Get Mystery Box with random crypto!

ዲያቆን ዳንኤል ወንድሙ ቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ menamaedot — ዲያቆን ዳንኤል ወንድሙ ቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ menamaedot — ዲያቆን ዳንኤል ወንድሙ ቻ
የሰርጥ አድራሻ: @menamaedot
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.20K
የሰርጥ መግለጫ

ይህን መጸሐፍ ብላ ሕዝ 3 ÷ 1
ይህ የቴሌግራም ቻናል የኔ የዲ/ን ዳንኤል ወንድሙ ነው
#በዚህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮቶች ይለቀቃሉ ሁላችሁም ስለ ቀናች ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ለማወቅ ቤተሰብ ይሁኑ
ስለ ፕሮግራሙ አስተያየት ካሎት በውስጥ መስመር ያናግሩን

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-04-19 09:54:30 #መልክአ_ሕማማት፤ (የ፯ቱ ጊዜያት ጸሎት)
*መልክአ ሕማማት ማለት ስለ ጌታችን መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሕማም፥ መከራ፥ ስቃይ፥ የሚናገር መጽሐፍ ሲሆን፤ ደራሲው ታላቁ ሊቅና የደብረ ባሕርይ ጋሥጫ መምህር #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_ ነው፡፡
*መልክአ ሕማማት በባለ 3ት መስመር አርኬ የተደረሰ ግጥማዊ ድርሰት ሲሆን፤ የተደረሰውም በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት አንጻር በመሆኑ ‹‹#ጸሎት_ዘሰባዐቱ_ጊዜያት›› በሚል መጠሪያም ይጠራል፡፡ የእያንዳንዱ ጊዜ ድርሰትም በዋነኛነት 3ት ክፍሎችን የያዘ ነው፤ እነርሱም፤
1ኛ) ስብሐተ እግዝእትነ ማርያም /የእመቤታችን ምስጋና/
2ኛ) ስበሐተ ኢየሱስ ክርስቶስ /የኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና/
3ኛ) ስብሐተ ሥሉስ ቅዱስ /የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና/
**በ7ቱ ጊዜያት ጸሎት ማድረስ እንደሚገባን ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 118 ላይ ‹‹ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ ይላል››፤ አባቶቻችን ሐዋርያትም ይህንኑ ደንግገዋል፡፡ /ዲድስቅልያ 37፣ ቀሌምንጦስ 1ና 7፣ አቡሊዲስ 25ኛና 27ኛ፣ ባስልዮስ 28ኛ አንቀጽ፣ ፍትሐ ነገሥት ገጽ 21/፡፡
፠ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ መልክአ ሕማማትን ሲደርስም በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት የተፈጸሙትን ድጊቶች ከ3ቱ የየጊዜያቱ የድርሰቱ ክፍሎች ምስጋና (የማርያም፣ የጌታ፣ የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና) ጋር እያመሠጠረና እያራቀቀ፥ እያስዋበና ምሥጢር እያመጣ፤ እንደ ወርቅ እያንከባለለ፥ እንደ ሸማ እየጠቀለለ፥ በግጥም እያስጌጠ፥ በቃላት እየሰደረ፥ በዜማ እያሸበረቀ፥ መንፈስን እየመሰጠ፤ ነው የደረሰው፡፡
#የ7ቱ_የጸሎት_ጊዜያት_የሚባሉትም፤
፠1ኛ) መንፈቀ ሌሊት(ሌሊት 6 ሰዐት)፤ ጌታችን የተወለደበት፥ የተጠመቀበት፥ የተነሣበትና ዳግመኛ የሚመጣበት ፥ … ሰዐት ነው፡፡
፠2ኛ) ነግህ (ማለዳ፥ ጧት)፤ ጨለማን አርቆ ብርሃንን የሚያመጣበት፥ አባታችን ቅዱስ አዳም የተፈጠረበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጲላጦስ አደባባይ ፊት ቁሞ የተመረመረበት፥ …. ሰዐት ነው፡፡
፠3ኛ) ሠለስት (ጠዋት ሦስት ሰዐት)፤ እናታችን ሔዋን የተፈጠረችበት፥ ነቢዩ ዳንኤል ጸሎት ያደረሰበት፥ እመቤታችን ከቅዱስ ገብርኤል ብሥራትን ሰምታ የጸነሰችበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በጲላጦስ አደባባይ የተገረፈበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡
፠4ኛ) ቀትር (6 ሰዐት)፤ አጋንንት የሚሰለጥኑበት ሰዐት ስለሆነ እንዳይሰለጥኑብን፥ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ የሳተበት ስለሆነ እንዳንስት እንጸልያለን፡፡ በተጨማሪም ነቢዩ ሄኖክ ቤተ መቅደስን ያጠነበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በመስቀል ላይ የተሰቀለበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡
፠5ኛ) ተስዓት (ዘጠኝ ሰዐት)፤ ቅዱስ ጴጥሮስና ዮሐንስ ለጸሎት ወደ ቤተ መቅደስ የወጡበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው የለየበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡
፠6ኛ) ሠርክ (ዐሥራ አንድ ሰዐት)፤ ነቢዩ ኤልያስ መሥዋዕት የሰዋበት፥ ዕዝራ ጸሎትን ያቀረበበት፥ ሕዝቅያስ ጸልዮ ፀሐይን ወደ ዐሥር ደረጃዎች የመለሰበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደ በፈቃዱ ወደ አዲስ መቃብር የወረደበት፥ …… ሰዐት ነው፡፡
፠7ኛ) ንዋም (የመኝታ ሰዐት)፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጌቴሴማኒ የጸሎትን ሥርዐት ያስተማረበት ፥ እንዲሁም ሌሊቱን በመላእክት ጥበቃ ከርኵሳን አጋንንት እንዲጠብቀን የምንጸለይበት …… ሰዐት ነው፡፡

ይህ ታላቅ ጸሎት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስር ባሉ በሁሉም ገዳማትና አድባራት በሰሙነ ሕማማት የሚደርስ ሲሆን፤ በአንዳንድ ትላልቅ ገዳማት (እንደ ዋልድባ፣ ማኅበረ ሥላሴ፣ ደብረ ባሕርይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ወደብረ ጎል አቡነ በጸሎተ ሚካኤል) ያሉ መነኰሳትና መናንያን ግን ከዓመት እስከ ዓመት ጸሎቱን በዜማ /በንባብ/ ያደርሱታል፡፡
1.3K views06:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 01:50:54 †​​ በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚገኙ እንግዳ ቃላትና ትርጉማቸው
† † † † † † † † †
በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡

† #ኪርያላይሶን፦
ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን»ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል አለበት፡፡ ትርጉሙ «አቤቱ ማረን»ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ«ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡

† #ናይናን፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡

† #እብኖዲ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው

† #ታኦስ፦
የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡

† #ማስያስ፦
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው

† #ትስቡጣ፦
«ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው

† #አምነስቲቲ_ሙኪርያቱ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡

† #አምንስቲቲ_ሙዓግያ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ -ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡

† #አምንስቲቲ_ሙዳሱጣ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡

"ጸልዩ ከመ እግዚእ አምላክነ ይምሐረነ ወይሣሃለነ ወይትወከፍ ስእለተነ ወያፈጽመነ ዛተ ሰሙነ በደኅና ወበሰላም ወያርእየነ ብርሃነ ትንሣኤሁ በፍስሐ ወበሐሴት ወይስረይ ለነ ኃጣዉኢነ

[ጌታችን አምላካችን ራርቶ ይቅር ይለን ዘንድ ልመናችንንም ተቀብሎ ይችን ሳምንት በደኅናና በሰላም ያስፈጽመን ዘንድ የትንሣኤውንም ብርሃን በፍጹም ደስታ ያሳየን ዘንድ ኃጢአታችንንም ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ]"

✞ በእንተ ጽንዐ ዛቲ(ግብረ ሕማማት ገፅ ፻፳፪)
-----------------------------------
ኪርያላይሶን እብኖዲ ናይን
ኪርያላይሶን ታኦስ ናይን
ኪርያላይሶን ማስያስ ናይን
ኪርያላይሶን ኢየሱስ ናይን
ኪርያላይሶን ክርስቶስ ናይን
ኪርያላይሶን አማኑኤል ናይን
ኪርያላይሶን ትስቡጣ ናይን
[በቀኝና በግራ በመቀባበል በል፡፡]

"እንበለ ደዌ ወሕማም፣
እንበለ ጻማ ወድካም፣
አመ ከመ ዮም
ያብጽሐነ ፤ ያብጻሕክሙ፣
እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም፡፡"አሜን
1.0K views22:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-13 10:25:52 የማመስገን ጊዜ ይህ የተመረጠ የዕጣን ጊዜም
ይህ ነው ሰው ወዳጅ መድሐኒታችን ክርስቶስን
ማመስገኛ ጊዜ
፠ ፦ ማርያም ዕጣን ናት ዕጣን እርሱ ነው
በማህፀንዋ ያደረው ከተመረጠ ዕጣን ሁሉ
የሚሸት ነውና የወለደችው መጥቶ አዳነን
፠ ፦ ኢየሱስ ክርስቶስ መዓዛ ያለው ሽቱ ነው ኑ
እንስገድለት ትዛዞቹንም እንጠብቅ ኃጢአታችንን
ያስተሰርይልን ዘንድ
፠ ፦ ለሚካኤል ምሕረት ተሰጠው ለገብርኤል
ማብሰር ለድንግል ማርያም ሰማያዊ ሀብት
፠ ፦ ለዳዊት ልቡና ለሰሎሞንም ጥበብ
ለሳሙኤልም ነገሥታቱን የቀባ እርሱ ነውና የሽቱ
ቀንድ ተሰጠው
፠ ፦ ለአባታችን ለጴጥሮስ መክፈቻ ለዮሐንስም
ድንግልና ለአባታችን ለጳውሎስም
የቤተክርስቲያን ብርሃኗ እርሱ ነውና መልክት
ተሰጠው
፠ ፦ መዓዛ ያላት ሽቱ ማርያም ናት በማኅፀኗ
ያለው ከዕጣን ሁሉ የሚበልጥ ነው መጥቶ
ከእርሷ ሰው ሆነ
፠ ፦ ንጽሕት ድንግል ማርያምን አብ ወደዳት
ለተወደደ ልጁም ማደሪያ ልትሆን አስጌጻት
፠ ፦ ለሙሴ ህግ ለአሮን ክህነት ተሰጠው
ለካህኑ ለዘካርያስ የተመረጠ ዕጣን ተሰጠው
፠ ፦ የምስክር ድንኯን አደረጎት ጌታ እንደተናገረ
ካህኑ አሮንም በመካከልዋ የተመረጠ ዕጣን
ያሳርጋል
፠ ፦ ሱራፌል ይሰግዱለታል ኪሩቤልም
ያመሰግኑታል
፠ ፦ እግዚአብሔር በአእላፍ መላእክት ዘንድ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ነው እያሉ ይጮሃሉ
በአለቆች ዘንድ ክቡር ነው
፠ ፦ መድሐኒታችን ሆይ ዕጣን አንተ ነህ
መጥተህ አድነኸናልና ይቅር በለን
738 views07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ