Get Mystery Box with random crypto!

ተሻገሩ ፡ ብሎ ፡ አዞ ፡ በውኃ ፡ ሚያስበላ ኧረ ፡ እስቲ ፡ ንገሩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ | The words of eternal life

ተሻገሩ ፡ ብሎ ፡ አዞ ፡ በውኃ ፡ ሚያስበላ
ኧረ ፡ እስቲ ፡ ንገሩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ይሆን ፡ ወይስ ፡ ሌላ
መፈጸም ፡ አቅቶት ፡ ከአፉ ፡ የወጣውን ፡ ቃል
ይቅርታ ፡ ጠይቆ ፡ ወይ ፡ ረዳት ፡ ፈልጐ ፡ እርሱ ፡ መች ፡ ያውቃል
ይሄ ፡ ግን ፡ የማውቀው ፡ ጀምሮ ፡ ፈጻሚ
ጠላት ፡ የመጣ ፡ እንደው ፡ እራሱን ፡ አስቀዳሚ
እነርሱን ፡ ተዉአቸው ፡ እኔን ፡ ያዙኝ ፡ የሚል
ከአውሬም ፡ መንጋጋ ፡ በጐቹን ፡ የሚያስጥል

አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው
አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው
መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

ለአብርሃም ፡ ተናግሮ ፡ ነግሮ ፡ ለይሳቅ ፡ አጸና
ለይሳቅ ፡ ተናግሮ ፡ ለያቆብ ፡ ፈጸመ ፡ እርሱ ፡ አይዋሽምና
ዮሴፍ ፡ በግብጽ ፡ ምድር ፡ ቢወርድ ፡ ቢገባም ፡ ተሽጦ
የፈርዖን ፡ መንግሥት ፡ ገዢ ፡ አደረገው ፡ ስርአት ፡ ለውጦ
እግዚአብሔር ፡ ደክሟል ፡ አረጀ ፡ ያለ ፡ ማነው
እኔስ ፡ እስከሚገባኝ ፡ ዛሬም ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነው
የእኔ ፡ እምነት ፡ ቢፈተን ፡ ቢለዋወጥበት
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ ታምኖ ፡ አለ ፡ እዚያው ፡ ባለበት

አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው
አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው
መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

በልዑል ፡ መጠጊያ ፡ አንባ ፡ መሽጐ ፡ ሚኖር
ሁሉንም ፡ በሚችል ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ያድራል ፡ ከቶ ፡ አይሸበርም
ከአዳኞች ፡ ወጥመድ ፡ ከሚያስደነግጥም ፡ ነገር
ከክፉ ፡ ከልሎ ፡ ይታደገው ፡ የለ ፡ ሕያው ፡ እግዚአብሔር
የቀኑ ፡ ፍላጻ ፡ የሌሊቱ ፡ ግርማ ፡ አደጋና ፡ ጋኔል ፡ ተጓዥ ፡ በጨለማ
ሺ ፡ በሺ ፡ ሲያረግፈው ፡ ሲያስረግጠኝ ፡ ኖርኩኝ
@astemiren


@zilivingword