Get Mystery Box with random crypto!

FastMereja.com

የሰርጥ አድራሻ: @fastmereja
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.85K
የሰርጥ መግለጫ

FastMereja.net

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-07-03 16:55:48 ከሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.መ ጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተሰጡ ሹመቶች፡

- ወ/ሮ ሽዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር

- ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር

- አቶ ቀጀላ መርዳሳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር
4.9K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-03 13:57:20
ደራሲ ገጣሚና ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን ህይወቱ ማለፉን አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘግቧል። ለቤተሰቦቹ ለጓደኞቹ እንዲሀም ለጥበብ አፍቃሪዎች መጽናናትን እንመኛለን ሲል ጋዜጣው በሀዘን መግለጫው ገልጿል።
5.8K views10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-02 18:09:57
የአዲስ አበባ ከተማ ኮሪደር ልማት 33 ቢሊዮን ብር እንደወጣበት ተገለፀ
#FastMereja
የአዲስ አበባ ከተማ ኮሪደር ልማት 33 ቢሊዮን ብር እንደወጣበት ተገለፀ። የኮሪደር ልማቱን ተግባራዊ ለማድረግ በተደረገ ጥናት መሰረት ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ የበጀት እቅድ ተይዞለት የነበረ ሲሆን፤ ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ በመሰራቱ በ33 ቢሊዮን ብር እየተገባደደ እንደሆነ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መናገራቸውን ኢቢሲ ዘግበዋል።
***
ትክክለኛው የቴሌግራም ገጻችን ይህ ነው
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja
6.8K views15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-02 12:53:17
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ለ371 አመራሮች ለተከታታይ 5 ወራት የትግርኛ እና የአፋን ኦሮሞ የቋንቋ ስልጠና ሰጠ

ስልጠናው አምስቱ ቋንቋዎች የፌደራል መንግስት የስራ ቋንቋ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ተከትሎ ነው ተብሏል። የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ371 አመራሮች የትግርኛ እና የአፋን ኦሮሞ የቋንቋ ስልጠና ለተከታታይ 5 ወራት ሲሰጥ ቆይቶ ዛሬ ማጠናቀቁን አስታወቀ።

መንግስት ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ አፋን ኦሮሞ፣ትግርኛ፣ሶማሊኛና አፋርኛ ቋንቋዎች የፌደራሉ መንግስት የስራ ቋንቋ እንዲሆኑ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ክፍለ ከተማው አስታውሶ ስልጠናው ይህንን ታሳቢ ያደረገ ስለመሆኑ አስታውቋል።

አመራሮቹ ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ አፋን ኦሮሞና ትግርኛ ቋንቋ ተምረው በዛሬው እለት የማጠቃለያ ፈተና ወስዷል። ከማጠቃለያ ፈተናው በኋላም የምርቃት ስነ ስርዓት ሊኖር እንደሚችል ተጠቁሟል ሲል አዲስ ማለዳ ዘግቧል።
6.8K views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-02 11:20:08
በቱርኪዬ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከቡር ሀካን ፊዳን ጋባዥነት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ እና የሶማሊያ ፌዴራል ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይና ዓለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር ክቡር አህመድ ሞአሊም ፊቂ ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በአንካራ ተገናኝተው ተወያይተዋል።

በቱርኪዬ መንግስት አመቻቺነት የተካሄደው የሁለቱ ሚኒስትሮች ውይይት በሁለቱ አገራት መካከል ላሉ አለመግባባቶች መፍትሄ ሊያመጡ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ግልፅና ወዳጅነት የተሞላበት የሀሳብ ልውውጥ የተደረገበት ነበር።

ሁለቱ ሚኒስትሮች ያሉ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ እልባት ለመስጠት ቁርጠኝነታቸውን የገለጹ ሲሆን የቱርኪዬ መንግስት ውይይቱን ለማመቻቸት ስለተጫወተው ገንቢ ሚናም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሁለቱ ሚኒስትሮች መልካም ጉርብትናን እና ቀጠናዊ መረጋጋትን ከግምት በማስገባት መፍትሄዎችን ለማመላከት ያለሙ ምከከሮችን ለመቀጠልም ተስማምተዋል።

ሁለቱ ሚኒስትሮች የቱርኪዬ ፕሬዚዳንት ከቡር ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ምክክሩን አገራቸው ለማስተናገድ የወሰዱትን ተነሳሽነት በማድነቅ ሁለተኛ ዙር ውይይታቸውን ነሐሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም በአንካራ ለመቀጠል ተስማምተዋል።

የቃል-አቀባይ ጽ/ቤት
5.8K views08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-02 11:07:51
አንድ ሽማግሌ ጮክ ብለው
ፈጣሪ ለችግራችሁ ሁሉ መፍትሄ ይሰጣችኋል እናንተ ብቻ ታገሱ ሲሉ

አንድ ከልጂ ጋር የተቀመጠች እናት
ዝም ብለህ አትቀባጥር ፈጣሪ ሚባል ነገር የለም አለቻቸው

ሽማግሌውም ደንግጠው ዝም አሉ
ፈጣሪም ድጋሚ እንዲናገሩ አደረጋቸው

ሽማግሌውም ቀጠሉ የችግራቸሁ ሁሉ መፍትሄ አንድ አምላክ ነው
ብቻ ታገሱ አሉ

ትግስቷ ያለቀው እናት ተነስታ እኚህን ሽማግሌ መገፈታተር እና መሳደብ ጀመረች

ይህን ጊዜ ታዳጊው እማ እባክሽ መማታትሽን አቁሚ ፈጣሪ የላከው ሰው ነው ብሎ ተናግሮ ሳይጨርስ

እናትየውም መማታቷን አቁማ እግራቸው ላይ ወድቃ ማልቀስ ጀመረች

ሽማግሌውም ለምን ታለቅሻለሽ አሏት
እሷም አለች ልጄ መናገር አይችልም ነበር ለመጀመሪያ ጊዜ አሁን አንደበቱ ተከፈት
ይህን ከፈጣሪ ውጪ ማን ማድረግ ይቸላል አሁን አምኛለሁ ይቅር በሉኝ አለች

አዎ ፈጣሪ ሁሉን ማድረግ ይችላል ለዛም ነው
እኛም ፈጣሪን አስቀድመን በክርስቶስ ሳምራ እና በቅዱስ ሚካኤል ያሉ አባቶች እና እናቶች ችግር ውስጥ ናቸው እንድረስላቸው ቤተልሄሙ በደሳሳ ጎጆ ዉስጥ ናት በመቃኞ ሰርተናት የአባቶችን ምርቃት እንቀበል ዘንድ አነሰ በዛ ሳንል የበረከቱ ተካፋይ እንሆን ዘንድ በክርስቶስ ሰምራ እና ቅዱስ ሚካኤል ስም እንማጸናለን።

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱስ ሚካኤል አድነት  ገዳም

                        ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
                        1000442598391

                              ወይም

                        አቢሲኒያ ባንክ
                        141029444
ለተጨማሪ መረጃ:- 
   የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957     
                         ወይም 0938644444
5.0K views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-02 11:03:35
ተመሳሳይ ውጤት በማምጣት የተመረቁት መንትዮቹ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
#FastMereja
የጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን ከነዚህም መካከል መንትዮቹ ይገኙበታል።

ሁለቱ መንትዮች ከኬጂ ጀምሮ በአንድ ክፍል የተማሩና በጅማ ዩኒቨርሲቲ በባዮሜዲካል ምህንድስና ቆይታቸውም ተመሳሳይ ሲጂፒኤ እንዲሁም የመውጫ ፈተና ውጤት ዮሴፍ ሞላወርቅ የመውጫ ፈተናውን 71 ነጥብ ያመጣ ሲሆን መንታ ወንድሙ ሰለሞን ሞላወርቅ ደግሞ 73 በማምጣት ተመርቀዋል።
5.6K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-02 11:03:05
ኤርትራዊው ቢኒያም ግርማይ በ2024 የቱር ደ ፍራንስ የሳይክል ውድድር መድረክን ያሸነፈ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ ሆኖ ታሪክ ሰርቷል!
#FastMereja
5.1K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-01 18:23:08 ቀለብ ላለመቁረጥ የ4 አመት ልጁ ላይ የግድያ ሙከራ የፈጸመ አባት በእስራት ተቀጣ።
#FastMereja
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን በደኖ ወረዳ ኮዬ ቀበሌ ነዋሪ የሆነዉ ከድር አህመድ የተሰኘዉ ግለሰብ ለልጁ ወርሃዊ ተቆራጭ ላለማድረግ ሲል የአራት አመት ህጻን ልጁ ላይ የግድያ ሙከራ መፈጸሙ ተሰምቷል።

ግለሰቡ በፍቺ ካጠናቀቀዉ የትዳር ህይወቱ ላገኘዉ አንድ የአራት አመት ህጻን ልጅ ላይ ነዉ መርዝ በመስጠት የግድያ ሙከራዉን ያደረገዉ።

ግለሰቡ ጥር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት አክረም ከድር የተሰኘዉ የአራት አመት ህጻን ልጅ ላይ አደገኛ ነዉ ፥ የሰዉልጅንም በፍጥነት ይገድላል የተባለዉን ለጫት ተክል ተባይ ማጥፊያነት የሚገለግል መርዝን በምግብ አድርጎ የሰጠዉ።

ተከሳሽ ህጻን አክረም የሚማርበት ብሪቱ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመሄድ ከጓደኞቹ ጋር ሲጫወት የነበረዉን ጨቅላ በመጥራት እና ከትምህርት ቤቱ በማስወጣት በሚወደዉ ምግብ ዉስጥ መርዙን እንደሰጠዉ ፖሊስ በምርመራው አረጋግጧል ተብሏል።

የአረም ማጥፊያ የተቀላቀለበትን ምግብ የተመገበዉ ህጻን ወደ ትምህርት ቤቱ ቢመለስም በግማሽ ሰዓት ዉስጥ ማስመለስ እና መሬት ላይ ወድቆ መንፈራፈር ይጀምራል።ህጻናት ጓደኞቹ የአክረምን ህመም ተመልክተዉ ለመምህራን በሰጡት ጥቆማ ህጻኖ ወደ በደኖ ጤና ጣቢያ ተልኮ የህክምና እርዳታ አግኝቶ ህይወቱ ሊተርፍ ችሏል።

ከፖሊስ በምርመራዉ ወላጅ አባቱ ባደረገዉ ድርጊት በቁጥጥር ስር አዉሎ ህጻኑ የግድያ ሙከራ እንደተፈጸመበት በሰዉና በህክምና ማስረጃ በማረጋገጥ ያቀረበውን መዝገብ አቃቤ ህግ ክስ የመሰረተ ሲሆን ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተከሳሽ ከድር አህመድ በገዛ ልጁ ላይ የግድያ ሙከራ በመፈጸሙ በ 7 አመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት አስታውቋል።
***
ትክክለኛው የቴሌግራም ገጻችን ይህ ነው
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja
6.3K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-07-01 18:23:06
5.8K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ