Get Mystery Box with random crypto!

Debre Birhan University Info

የቴሌግራም ቻናል አርማ debreberhan_university — Debre Birhan University Info D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debreberhan_university — Debre Birhan University Info
የሰርጥ አድራሻ: @debreberhan_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.16K

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2022-05-22 10:58:24
የሀዘን መግለጫ
ተማሪ እመቤት ደረጄ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ natural science ተማሪ ስትሆን ባደረባት ጽኑ ህመም በህክምና ስትረዳ ቆይታ በቀን 13/92014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት አርፋለች::

በተማሪያችን ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቿ ለወዳጅ ዘመዶቿ ለጓደኞቿ እንዲሁም ለደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና መላው ማህበረሰብ መጽናናትን እንመኛለን።
@debreberhan_university
@debreberhan_university
4.7K viewsedited  07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:54:41 ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለሴት የአሰተዳደር ሰራተኞች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ

የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሴቶችና ህጻናት ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ለሴት የአሰተዳደር ሰራተኞች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ፡፡በስልጠናው በማህበራዊው፣ በኢኮኖሚው፣ በፓለቲካውና በሌሎችም ዘርፎች የሴቶች ተሳትፎ ሊጎለብት እንደሚገባው ተገልጿል።

የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሴቶችና ህጻናት ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አዲስ አስፋወሰን በስልጠናው ወቅት እንደተናገሩት ሴቶች በማህበራዊው፣ በኢኮኖሚው፣ በፓለቲካውና በሌሎችም ዘርፎች ያላቸው ተሳትፎና ተጠቃሚነት ውስን በመሆኑ ተሳትፏቸው ሊጎለብት ይገባል ብለዋል።ስልጠናው 100 ለሚሆኑ የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሴት የአስተዳደር ሰራተኞች እንደተሰጠ ገልጸው ግንዛቤውን ካገኙ በኋላም ልምዶቻቸውንና ያገኙትን ተሞክሮ ለሌሎች የሚያጋሩ ይሆናል ብለዋል። አክለውም እንደዚህ አይነቱ ስልጠና ሴቶችን ለአመራርነት በማብቃት ደረጃም ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በስነ ልቦናና ስነ ማህበረሰብ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት አቶ ዘነበ ደምሴ “ጀግኒትን ማጀገን” (Women Empowerment) በሚል ርዕስ የስልጠናውን ጽሁፍ በማዘጋጀት በየጊዜው ሴቶችን እያሰለጠኑ የሚገኙ ሲሆን የዛሬውን የስልጠና አላማ ሲገልጹ ጀግኒት እየገጠሟት ያሉትን ተግዳሮቶች በመለየት የጀግንነት ጉዞዋን እንድትቀጥል ማድረግ ነው ብለዋል። በተጨማሪም እውቅና እንድታገኝና የበለጠ የምትጀግንባቸውን መሰረታዊ ጉዳዮች በመለየት ማጀገን እንደሆነ ተናግረዋል።አገልግሎታቸው ለማይታወቁ ጉዳዮች ዋጋ መስጠትን፣ሲማሩ ደግሞ ጀግና ነኝ ማለትን እንዲለማመዱ እድል እንደሚፈጥርላቸውም አክለው ተናግረዋል።

ሰልጣኞቹ በበኩላቸው ከቤት ውስጥ ስራችን ጀምሮ ትልቅ ሃላፊነት ተጥሎብን ይህንን ሃላፊነት እየተወጣን ብንገኝም ጀግንነታችንን ሳንረዳ ቆይተናል ብለዋል።
ከስልጠናው በኋላም ያገኙትን ልምድና ተሞክሮ ለሌሎች በማካፈል እንደሚጠቀሙበትና በትምህርቱ፣ በጤናው፣ በማህበራዊው፣ በኢኮኖሚው፣ በሁሉም ዘርፎች ከቤት ውስጥ ሃላፊነት ጀምሮ ለጀግንነታቸው እውቅና እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
@debreberhan_university
@debreberhan_university
4.1K viewsedited  11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:54:27
3.1K views11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 16:02:33
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የሆነው ናትናኤል ብርሃኑ የግጥም መድብሉን ተጋባዝ እንግዶች ቤተሰቦቹ እንዲሁም አድናቂዎቹ በተገኙበት በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መመረቂያ አዳራሽ ዛሬ ግንቦት 06, 2014 ዓ.ም በይፋ አስመርቋል!
ተማሪ ናትናኤል እንኳን ደስ አለህ!

@debreberhan_university
4.2K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 12:39:24
ግንቦት 6 ቀን 1991 ዓ.ም - ፕ/ር አስራት ወልደየስ

ፕ/ር አስራት ወልደየስ የህዝብ ግድያ እና ማፈናቀል፣ ሰውን በዘሩ እና በማንነቱ መግደል እስካላቆናችሁ ድረስ በእናተ በገዳዮች ፊት ቆሜ ልሟገታችሁ ቃል እገባለሁ በማለት ጥር 14/1984 ዓ.ም በተናገሩት ጥርስ ተነክሶባቸው ስመ ጥር ሀኪም ሆነው ህክምና ተከልክለው ህይወታቸው ያለፈ ምሁር ነበሩ ።

ፕ/ር አስራት ወልደየስ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅትን መስርተው ለህዝብ እኩልነት ፣ መብት ፣ ነፃነት ሲታገሉ በኢህአዴግ መንግስት ታስረውና ህክምና ተነፍገው ከ23 ዓመታተ በፊት ግንቦት 6 ቀን 1991ዓ.ም ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል።

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲም በስማቸው ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስን ሰይሟል ::
@debreberhan_university
4.1K viewsedited  09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ