2022-07-16 18:09:44
ሰበር መረጃ
--------
መጅሊሱን የመዝረፍና የመቀራመት ዘመቻ ትጧጡፎ መቀጠሉ ታወቀ
----RN05----
የነሙፍቲ ሃጅ ዑመር ዕድሪስ ቡድን በዛሬዉ እለት በአሰቸኳይ ከኢትዪ ንግድ ባንክ 1,400,000 (አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሺህ) ብር ወጪ አስደርገው ለግል ጥቅማቸው መከፋፈላቸውን ከታማኝ የውስጥ ምንጮች የደረሱን መረጃዎች አረጋግጠዋል።
.
ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ በመጅሊሱ ዙሪያ ለተፈጠረው ውዝግብ አማራጭ መፍትሄ ያመጣል በሚል ግምት የሚያዚያ 23/2011ዱ የሸራተኑ ጉባኤ እንደ አዲስ ሃምሌ 10/2014 እንዲካሄድ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ተከትሎ በጉባኤው ላይ ጥርጣሬ አለን ስልጣናችንን አስረክበን ለመጭው ተመራጭ ቡድን እናስረክባለን በሚል ስጋት የእነ ሙፍቲ ሃጅ ዑመር ቡድን የህዝበ ሙስሊሙን ሃብት በሚያሳዝንና በሚያስገርም ሁኔታ በዛሬው ዕለት በአስቸኳይ ትዕዛዝ ወጭ አድርገው ሲመዘብሩና ሲከፋፈሉ መዋላቸውን የደረሰን ታማኝ መረጃ አረጋግጧል።
.
እነ ሙፍቲ ሃጅ ዑመርና ዱድናቸው ገንዘቡን ለመቀራመቱ በምክንያትነት የተጠቀሙት እኛ ሃጅ ስላልሄድን ሌሎች ባልደረቦቻችን ሳውዲ ሄደው ያገኙት አበል በቤተሰቦቻችን ቁጥር ልክ ሊከፈለን ይገባል በሚል ሲሆን ድርሻቸውም እንደሚከተለው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
.
1ኛ. ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ዕድሪስ 6300 ዶላር ወይም 350 ሺህ ብር
2ኛ. ሸህ ቃሲም ታጁዲን 6300 ዶላር ወይም 350 ሺህ ብር
3ኛ. ሸህ አህመድ አወሎ 6300 ዶላር ወይም 350 ሺህ ብር
4ኛ. ሸህ አብዱልሀሚድ (በዶ/ር ጀይላን ቦታ ሰሞኑን የተተካና አንድ ወር ያልሰራ) 6300ዶላር ወይም 350 ሺህ ብር
በድምሩ በ4ቱ ግለሰቦች 1,400,000 (አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሺህ) በዛሬዉ እለት በአሰቸኳይ ከኢትዪ ንግድ ባንክ ወጪ ተደርጎ ተከፍሏቸዋል።
.
ወደ ሃጅ ያቀኑት እያንዳዱ ኡለማም አምስት አምስት የቤተሰቡ አባል በዚህ ልክ አበል ተከፍሏቸው ወደ ሃጅ መላካቸው ይታወቃል።
.
መጅሊሱ በርካታ ሺህ ቁጥር ያላቸውን ሁጃጆች የዶላር እጥረት ገጥሞኛል በሚል ብራቸውን ከተቀበለ በኋላ ሃጅ እንዳይሄዱ ማድረጉ ይታወሳል።
.
በዚሁ ምክንያት ሃጅ ማድረግ ያልቻሉት ሁጃጆችም ገንዘባቸውን ለማስመለስ በመጅሊሱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተቃውሞ ማሰማታቸውና ኮሚቴ አዋቅረው ገንዘባቸውን የማስመለስ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ይታወቃል።
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
60 views15:09