Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawigetmoch — መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawigetmoch — መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
የሰርጥ አድራሻ: @menfesawigetmoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.32K

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-09 09:13:41
1.2K views06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-26 06:12:18 የክብርህ ቀዳሽ
የመንግስትህ ወራሽ
እንድሆን እርዳኝ
1.5K views03:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-17 22:45:08
ጌታ ሆይ..
የተዘጋው ልቤን ፥ክፈተው በመስቀል፤
የሚያስክደኝ ጠላት፥ ከስሩ እንዲቀል።
የጥርጥር ነገር፥ በኔ እንዳይበረታ፤
ከእውነት እንዳልሽሽ፥ ልቦናዬን ፍታ።
ካንተ ተልይቼ ፥መቼም አልሆን ደህና፤
እውነቴም ህይወቴም፥ መንገዴ ነህና።
++++++
ታዜና
      #መንፈሳዊ_ግጥሞች
      t.me/Menfesawigetmoch
1.9K viewsedited  19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-06 05:05:53
"ምን እላለሁ፤
ምን እናገራለሁ፤
የጌታዬ ልደቱ ድንቅ ነው።
የአማኑኤል ልደቱ ድንቅ ነው።"*

አለምን በቃሉ፥ የፈጠረ ጌታ፥
ሁላችንን ሊያድን ሊወስድ፥ የኛን ተርታ።
ያለም ጌታ ሆኖ፥ ያየነው በበረት፤
ምን አይነት ፍቅር ነው፥ ምን አይነት ደግነት።

በናቱ እቅፍ ሆኖ፥ በሰማያት አለ፤
በሰማያት ሆኖ፥ በናቱ እቅፍ አለ።
ከኪሩቤል ጀርባ፥ ሳይወርድ ከዙፋኑ፤
ይገርማል ይደንቃል፥ በኛ መመስገኑ።

ቅድመ አለም ያለ እናት ተወልዶ ከአባቱ
ድህረ አለም ያላአባት  ወለደች እናቱ
ይህን ድንቅ ጥበብ፥ ፍጥረቱ ተማክሮ፤
ድንቅ ይባላል እንጂ፥ ማን ያውቃል መርምሮ።

ነብያት የናፈቁት፥ ትንቢታቸው መጣ ፤
ከድንግል ማህፀን፥ ያለድካም ወጣ፤
መለኮት ሳይከፈል፥ ወደ አለም መጣ፤
የጽድቃችን ጸሀይ፥ ከሰማያት ወጣ።
++++++
እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ

*("ምን እላለሁ ምን እናገራለሁ..."
ሐይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ)
ታዜና
      #መንፈሳዊ_ግጥሞች
      t.me/Menfesawigetmoch
2.0K viewsedited  02:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-29 04:42:15 ታላቁን ነጎድጓድ፥ ታላቁን ማእበል፤
እንዴት ያላንተ እኔ፥ ችዬ አለፍኩት ልበል።
የልቤን ስንፍና፥ ሀይማኖት ደግፎ፤
ዛሬ ማለት አልኩኝ፥ ትናንትና ታልፎ።

በርሀብ በጥጋብ፥ ሁሉን ለሚለኩ፤
በጽድቅህ ይሰፈር፥ የዘመኔ ልኩ።
የዛለው ጉልበቴን፥ አበርታልኝ አንተ፤
ገደል እንዳይጥለኝ፥ ሆዴ እየጎተተ።

ወንድምህ የት አለ፥ ወዴት ነው ለሚለኝ፤
ይቅርታ መጠየቅ ፥ሽንፈት ከመሰለኝ።
ልቤ ቂም አርግዞ፥ ሁሉንም ከጠላ፤
እፉኝት ሆኛለሁ፥ እናቱን የበላ።

ትዕቢት እንዳይሞላኝ፥ በራስ በመመካት፤
ለስጋዬ ተግሳጽ፥ ፈተናን አትንሳት።
ነፍሴ እንዳትደክም፥ ስጋ ተንተርሳ፤
በመንግስትህ ጊዜ፥ ልጅህን አትርሳ።
++++++
ታዜና
      #መንፈሳዊ_ግጥሞች
      t.me/Menfesawigetmoch
2.0K viewsedited  01:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-25 13:53:52 ++ምናለ ብታስተምረኝ++
በክብር በሞገስ በመወደስ ፈንታ
መቀመጥ እንድችል ከመዋረድ ተርታ
ስድብን እየሰማሁ ያለ አንዳች ሁካታ
ለመቆም እንድችል ልቤ ሳይረታ
ምናል ብታስተምረኝ ብታስችለኝ ጌታ!?
ለእኔም አስተምረኝ ባላጠፉት ጥፋት
በጸጋ መቀበል የአይሁድን ትፋት
እንዴት እንደሚቻል ሳያጉረመርሙ
ንገረኝ ጌታዬ ይረዳኝ ትርጉሙ!
የመናቅን ጥበብ የውርደትን ዘዴ
እባክህ አስረዳኝ አስተምረኝ አንዴ
ብዔል ዜቡል ተብለህ ያልተበሳጨኸው
የኃጢአተኞች ወዳጅ መባል ያልጠላኸው
ጋኔን ይዞታልን የሰማህ በጸጋ
ለእኔም አስተምረኝ በቂም አልወጋ!
አልወጋ እባክህ በመራርነት ጦር
በቁጣ ጥላቻ ነፍሴ አትሰበር
እንዴት ነበር ያኔ የይሁዳን እግር

ዝቅ ብለህ ያጠብኸው ስታውቅ ሁሉን ነገር?
ለእኔም አስተምረኝ ብዙ ሳልናገር!
በችንካር ተጣብቀህ ከመስቀሉ ጋራ
የደምህ ነጠብጣብ ገና ሳያባራ
አያውቁትምና የሚያደርጉትን
ይቅርታን የለመንህ ላጠጡህ ሐሞትን
ምናል ብታስተምረኝ እንዲህ ዓይነት ሕይወትን?
አሁን ምን ቸገረህ ብትሰጠኝ ለአንድ አፍታ
የትሕትናን ቀሚስ የትዕግሥትን ኩታ
እያየህም አይደል ነፍሴ እንዲህ ተራቁታ?
የመሰደብን ዘውድ የመናቅን ካባ
ምናለ ብትኖር ይ’ች ልቤ ደርባ!?
ትዕቢት ለተሞላው ለአትንኩኝ ባይ ልቤ
ለክብሩ ለሚኖር ለኮርማው ሃሳቤ
ምናለ ብትቀባው የትሕትናን ሽቶ
እንደዚህ ከሚኖር ሸትቶ ተበላሽቶ!?
ኸረ እኔ አልቻልኩም አቅቶኛል በጣም
ስድብን መቀበል ሐሜትን ማጣጣም

ስተርከው እንጂ ስኖረው አቃተኝ
ይህን መራር ኑሮ አንተው ይዘህ ጋተኝ!
እንኳን እንደ አንተ ዝም ልል ሲረግጡኝ
ቁጣዬ ነደደ ስለገላመጡኝ
ያንን ሁሉ ታሪክ ያን ሁሉ ጥቅስ ረሳሁ
በቂምና በቀል በጥላቻ ከሳሁ
እንደ አራስ ነብር ለክብሬ ተነሣሁ!
ዲ/ን ሄኖክ ሃይሌ /
2.0K views10:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-21 09:40:38
ቅዱስ ሚካኤል፣ ክንፉን ዘርግቶ፤
ያሻግረናል፣ በፀዳል መርቶ፡፡
ህዳር ሚካኤል፣ ህዳር ሲታጠን፤
ፍቅርና ሰላም፣ ጤናውን ይስጠን፡፡
++++++
ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች
t.me/Menfesawigetmoch
2.6K viewsedited  06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-14 23:18:17
አለምን የሰራ ሲሆን፥
ከእኛ እንዳንዱ ቢሆን።
እንደ በደለኛ ቆጥረነው፥
በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀልነው።
++++++
ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች
t.me/Menfesawigetmoch
2.5K views20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-28 10:41:09 በአማኑኤል ስምህ
በፈሰሰ ደምህ
በተወጋ ጎንህ
በሰጠኸኝ ነፍስህ
አትተወኝ እልሀለሁ
ነፍሴን ማራት እልሀለሁ

እረኛዬ ሆነህ፥ ያሳጣኸን የለም፤
የችንካርህ ጽሁፍ፥ ፍቅር ነው ዘላለም።
በደሌን ታግሰህ፥ አይዞህ ትለኛለህ፤
በለመለመ መስክ፥ ታሰማራኛለህ።
++++++
ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች
t.me/Menfesawigetmoch
2.2K viewsedited  07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-12 11:38:21
ማርያምን ተረከ…

ጽጋን የተሞላች የጌታዬ እናቱ
የአዳም ተስፋ ናት ኪዳን የምህረቱ፡፡
በደም የነጠቀ ከዘላለም ሲቃ
ማረፊያ ነው ልጇ የሰላም አለቃ፡፡

እርሻችን አሸተ ደመናው ተከፍቶ
እንጀራን ጠገብን ጎተራችን ሞልቶ፡፡
የዘራነው ሁሉ በወቅቱ ደረሰ
የአይኖቻችን እንባ በልጇ ታበሰ፡፡

የወይኑን እንስራ ይሞላል ምልጃዋ
በታሪክ መካከል ያበራል ስራዋ፡፡

ያዘነ ተጽናና ደካማው በረታ
ታላቅ ለታናሹ ለቀቀለት ቦታ፡፡
ትውልድ ተረጋጋ ዘመን ተባረከ
ብራና መጻፉ ማርያምን ተረከ፡፡
++++++
ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች
t.me/Menfesawigetmoch
2.8K viewsedited  08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ