በሰበባስባቡ የሚገደለውን ንፁሐን እናንተ ታውቁታላችሁ። በዚህም ምክንያት የቤት ስራችን እስክንጨርስ ድረስ ዱሩ ቤቴ ብለን ከወጣን ሰነባብተናል። ሐቁ ይህ ሆኖ እያለ በግድ ካልደገፋችሁኝ በሚል የበቀል ስሜት በመነሳሳት መንግስት ያሰማራው ዘራፊ ቡድን በፋኖ ስም ተደራጅቶ እንዲዘርፋችሁ መደረጉ ስንስማ በህዝባችን ጊዜና ዘመን የመይሽረው መከራ የቆሰለው ልባችን ክፉኛ መርቅዟል።

ይሁን እንጅ ሁላችንም በየ እድሜ ደረጃችን ልጅነታችን፣ጉልምስናችን እና የመጦሪያ ዘመናችን እያባከን በዱር በገደል የምንሰቃየው ይህን በበቀል ተወልዶ በበቀል ያደገ ስርዓት ግብዓተ መሬቱን ለመፈፀም ነውና እንባችሁ የሚታበስበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም። በመሆኑም ይህ እየተደረገባችሁ ያለው ዘረፋም ሆነ የቆየው ስርዓታዊ በደል ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት የሚያገኘው ከስርዓቱ መቀበር ጋር በመሆኑ ለምናደርገው ዘርፈ ብዙ የሆነ የህልውና ተጋድሎም እንደተለመደው ከጎናችን እንድትሆኑ የዘወትር መልዕክታችን ነው።

2: በጥቅም ተሸውዳችሁም ሆነ ግላዊ ፍላጎታችሁ አስገድዷችሁ የምትዘርፉ የመንግስት ታጣቂዎች ከህዝብ ሰርቆ ማምለጥ እንመደማይቻል ሽንት ቤት ሲሔዱ ሳይቀር ከምትጠብቋቸው የቅርብ አለቆቻችሁ በላይ ሊያስተምራችሁ የሚችል ምሳሌ የለማ እና ብትማሩ መልካም ነበር። የምትጠብቁት አመራር በሙሉ ከአየር መንገድ ወደ ቢሮ ለመግባት በብረት ለበስ ታንክ ተሸከርካሪ የሚጓዘው እና በእናንተ እና በሌሎች ኋይሎች የሚጠበቀው የአባቱን ገዳይ ፈርቶ ሳይሆን ትናት እንደ እናንተ የዘረፈው እና የበደለው ህዝብ እንደሚበቀለው ስለሚያውቅ ነው። ይህንን እውነት ከአናንተ ውጭ የቀረበ የሚያረጋግጠው የለም። ይህ ወቅት ለእናንተ የንስሐ ጊዜ ነው።አውቃችሁም ሆነ ሳታውቁ የበደላችሁትን የአማራ ህዝብ የምትክሱበት የመጨረሻው ሰዓት ላይ ናችሁ። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በዚህ እኩይ አላማ የምትቀጥሉ ከሆነ ግን የእናንተም እጣ ፋንታ ከአለቆቻችሁ የከፋ እንደሚሆን ማስታወስ እንወዳለን።
6.4K views12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ