ተሻገሩ ፡ ብሎ ፡ አዞ ፡ በውኃ ፡ ሚያስበላ ኧረ ፡ እስቲ ፡ ንገሩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ይሆን ፡ ወይስ ፡ ሌላ መፈጸም ፡ አቅቶት ፡ ከአፉ ፡ የወጣውን ፡ ቃል ይቅርታ ፡ ጠይቆ ፡ ወይ ፡ ረዳት ፡ ፈልጐ ፡ እርሱ ፡ መች ፡ ያውቃል ይሄ ፡ ግን ፡ የማውቀው ፡ ጀምሮ ፡ ፈጻሚ ጠላት ፡ የመጣ ፡ እንደው ፡ እራሱን ፡ አስቀዳሚ እነርሱን ፡ ተዉአቸው ፡ እኔን ፡ ያዙኝ ፡ የሚል ከአውሬም ፡ መንጋጋ ፡ በጐቹን ፡ የሚያስጥል አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው ለአብርሃም ፡ ተናግሮ ፡ ነግሮ ፡ ለይሳቅ ፡ አጸና ለይሳቅ ፡ ተናግሮ ፡ ለያቆብ ፡ ፈጸመ ፡ እርሱ ፡ አይዋሽምና ዮሴፍ ፡ በግብጽ ፡ ምድር ፡ ቢወርድ ፡ ቢገባም ፡ ተሽጦ የፈርዖን ፡ መንግሥት ፡ ገዢ ፡ አደረገው ፡ ስርአት ፡ ለውጦ እግዚአብሔር ፡ ደክሟል ፡ አረጀ ፡ ያለ ፡ ማነው እኔስ ፡ እስከሚገባኝ ፡ ዛሬም ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነው የእኔ ፡ እምነት ፡ ቢፈተን ፡ ቢለዋወጥበት እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ ታምኖ ፡ አለ ፡ እዚያው ፡ ባለበት አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው በልዑል ፡ መጠጊያ ፡ አንባ ፡ መሽጐ ፡ ሚኖር ሁሉንም ፡ በሚችል ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ያድራል ፡ ከቶ ፡ አይሸበርም ከአዳኞች ፡ ወጥመድ ፡ ከሚያስደነግጥም ፡ ነገር ከክፉ ፡ ከልሎ ፡ ይታደገው ፡ የለ ፡ ሕያው ፡ እግዚአብሔር የቀኑ ፡ ፍላጻ ፡ የሌሊቱ ፡ ግርማ ፡ አደጋና ፡ ጋኔል ፡ ተጓዥ ፡ በጨለማ ሺ ፡ በሺ ፡ ሲያረግፈው ፡ ሲያስረግጠኝ ፡ ኖርኩኝ @astemiren @zilivingword 719 viewsBINU, 12:18