2024-04-18 20:38:06
ሚያዚያ 9/2016 ዓ·ም
የድል ዜና
በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በከሰም ክፍለ ጦር በተስፋ ብርጌድ ፣ በነበልባል ብርጌድ እና በኃይለማርያም ማሞ ብርጌድ በተደረገ ውጊያ ከፍተኛ ድል ተቀዳጀ።
በአርበኛ እና ደራሲ አሰግድ መኮንን የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ተስፋ ብርጌድ ዛሬ ታላቅ ድል ተቀዳጀ። በበረኸት ወረዳ የሚንቀሳቀሰው እና በ ፶/አለቃ ጎሽመው ኃይሌ የሚመራው ተስፋ ብርጌድ ዛሬ ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 9:00 ሰዓት ድረስ ለተከታታይ 8 ሰዓት እራሱን ጥምር ጦር ብሎ ከሚጠራው የአገዛዙ ጠባቂ ሰራዊት ጋር ከፍተኛ ትንቅንቅ በማድረግ እንዲሁም የአገዛዙን ሰራዊት በመደምሰስ ከፍተኛ ሙት እና ቁስለኛ ያደረገ ሲሆን ምርኮዎችንም አግኝቷል።
በዕለቱ ጦርነት በተደረገባቸው 09 ቀበሌ፣ 02 ቀበሌ፣ ዋንሴ፣ ፍርዱ ሃገር፣ደመወዜ፣ አቤቶ እና መሃል በረኸት ላይ ወራሪው ሃይል ተደምስሶ 3000 (ሶስት ሽህ) የክላሽ ጥይት፣50 የጀርባ ቦርሳ እና በርካታ ክላሽ ኮፍ መሳሪያዎችን ተኩሰው የማይስቱት ብቻ ሳይሆን ጭንቅላት የሚመቱት የበረኸቶቹ የበረሃ ነብሮች በምርኮ ገቢ ያደረጓቸው የጠላት ሃብትም ወደ ተስፋ ብርጌድ ገቢ ተደርጓል።
በምንጃር አረርቲ ከተማ የስርዓቱ ጠባቂ ጥምር ሃይል በካምፕነት በሚጠቀምበት የምንጃር ሸንኮራ የወረዳው ፖሊስ ጣቢያ ላይ አዳሩን የነበልባል ብርጌድ እርምጃ ወሰደ። ዛሬ ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ላይ የምንጃር ሸንኮራ ክንደ ብርቱዎቹ የነበልባል ብርጌድ ፉኖዎች በከተማዋ ሰርጎ በመግባት በወራሪው የሃገር መከላከያ ፣ የአማራ አድማ ብተና እና የአማራ ሚሊሻ ላይ እርምጃ በመውሰድ እራሱን ጥምር ጦር ብሎ በሚጠራው ሃይል ላይ ድገተኛ ጥቃት በማድረስ በርካቶችን ገድለው እና አቁስለው እቅዳቸውን ሙሉ አሳክተው በፋኖ ላይ ምንም ጉዳት ሳይደርስ ከአረርቲ ከተማ ለቀው ወተዋል።
በተያዘ ዜና በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በከሰም ክፍለ ጦር በነበልባል ብርጌድ በሸንኮራ ንኡስ ወረዳ በባልጪ ከተማ የአገዛዙ ሃይል በካምፕነት በሚጠቀምበት ፖሊስ ጣቢያ ላይ ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ላይ ፋኖዎቹ ሰርገው በመግባት እራሱን ጥምር ጦር ብሎ በሚጠራው ሃይል ላይ እርምጃ በመውሰድ በርካቶችን በመግደል እና በማቁሰል የነበልባል ብርጌድ ባቀደው መሰረት ኦፕሬሽኑን ሰርቶ ምንም ጉዳት ሳያስተናግድ የባልጪ ከተማን ከለሊቱ 9:00ሰዓት ላይ ለቆ ወቷል።
አዳሩን ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደው ወራሪ ሃይል በደረሰበት ጉዳት በእጅጉ በመናደዱ የበቀል በትሩን ዛሬ ቀኑን ሙሉ በምንጃር አረርቲ ከተማ የሚኖሩ ንፁሃን አማራዎችን፣ የባጃጅ አሽከርካሪዎችን እና የከተማዋን ነዋሪ ሲደበድብ እና ሲያስር ውሏል። ይህ የሚያሳየው የስርዓቱን ተስፋ መቁረጥ እና የውድቀት ዋዜማ ላይ መሆኑን ነው።
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የከሰም ክፍለ ጦር የሃይለማርያም ማሞ ብርጌድ በሃገረ ማርያም ከሰም ወረዳ በሾላ ገበያ ከተማ ክንደ ነበልባሎቹ የአርበኛው የሃይለማርያም ማሞ የመንፈስ ልጆች ከለሊቱ 9:00 ሰዓት ወደ ከተማዋ በመግባት በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ጥቃት አደረሱ። ፋኖዎቹ ጥምር ጦሩ በሰፈረበት ቦታ በመጠጋት በተለምዶ ካንቦ ማርያም በሚባል አካባቢ እና አስተዳደር ግቢ በመግባት ጥቃት በማድረስ የስርዓቱን አስጠባቂ ሃይል ሙት እና ቁስለኛ አድርገው ተልእኳቸውን አሳክተው ያለምንም ጉዳት ስራቸውን ሰርተው ከተማዋን ለቀው ወተዋል።
የከሰም ክፍለጦር በስሩ ካሉት አራት ብርጌዶች ውስጥ ሶስቱን አናቦ ስራ በመስራቱ የተሻለ ውጤት እንዲገኝ አድርጓል። አማራ ሲናበብ እና ሲተባበር ጠላቱን ያሸንፋል።
ድል ለአማራ ፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!
5.2K views17:38