Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ12 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ፡፡ #FastMereja አዲ | FastMereja.com

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ12 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ፡፡
#FastMereja
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ12 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ፡፡ ምሁራኑ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው በማስተማር ውጤተማነት፤ ባሰተሟቸው ጥናታዊ ጹሁፎች፤ ላማህበረሰብ ለበረከቱት አካዳሚያዊ አገልግሎትና በዩኒቨርሲቲው በነበራቸው የ ተቋም አስተዳደር ድምር ውጤት ነው። በዚሁ መሰረት፡-

ፕሮፌሰር ይምጡበዝናሽ ወ/አማኑኤል በሜዲካል ማይክሮ ባዮሎጂ
ፕሮፌሰር አንተነህ በለጠ በፍርማሴዩቲክስ
ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ በፕላንት ጄኔቲክስ
ፕሮፌሰር አህመደ ሁሴን በአናሊቲካል ኬሚስትሪ
ፕሮፌሰር ታደሰ እጓለ በማይክሮባዮሎጂ
ፕሮፌሰር ተክለሀይማኖት ኃ/ሥላሴ በፕላንት ባዮቴክኖሎጂ
ፕሮፌሰር ተሸመ ሰንበታ በኮንደንስድ ማተር ፊዝክስ
ፕሮፌሰር እንጉዳይ አደመ በካሪኩለም ጥናት
ፕሮፈፌሰር ሀብቴ ተኪኤ በሜዲካል ኢንቶሞሎጂ
ፕሮፌሰር ቃላብ ባዬ በ ሂዩማን ኒውትሪሽን
ፕሮፌሰር ሰለሞን ሙሉጌታ በአርባን ፕላኒንግ
ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ፍሰሀ በፖሊዮኢንቨሮመንታል ጥናት ናቸው።

ወደ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ካደጉት መካከል ሁለት ሴት ምሁራን የሚገኙበት ሲሆን ይህም በአንድ ግዜ ሁለት ሴት ፕሮፌሰሮች ማዕረጉን ያገኙበት ልዩ ያደርገዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ''ስለ ራስገዝ ዩኒቨርሰቲ ለመደንገግ በወጣ'' አዋጅ ቁጥር 1294/2015 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ነው በዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቀረቡለትን የማዕረግ እድገት ያጸደቀው፡፡