ማርያምን ተረከ… ጽጋን የተሞላች የጌታዬ እናቱ የአዳም ተስፋ ናት ኪዳን የምህረቱ፡፡ በደም የነጠ | መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ማርያምን ተረከ…
ጽጋን የተሞላች የጌታዬ እናቱ
የአዳም ተስፋ ናት ኪዳን የምህረቱ፡፡
በደም የነጠቀ ከዘላለም ሲቃ
ማረፊያ ነው ልጇ የሰላም አለቃ፡፡
፡
እርሻችን አሸተ ደመናው ተከፍቶ
እንጀራን ጠገብን ጎተራችን ሞልቶ፡፡
የዘራነው ሁሉ በወቅቱ ደረሰ
የአይኖቻችን እንባ በልጇ ታበሰ፡፡
፡
የወይኑን እንስራ ይሞላል ምልጃዋ
በታሪክ መካከል ያበራል ስራዋ፡፡
፡
ያዘነ ተጽናና ደካማው በረታ
ታላቅ ለታናሹ ለቀቀለት ቦታ፡፡
ትውልድ ተረጋጋ ዘመን ተባረከ
ብራና መጻፉ ማርያምን ተረከ፡፡
++++++
ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች
t.me/Menfesawigetmoch