Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethmedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.07K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 69

2022-07-18 06:03:11 የስልጣን ባለቤትነቱን ጉዳይ ለሕዝባችን መስጠት ለነገ የሚባል አይደለም።



እንደዜጋ በዚህ በምንኖርበት ሀገር ላይ እንደሌሎች ወንድም ሕዝቦች የተቋም ግንባታና ማህበረሰብ አቀፍ የእንቅስቃሴ መብቶቻችን እንዲጠበቅ እንፈልጋለን። ለዚህ መሳካት ደግሞ ሕግና ደንብ፣ መመሪያና ሞራል መፍቻ ቁልፎች ይሆናሉ።

በመሆኑም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በሀገሪቱ ሕገ መንግስትና በተቋሙ ደንብና መመሪያ መሰረት ሕዝባችን ፍላጎቱ ይሳካ ዘንድ የስልጣን ባለቤትነቱን ጉዳይ ለሕዝባችን መስጠት ለነገ የሚባል አይደለም።

በሀገሪቱ ከግማሽ ቁጥር በላይን የሚሸፍነው ሕዝባችን ሠላሙ ሳይረጋገጥ፣ ተቋሙ ሳይገነባ፣ ሕዝባዊ የስልጣን ባለቤትነቱን ሳያረጋግጥ እንዴትስ ስለሌሌች ልማትና ግንባታ እንዲሁም አብሮ የመኖር ጥምረት ማሰላሰል ይቻላል?


ከሀገሪቱ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ሕዝባችንን ችግሮች መፍታት የሀገር ሠላምን ማስጠበቅ፣ ልማትን ማፋጠን፣ ዲሞክራሲን የማጎልበት ዋነኛ ካስማ በመሆኑ የመጅሊስ ጉዳይ አበይት አጀንዳና ሕዝባዊ ውክልና የሚያገኝበት ጊዜው አሁን ነው! የሐምሌ 11/2014 የሸራተን ጉባዔ!

ሙጂብ አሚኖ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
29 views03:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 06:00:43 "አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳወሱት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹በሶስት መስጊዶች ካልሆነ በቀር (ሌሎችን መስጊዶች) ለመጎብኘት ለጉዞ መነሳት አያስፈልግም፡፡ 1) ‹‹አል-መስጂደል ሐራም›› (መካ) 2) ‹‹መስጂደር-ረሱል›› (በመዲና ያለው የነቢዩ መስጊድ) 3) ‹‹መስጂደል አቅሷ›› (የእየሩሳሌሙ አቅሷ መስጊድ)፡፡
(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።


https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
29 views03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 22:19:03 ጊዜያቸው ደርሷል!

እንደ ሰጎን አሸዋ ውስጥ ቀብረው ሲያደቡ ለነበሩ ኃይሎች ጊዜያቸው ደርሷል!


እስልምና በዓለም ላይ ከሚገኙ መርሆዎች ሁሉ በላቀ ሁኔታ ህዝብን በአንድ ጥላስር ማሰባሰብ የሚችል ፅንስ ሀሳብ ነዉ። በዚህ መርህ የሚገኘው ሰላም የፍፁማዊነትን ኒሻን የሚጎናፀፍ ነው። የመንፈሳዊ ደህንነትና የእምነትም ነፃነት ነው።

ይህን ማሰብ ግን ከትናንት የቆሸሸና የጨቀየ አሰራር ሳይወጣ የሀይማኖት ተቋሞችን ከአደፈ አሰራር ያነፃል ከጎበጠበት ያቃናል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ያለ አባት ያለ ሰብሳቢ ለብዙ አመታት ያሁሉ በደልና ግፍ ሲያስተናግዱ ቆይተው የ ሚያዚያ 20/1966 ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ መካሄድ እነርሱን ወክሎ የሚናገር የሀጅና ኡምራ ጉዟቸውን የሚያቀላጥፍ መስጂዶችንና አውቃፍን የሚያስተዳድርና የሚገነባ ኢስላማዊ እውቀትን የሚያካሂድ የሚመራ ተቋም እንዲኖራቸው በመጠየቃቸው የኢትዮጺያ እ/ጉ/ጠ/ ም/ቤት በብሄራዊ ደረጃ ተቋቋመ።

ይህ በእነ ሀጅ መሀመድ ሳኒ ሀቢብ መሪነት የተቋቋመ መጅሊስ ለዘመናት የተፈፀመበትን በደል አይቶ አላህ የሰጠው አባት አድርጎ በመውሰድም እስከ እለተሞታቸው ድረስ የሙስሊም የነበረው ተቋም መፍረክረክና ቡድን በቡድን መከፋፈል ጀመረ።

ሚያዚያ11/1981 ታላቁን አባት ሀጅ ሳኒ ሀቢብን ( አሏህ ይዘንላቸውና) ቀብሮ የመጣው የኢትዮጵያ ሙስሊም እነሆ እስከ ዛሬ እንድ ሰብሳቢ አባትና የኔነው ብሎ የሚመካበት ተቋም አጥቶ እርስ በእርስ እያባሉ የግል ጥቅማቸውን በሚያግበሰብሱ መጅሊስ ተብዬዎች እጅ ወድቋል።

ይሄ መጅሊስ ባለፉት 3 አመታት መሪዎቹ የሙስሊም ጠላት ከሆኑ ተቋሞች ጋር አብሯል፤ የተለያዩ ኀይሎችን በመያዝ ሙስሊሞች እምነታቸውን ተንተርሶ ጥቃት እንዲፈፀምባቸው አድርጓል ፤ ከግለሰቦች ከፍተኛ ጥረትና ልፋት የተመሰረቱ ኢስላማዊ ተቋማት እንዲፈርሱ አድርጓል፤ሙስሊሞች በግልፅም ሆነ በስውር በመካከላቸው መከፋፈል እንዲኖር ተሰርቷል፣....በርካታ ዘግናኝ ወንጀሎች የታጨቀበት ተቋም!•••

መጅሊስ በዘመድ በጓደኝነትና በጥቅማ ጥቅም በተጓደኑ ሰዎች ከፍተኛ ዘረፋ ሲፈፀሙ በነበሩ ሰዎች የተሞላ ነበር።በተለይም ከ 2004 ወዲህ ህዝበ ሙስሊሙ በድምፃችን ይሰማ መሪነት እጅግ የተዋጣለት ትግል በማድረግ መንግስትን ከፊት አድርጎ እስልምና ላይ ያዘመተውን ሊባኖስን መነሻው አድርጉ አህባሽን ሊያጠምቅ የነበረውን ህወሀት መሪ መጅሊስ ማፍረክረክ ቢችልም ከ 2010 ሰላማዊ የመንግስት ሽግሽግ በኃላ እነዚያ ወገናቸው የሆነውን ህዝበ ሙስሊም ስያሰቃዩና ሲዘርፉ ሲያሳስሩ ሲያስግድሉ የነበሩ ርዝራዥ መጅሊሶች ለተወሰነ ጊዜ አንገታቸውን እንደ ሰጎን አሸዋ ውስጥ ቀብረው ሲያደቡ ቆይተው፤ የ2011 የሚያዚያ ጊዚያዊ የፌደራል መጅሊስ ምስረታ በኀላ የተለመደ ስራቸውን በተቀናበረ መልኩ ማከናወን ጀምረዉ ዛሬ ድረስ ሕዝባችንን እያንገላቱ፣ ለሕግ ተገዢ ሳይሆኑ፣ የሀገርን ሠላምና ደህንነት ለማወክ እየተንቀሳቀሱ ለመሆኑ አስረጂ ማቅረብ አያስፈልግም።•••

እንደ ሰጎን አሸዋ ውስጥ ቀብረው በማድባት የሕዝባችንን አንድነት ሲፈታተኑ፣ ፍቅሩን ሲያደፈርሱ ፣ግንኙነቱን ሲያላሉ፤ አብሮነቱን ሲንዱ፤ በቁርጠኝነት የኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞችን ተቋም ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል።

መንግስትና ሠላማዊ ሕዝባችን ላለፉት 3 አመታት በጥልቅ ትዕግስት፣ በተረጋጋ ሁኔታ፣ እድልን ለመስጠት ሲባል ሰላም እየደፈረሰ፤ ትንኮሳዎች እየተፈጸሙ፣ መመሪያ እየተጣሰም ጭምር በዝምታ አልፏል።

ለሦስት አመታት ያህል በዋዘ ያለፈዉን ወሳኝ የተቋም ግንባታ ወቅቶች ሕዝባችንን ቢያስቆጭም፤ እንደ መንግስትም ሕዝቡን ለልማት የሚያሰልፍ መሪ ተቋም ባለመማኖሩ እድገታችንን እንደሀገር የሚጎትት በመሆኑ ቅር ቢያሰኝም- ካለፈው ይልቅ የወደፊቱ በጉጉት የሚጠበቀዉን የህዝባችንን የመጅሊስ ምሥረታ ጥያቄዎች በማጤን ሙስሊም ሙህራንና ሊህቃን፣ መሻይኾች፣ ዓሊሞችና የማህበረሰቡ ወኪሎች፣ በአሁኑ ሰዓት ላይ በመጅሊስ የስልጣን ወንበር ላይ ያሉትን ጨምሮ ከመንግስት ጋር በመሆን ሰፊ ውይይት አድርገዉ ሁሉንም ወገን የሚወክል ሕዝባዊና ለአንድነት የሚሰራ መጅሊስ እንዲቋቋም ከስምምነት ተደርሶ፤ ለነገ ሰኞ ሐምሌ 10/2014 ወሳኝ፣ ታሪካዊ ቀጠሮ ተይዟል።

እንደ ሰጎን አሸዋ ውስጥ ቀብረው ሲያደቡ የነበሩ አንዳንድ አካላት ስለአንድነት፣ ስለሕዝብ፣ ስለተቋም ግንባታ፣... እንደማይጨነቁ በግልጽ አውጀዋል። ትዕግስትን ከረገጠ፣ ሕግን ከጣሰ፣ አንድነትን ከገፋ፤ ፍቅርን ካልተቀበለ፣ ሕብረትን ከናቀ፣ ••• ሜዳውም ይኸው፤ፈረሱም ይኸው ማለት የሕዝባችን ፈንታ ነው። ወደፈለገበት ይሂድ፤ ቀልብ የገዛ ቀን የጥንካሬያችን ምንጭ በሆነው የአንድነት ዋርካችን ስር ይሰባሰባል።

ሙጂብ አሚኖ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
100 views19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 22:15:24
እንግዲህ ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሚከራከሩትና የውሸት ጠበቃ ለመሆን የሚሞክሩት በፅንፈኝነታቸው አንቱታን ያተረፉ ዘረኛ ከፋፋይ ሰዎች እነዚህ ናቸው ድንቄም ለሙስሊም አሳቢ አላሑ ሙስተዐን
95 viewsedited  19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 19:37:54 ስርዓተ አልበኝነትን ሕግን በማስከበር መጠፍነጉ የግድ ነው!



በሶስት አመት ቆይታ ብቻ!...

- ከሸራትን 2011 ጀምሮ አንድነት እንዳይኖር፣ እንዲፈርስ በግልፅ ሲቃወሙ እንደነበር
– ከ2011 በፊት ህዝቡን ሲያስገርፉ፣ በወሸት ምስክር ሲያሳስሩ
– ተቋማዊ ግንባታ እንዳይሳካ

– ከ10 ያላነሱ የሽምግልና ጥረቶችን ሲያሰናክሉ

– ከሐይማኖት ይልቅ የለቲካዊ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮሩ

– ጥቂት ግለሰቦች በተከበረው ሱፊያ ስም እየነገዱ

– ህጋዊ ሂደት ተከትለው የተወሰኑ ውሳኔዎችን ለመተግበር ፈቃደኛ ካለመሆንም አልፈው ስልጣን ከምንለቅ ደም ይፈሳል በማለት

– የሙስሊሙን ሐብት እና ገንዘብ በመዝረፍ

– መንግስትንም ሆነ ህዝበ ሙስሊሙን ለማሳሳት

– የሀገሪቷ ግማሽ አካል የሆነውን ህዝበ ሙስሊም ለልማት እና አገራዊ ግንባታ አስተዋፅኦ እንዳያደርግ ከውስጥ እና ከውጭ አካላት ጋር በመተባበር

– የአንድነት መጅሊሱ የሁሉም ክልል መጅሊሶች በተገኙበት በነገው እለት በሸራተን ሆቴል በሚደረገው የጠቅላላ ጉባኤ በታቀደለት መሰረት የሚካሄድ በመሆኑ ህዝበ ሙስሊሙ በጉጉት የሚጠብቀው መሆኑን በማወቅ ይህንን ታላቅ እድል ለማደናቀፍ በዛሬው እለት እየተሰራ መሆኑ ልብ ይሏል።

በመጅሊሱ ቅጥር ጊቢ ካለፉት ጊዜያት ጀምሮ የሚካሄዱት ውንብድና መሰል እንቅስቃሴዎች፣ ሕገ-ወጥነትን የተላበሱ አካሄዶች፣ በማን አለብኝነት የሚደረጉ ቅስቀሳዎች፣ አንድነትን የሚንዱና ሕዝብ ለሕዝብ ደም እንዲፋሰስ የሚስተጋቡ ድምጾች፣ ተቋምን የማፈራረስ ሂደቶች ፤ ከታሪካዊና ፖለቲካዊ ጠላቶቻችን ጋር በጣምራነት የመስራት ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች፣ ተቋምን ለግለሰቦች እርስትነት የማጽደቅ ክንውኖች፣ ትዉልድ እንዲከስም የታቀዱ እቅዶች፣ ...ወዘተረፈ እኩዮች ከዛሬው ክስተት ጋር በነጠላ ሳይሆን በጣምራነት ልንመለከተዉ የሚገባ አሳፋሪ እንዲሁም ኃይማኖትን ሽፋን በማድረግ ለሀገር ሠላምና ብልጽግና ሳንካ ከሆኑ ቡድኖች ጋር በጋራ የመስራት የሁከት፣ የብጥብጥ አጀንዳ መሆኑ ልብ ይሏል።

የቅርብ ጊዜውን በአዲስ አበባ መጅሊስ ላይ በኃይል ለመያዝ የተደረገውን የውንብድና ተግባር፤ ሎሎችም... ከዚህ ቀደም ደም ለማፋሰስ ሳይቀር የተደረጉ እኩይ እንቅስቃሴዎች በትዕግስት እንደታለፉ የሚታወቅ ሲሆን መንግስትና ሕዝባችን ሆደ ሰፊ በመሆን እንዳስተናገዱት እሙን ነው።

መንግስታችን ጥልቅ በሆን መንገድ ባሳየው ትዕግስትና ጉዳዮችን በጥንቃቄ ለመፍታት ላሳየዉ የተከበረ ተግባር በእጅጉ የምናከበር ሲሆን በተለይም በነገው እለት በሸራተን አዲስ የሚካሄደው ጉባዔ በሠላም እንዲከናወን ላደረገው ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋና እያቀረብን ጥቂቶች ጉባዔውን በተለያየ መልኩ ለማደናቀፍ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ተስተዉለዋል።

መንግስት ላሳየው ሆደ ሰፊነት ምስጋናችንን እያቀረብን ይህ ጥቂት ኃይል ከመማርና ወደሰላም ከመመለስ ይቅል በአፍራሽና አንድነትን በመናድ እንቅስቃሴ/ተግባር ውስጥ በመቀጠሉ መንግስት ሕግ የማስከበር ስራዉን እንዲሰራ አጥብቀን እንጠይቃለን።

ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች በነገዉ እለት በጉጉት የሚጠብቁትን የሸራተን ጉባዔ ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀስ ማንኛውም አካል ከድርጊቱ እንዲቆጠቡና ወደ መልካም ቀልቡ እንዲመለስ እንጠይቃለን።

ሙጂብ አሚኖ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
132 viewsedited  16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 19:28:28 በፌዴራል መንግስቱ ለነገ ሰኞ ሀምሌ 11, 2014 በተጠራው በሸራተን ሆቴል የመጅሊሱ አመራሮችን የማስማማትና የማስመረጥ ስብሰባ በነ ሙፍቲ በኩል ያሉ ወገኖች ስብሰባውን እንደማይሳተፉ አሳወቁ!
--------------
የህዝበ ሙስሊሙ ተቋም ተቋማዊ ይዘቱ ይረጋገጥ ዘንድ የተሰጠው እድልን ተጠቅሞ በፌዴራል ደረጃ እውቅናው ይረጋገጥ ዘንድ እስከዛሬ ብዙ ውጣ ውረዶችን ማለፉ ይታወቃል።
በተለያዩ ግዜያት የመስማማትና የጋራ አቋም ለመያዝ የተደረጉ ሙከራዎች በነሙፍቲ በኩል ሲሰናከሉና ስብሰባዎች ሲሰረዙ፣ የውይይት መድረኮች ሲሰናከሉና ለእርስበርስ ብጥብጥ የሚዳርጉ ክስተቶችን በአላህ እገዛ በቀላሉ ስናሳልፍ ዛሬ ደርሰናል።
ባለፈው ጠቅላይ ሚኒስተሩ ዶ/ር አብይ አህመድ በሁለቱመወ ጎን ያሉ ሙስሊሞችን በመሰብሰብ ወደ አንድ ነጥብ እንዲመጡና ሀምሌ 11 በሸራተን ስብሰባ ተካሂዶ መመረጥ ያለባቸው አካላት ተመርጠው ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ወደ መፍትሄ እንዲመጣ በጠራው መሰረት ለሰኞ ተቀጣጥረው የተለያዩ የነበረ ቢሆንም እነሆ በነሙፍቲ በኩል ያለውና (ሱፍያ) ነን በማለት ከኛ በቀር ላሳር የሚለው ቡድን ፈፅሞ የተቋሙ መፅደቅ እንደማያሳስበውና በጋራ አንድነት ነጥብ የማያምን መሆኑን ባሳየ መልኩ የጠ/ሚኒስትሩን ጥሪ በማፍረስ የነገው ስብሰባ ላይ ለመገኘት ፈቃደኛ አለመሆኑን ዛሬ ባደረገው ስብሰባ አፅድቆ በፊርማ በማረጋገጥ አውጥቷል።

ይኸው ነው። ህዝበ ሙስሊም ሆይ ንቃ!!!
ሱፍያን ፈፅሞ የማይወክሉት እነዚሁ አካላት ከአሽዓሪያ በቀር የመጅሊሱ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ሰለፊያ አይካተትም በሚል ግትር አቋሙ መፅናቱን አሳይቷል።

አላህ የዚህን ህዝብ እንባ የሚያብስበት መልካም ዜናን ያሰማን !!!!

ሁዳ መልቲሚዲያ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
123 views16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 18:41:03 ከሊባኖስ በየሁዳው ፕ/ረ ሀጋይ ኤርሊች ጥናት ወደ ሀገራችን ከገባች 10 አመት አካባቢ የሆናት አህባሽ እንደ አስመጪዋ ወያኔ እኔ ካልመራሁ ሀገር ይፈርሳል እንጂ እያለች ነው ።
ሱፍይነታቸውን የጠበቁና ከአህባሽ ሴራ ነፃ የሆኑት ሱፍዮች ግን አሁንም መጅሊስ የጋራ ነው በሚለው አቋማቸው እንደፀኑ ናቸው ።

ሙሀመድ ፈረጅ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
26 views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 18:32:00 ሀጂ ዑመር ኢድሪስ እንዳሉት ከሆነ"ስልጣኔ የማይነካ መሆኑን ማረጋገጫ ካልተሰጠኝ ስብሰባው ላይ አልገኝም " ገርሞ ይገርማል አሉ ሼይኽ ሙሀመድ ወሌ ረሂመሁሏህ
39 views15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 18:18:20 ሱፊያ ነኝ የሚለው ኃይል መግለጫ አውጥቷል። መንግስትን አፍንጫህን ላስ ብለውታል። ነገ ፕሮግራሙን ሰርዣለሁ ብሏል።

ከዚህ ትዕቢት ጀርባ መንግስት ከሌለ የናፈቀኝ ቀጣዩ ኢፒሶድ ነው።

ዐብድልጀሊል ሼኽ ዓሊ ካሳ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
45 views15:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 16:43:02 ሰበር መረጃ !

#Ethiopia | ነገ በዕለተ-ሰኞ ሐምሌ 11 ቀን 2014፣ በአዲስ አበባ ከተማ፣ በሸራተን ዐዲስ ሆቴል፣ በላሊበላ አዳራሽ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ አካላት የሚመረጡበትን ሁኔታ መንግሥት ያመቻቸ መሆኑን ሁላችንም ሰምተናል፡፡

በተለያየ መልኩ፣ በዚህ ታሪካዊ ኩነት ላይ ይሳተፍ ዘንድ ጥሪው የደረሰው አካል ሁሉ በቦታው በመገኘት ታሪካዊ ሚናውን መወጣት ይኖርበታል፡፡

እስከዛሬ ድረስ መጅሊሱን ለማቋቋም የሚያስችሉንን በርካታ ዕድሎች አበለሻሽተናል፡፡ የነገውም አንድ ተጨማሪ ዕድል ነውና 'ልጅ የሰጡትን ይዞ ያለቅሳል፡፡' እንደሚባለው ዕድሉን ከተጠቀምንበት በኀላ ሌላውን ለሌላ ጊዜ በይደር አቆይተን፣ በነገው ዕለት የኩነቱ ተሳታፊ መሆን አለብን የሚል አስተያየት አለኝ፡፡

Hilal tube


https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
93 views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ